TIKVAHETHMAGAZINE Telegram 23901
#ምንጃር_ሸንኮራ

በሀገራችን ኢትዮጵያ የጥምቀት በዓል በደመቀ ሁኔታ ከሚከበርባቸው ቦታዎች አንዱ በምንጃር ሸንኮራ ኢራንቡቲ ነው። በዓሉ በዚህ አከባቢ መከበር ከጀመረ ዘንድሮ ለ623 ኛ ጊዜ መሆኑ ተነግሯል።

በተለይም የሸንኮራ ወንዝ ዳርቻ ባለው ኢራንቡቲ 44 ታቦታት በአንድነት የሚያድሩበት ልዩ ጥምቀተ ባህር መሆኑ ይነገርለታል።

ቀደምት አበው ይህን የሸንኮራ ወንዝ ዳርቻ ለባህረ ጥምቀትነት የመረጡበትን ምክንያት ኢየሱስ ክርስቶስ ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ ማምራቱን በማሰብ ተፈጥሮአዊ ወንዝ ፍለጋ እንደሆነ የአካባቢው የቤተ ክርስቲያን አገልጋዮች ይገልጻሉ።

የሸንኮራ ወንዝ ለጥምቀተ ባህርነት ሲመረጥ ወንዙ እንደ ዮርዳኖስ ከላይ ከመነሻው አንድ ሆኖ መሀል ላይ ለሁለት ተከፍሎ ዝቅ ብሎ የሚገናኝ፣ ውኃውም ከምዕራብ ወደ ምሥራቅ የሚፈስ መሆኑ ከዮርዳኖስ ወንዝ ጋር ስለሚያመሳስለው እንደሆነም ይነገራል።

በተጨማሪም ከመነሻው ጀምሮ የ44ቱም ታቦታት ጸበል መኖሩ ለጥምቀቱ ያለውን ተምሳሌትነት ከፍ ያደርገዋል

ለአከባቢው ማኅበረሰብ የጥምቀት በዓል ከሃይማኖታዊ በዓልነቱ በተጨማሪ ያለፈውን በሙሉ የሚጋብዝበትና ማኅበራዊ እሴቱን የሚያሳይበት በዓሉ ነው።

ለወትሮው ከሌሎች አከባቢዎች የሚመጡ በርካታ ጎብኚዎችን የሚያስተናግደው ኢራንቡቲ ዘንድሮ ካለው የጸጥታ ችግር ምክንያት በርካታ ምዕመኖችን በስፍራው አልተገኙም።

ፎቶ: ምንጃር ሸንኮራ ወረዳ ኮሚኒኬሽን
Credit: SBS Radio

@tikvahethmagazine



tgoop.com/tikvahethmagazine/23901
Create:
Last Update:

#ምንጃር_ሸንኮራ

በሀገራችን ኢትዮጵያ የጥምቀት በዓል በደመቀ ሁኔታ ከሚከበርባቸው ቦታዎች አንዱ በምንጃር ሸንኮራ ኢራንቡቲ ነው። በዓሉ በዚህ አከባቢ መከበር ከጀመረ ዘንድሮ ለ623 ኛ ጊዜ መሆኑ ተነግሯል።

በተለይም የሸንኮራ ወንዝ ዳርቻ ባለው ኢራንቡቲ 44 ታቦታት በአንድነት የሚያድሩበት ልዩ ጥምቀተ ባህር መሆኑ ይነገርለታል።

ቀደምት አበው ይህን የሸንኮራ ወንዝ ዳርቻ ለባህረ ጥምቀትነት የመረጡበትን ምክንያት ኢየሱስ ክርስቶስ ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ ማምራቱን በማሰብ ተፈጥሮአዊ ወንዝ ፍለጋ እንደሆነ የአካባቢው የቤተ ክርስቲያን አገልጋዮች ይገልጻሉ።

የሸንኮራ ወንዝ ለጥምቀተ ባህርነት ሲመረጥ ወንዙ እንደ ዮርዳኖስ ከላይ ከመነሻው አንድ ሆኖ መሀል ላይ ለሁለት ተከፍሎ ዝቅ ብሎ የሚገናኝ፣ ውኃውም ከምዕራብ ወደ ምሥራቅ የሚፈስ መሆኑ ከዮርዳኖስ ወንዝ ጋር ስለሚያመሳስለው እንደሆነም ይነገራል።

በተጨማሪም ከመነሻው ጀምሮ የ44ቱም ታቦታት ጸበል መኖሩ ለጥምቀቱ ያለውን ተምሳሌትነት ከፍ ያደርገዋል

ለአከባቢው ማኅበረሰብ የጥምቀት በዓል ከሃይማኖታዊ በዓልነቱ በተጨማሪ ያለፈውን በሙሉ የሚጋብዝበትና ማኅበራዊ እሴቱን የሚያሳይበት በዓሉ ነው።

ለወትሮው ከሌሎች አከባቢዎች የሚመጡ በርካታ ጎብኚዎችን የሚያስተናግደው ኢራንቡቲ ዘንድሮ ካለው የጸጥታ ችግር ምክንያት በርካታ ምዕመኖችን በስፍራው አልተገኙም።

ፎቶ: ምንጃር ሸንኮራ ወረዳ ኮሚኒኬሽን
Credit: SBS Radio

@tikvahethmagazine

BY TIKVAH-MAGAZINE






Share with your friend now:
tgoop.com/tikvahethmagazine/23901

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

Concise How to Create a Private or Public Channel on Telegram? "Doxxing content is forbidden on Telegram and our moderators routinely remove such content from around the world," said a spokesman for the messaging app, Remi Vaughn. Done! Now you’re the proud owner of a Telegram channel. The next step is to set up and customize your channel. The Standard Channel
from us


Telegram TIKVAH-MAGAZINE
FROM American