TIKVAHETHMAGAZINE Telegram 23936
በደቡብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የቤንዚን ምርት ሽያጭ በኩፖን እንዲሆን ተወሰነ።

የደቡብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ንግድና ገቢያ ልማት ቢሮ ለሁሉም ዞን ንግድና ገቢያ ልማት መምሪያ ዛሬ ተጽፎ በተሰራጨው ሰልኩላር ደብዳቤ መሰረት ከጥር 30 ጀምሮ ሁሉም የነዳጅ ማደያ ያለባቸው ከተሞች ከጥር 30/2017 ጀምሮ ነዳጅ በኩፖን እንዲሸጥ ትዕዛዝ አስተላልፏል።

ቢሮው የነዳጅ ምርት እጥረቱ ከጊዜ ወደ ጊዜ ከመሻሻል ይልቅ እየተባባሰ ከመምጣቱ ጋር ተያይዞ በተለይ የባለ ሁለት እግር ሞተሮች በየቀኑ ተመላልሶ መቅዳት ለኮንትሮባንድ ሽያጭ ከፍተኛ አስተዋጽኦ በማድረግ ለችግሩ መባባስ ዋነኛ መንስኤዎች መሆናቸውን ከተደረገው ክትትል ለማረጋገጥ ተችሏል ብሏል።

በአንዳንድ የክልሉ ከተሞች የኩፖን ሥርዓት በመዘርጋቱ ሥርጭት ላይ ያለውን የቤንዚን ምርት በአግባቡ ማሰራጨት መቻሉንና ለክትትልም ምቹ ሁኔታ መፈጠሩን ማስተዋሉን ነው በደብዳቤው የጠቀሰው።

በመሆኑም የነዳጅ ማደያ ያለባቸው ከተሞች ከጥር 30/2017 ዓ.ም ጀምሮ የትኛውም ተሽከርካሪ በኩፖን ብቻ እንዲስተናገድ እና ታርጋ የሌላቸው ተሽከርካሪዎች ሀጋዊ የተሽከርካሪ ሠሌዳ እስኪያወጡ ድረስ የግልም ሆነ የመንግስት ተሽከርካሪዎች እንዳይስተናገዱ ሲል በደብዳቤው ጠቅሷል።

ቢሮው አክሎም "ህገ-ወጥ የሆኑትን ማክሰም አስፈላጊ በመሆኑ ተግባራዊ እንዲደረግ እየገለጽን የነዳጅ ምርት ሽያጭም ቢሆን በኤሌክትሮኒክስ ቴሌ ብር እና ሲቢኢ ብር/ የመገበያያ መንገዶች ብቻ እንዲፈጸም በጥብቅ እናሳስባለን፡፡" ሲል በሰርኩላር ደብዳቤው አስታውቋል።

ከዚህ ቀደም ወላይታ ሶዶ ከተማ፤ ወራቤ ከተማ፤ ዲላ ከተማ በዚሁ መልኩ ሲጠቀሙ ቆይተዋል። በክልሉ ይተግበር ስለተባለው የኩፖን አሰራር ዙሪያ የሚመለከታቸውን አካላት አናግረን ተጨማሪ መረጃዎችን የምናደርሳችሁ ይሆናል።

💬 ለመሆኑ የኩፖን አሰራር ተግባራዊ በተደረገባቸው ከተሞች ምን ለውጥ ነበረው በአከባቢው ያላችሁ የቲክቫህ ቤተሰቦች ተሞክሯችሁን አካፍሉን

@tikvahethmagazine
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM



tgoop.com/tikvahethmagazine/23936
Create:
Last Update:

በደቡብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የቤንዚን ምርት ሽያጭ በኩፖን እንዲሆን ተወሰነ።

የደቡብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ንግድና ገቢያ ልማት ቢሮ ለሁሉም ዞን ንግድና ገቢያ ልማት መምሪያ ዛሬ ተጽፎ በተሰራጨው ሰልኩላር ደብዳቤ መሰረት ከጥር 30 ጀምሮ ሁሉም የነዳጅ ማደያ ያለባቸው ከተሞች ከጥር 30/2017 ጀምሮ ነዳጅ በኩፖን እንዲሸጥ ትዕዛዝ አስተላልፏል።

ቢሮው የነዳጅ ምርት እጥረቱ ከጊዜ ወደ ጊዜ ከመሻሻል ይልቅ እየተባባሰ ከመምጣቱ ጋር ተያይዞ በተለይ የባለ ሁለት እግር ሞተሮች በየቀኑ ተመላልሶ መቅዳት ለኮንትሮባንድ ሽያጭ ከፍተኛ አስተዋጽኦ በማድረግ ለችግሩ መባባስ ዋነኛ መንስኤዎች መሆናቸውን ከተደረገው ክትትል ለማረጋገጥ ተችሏል ብሏል።

በአንዳንድ የክልሉ ከተሞች የኩፖን ሥርዓት በመዘርጋቱ ሥርጭት ላይ ያለውን የቤንዚን ምርት በአግባቡ ማሰራጨት መቻሉንና ለክትትልም ምቹ ሁኔታ መፈጠሩን ማስተዋሉን ነው በደብዳቤው የጠቀሰው።

በመሆኑም የነዳጅ ማደያ ያለባቸው ከተሞች ከጥር 30/2017 ዓ.ም ጀምሮ የትኛውም ተሽከርካሪ በኩፖን ብቻ እንዲስተናገድ እና ታርጋ የሌላቸው ተሽከርካሪዎች ሀጋዊ የተሽከርካሪ ሠሌዳ እስኪያወጡ ድረስ የግልም ሆነ የመንግስት ተሽከርካሪዎች እንዳይስተናገዱ ሲል በደብዳቤው ጠቅሷል።

ቢሮው አክሎም "ህገ-ወጥ የሆኑትን ማክሰም አስፈላጊ በመሆኑ ተግባራዊ እንዲደረግ እየገለጽን የነዳጅ ምርት ሽያጭም ቢሆን በኤሌክትሮኒክስ ቴሌ ብር እና ሲቢኢ ብር/ የመገበያያ መንገዶች ብቻ እንዲፈጸም በጥብቅ እናሳስባለን፡፡" ሲል በሰርኩላር ደብዳቤው አስታውቋል።

ከዚህ ቀደም ወላይታ ሶዶ ከተማ፤ ወራቤ ከተማ፤ ዲላ ከተማ በዚሁ መልኩ ሲጠቀሙ ቆይተዋል። በክልሉ ይተግበር ስለተባለው የኩፖን አሰራር ዙሪያ የሚመለከታቸውን አካላት አናግረን ተጨማሪ መረጃዎችን የምናደርሳችሁ ይሆናል።

💬 ለመሆኑ የኩፖን አሰራር ተግባራዊ በተደረገባቸው ከተሞች ምን ለውጥ ነበረው በአከባቢው ያላችሁ የቲክቫህ ቤተሰቦች ተሞክሯችሁን አካፍሉን

@tikvahethmagazine

BY TIKVAH-MAGAZINE






Share with your friend now:
tgoop.com/tikvahethmagazine/23936

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

Activate up to 20 bots On Tuesday, some local media outlets included Sing Tao Daily cited sources as saying the Hong Kong government was considering restricting access to Telegram. Privacy Commissioner for Personal Data Ada Chung told to the Legislative Council on Monday that government officials, police and lawmakers remain the targets of “doxxing” despite a privacy law amendment last year that criminalised the malicious disclosure of personal information. The optimal dimension of the avatar on Telegram is 512px by 512px, and it’s recommended to use PNG format to deliver an unpixelated avatar. Hui said the messages, which included urging the disruption of airport operations, were attempts to incite followers to make use of poisonous, corrosive or flammable substances to vandalize police vehicles, and also called on others to make weapons to harm police. The public channel had more than 109,000 subscribers, Judge Hui said. Ng had the power to remove or amend the messages in the channel, but he “allowed them to exist.”
from us


Telegram TIKVAH-MAGAZINE
FROM American