TIKVAHETHMAGAZINE Telegram 23937
በደቡብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የቤንዚን ምርት ሽያጭ በኩፖን እንዲሆን ተወሰነ።

የደቡብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ንግድና ገቢያ ልማት ቢሮ ለሁሉም ዞን ንግድና ገቢያ ልማት መምሪያ ዛሬ ተጽፎ በተሰራጨው ሰልኩላር ደብዳቤ መሰረት ከጥር 30 ጀምሮ ሁሉም የነዳጅ ማደያ ያለባቸው ከተሞች ከጥር 30/2017 ጀምሮ ነዳጅ በኩፖን እንዲሸጥ ትዕዛዝ አስተላልፏል።

ቢሮው የነዳጅ ምርት እጥረቱ ከጊዜ ወደ ጊዜ ከመሻሻል ይልቅ እየተባባሰ ከመምጣቱ ጋር ተያይዞ በተለይ የባለ ሁለት እግር ሞተሮች በየቀኑ ተመላልሶ መቅዳት ለኮንትሮባንድ ሽያጭ ከፍተኛ አስተዋጽኦ በማድረግ ለችግሩ መባባስ ዋነኛ መንስኤዎች መሆናቸውን ከተደረገው ክትትል ለማረጋገጥ ተችሏል ብሏል።

በአንዳንድ የክልሉ ከተሞች የኩፖን ሥርዓት በመዘርጋቱ ሥርጭት ላይ ያለውን የቤንዚን ምርት በአግባቡ ማሰራጨት መቻሉንና ለክትትልም ምቹ ሁኔታ መፈጠሩን ማስተዋሉን ነው በደብዳቤው የጠቀሰው።

በመሆኑም የነዳጅ ማደያ ያለባቸው ከተሞች ከጥር 30/2017 ዓ.ም ጀምሮ የትኛውም ተሽከርካሪ በኩፖን ብቻ እንዲስተናገድ እና ታርጋ የሌላቸው ተሽከርካሪዎች ሀጋዊ የተሽከርካሪ ሠሌዳ እስኪያወጡ ድረስ የግልም ሆነ የመንግስት ተሽከርካሪዎች እንዳይስተናገዱ ሲል በደብዳቤው ጠቅሷል።

ቢሮው አክሎም "ህገ-ወጥ የሆኑትን ማክሰም አስፈላጊ በመሆኑ ተግባራዊ እንዲደረግ እየገለጽን የነዳጅ ምርት ሽያጭም ቢሆን በኤሌክትሮኒክስ ቴሌ ብር እና ሲቢኢ ብር/ የመገበያያ መንገዶች ብቻ እንዲፈጸም በጥብቅ እናሳስባለን፡፡" ሲል በሰርኩላር ደብዳቤው አስታውቋል።

ከዚህ ቀደም ወላይታ ሶዶ ከተማ፤ ወራቤ ከተማ፤ ዲላ ከተማ በዚሁ መልኩ ሲጠቀሙ ቆይተዋል። በክልሉ ይተግበር ስለተባለው የኩፖን አሰራር ዙሪያ የሚመለከታቸውን አካላት አናግረን ተጨማሪ መረጃዎችን የምናደርሳችሁ ይሆናል።

💬 ለመሆኑ የኩፖን አሰራር ተግባራዊ በተደረገባቸው ከተሞች ምን ለውጥ ነበረው በአከባቢው ያላችሁ የቲክቫህ ቤተሰቦች ተሞክሯችሁን አካፍሉን

@tikvahethmagazine
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM



tgoop.com/tikvahethmagazine/23937
Create:
Last Update:

በደቡብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የቤንዚን ምርት ሽያጭ በኩፖን እንዲሆን ተወሰነ።

የደቡብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ንግድና ገቢያ ልማት ቢሮ ለሁሉም ዞን ንግድና ገቢያ ልማት መምሪያ ዛሬ ተጽፎ በተሰራጨው ሰልኩላር ደብዳቤ መሰረት ከጥር 30 ጀምሮ ሁሉም የነዳጅ ማደያ ያለባቸው ከተሞች ከጥር 30/2017 ጀምሮ ነዳጅ በኩፖን እንዲሸጥ ትዕዛዝ አስተላልፏል።

ቢሮው የነዳጅ ምርት እጥረቱ ከጊዜ ወደ ጊዜ ከመሻሻል ይልቅ እየተባባሰ ከመምጣቱ ጋር ተያይዞ በተለይ የባለ ሁለት እግር ሞተሮች በየቀኑ ተመላልሶ መቅዳት ለኮንትሮባንድ ሽያጭ ከፍተኛ አስተዋጽኦ በማድረግ ለችግሩ መባባስ ዋነኛ መንስኤዎች መሆናቸውን ከተደረገው ክትትል ለማረጋገጥ ተችሏል ብሏል።

በአንዳንድ የክልሉ ከተሞች የኩፖን ሥርዓት በመዘርጋቱ ሥርጭት ላይ ያለውን የቤንዚን ምርት በአግባቡ ማሰራጨት መቻሉንና ለክትትልም ምቹ ሁኔታ መፈጠሩን ማስተዋሉን ነው በደብዳቤው የጠቀሰው።

በመሆኑም የነዳጅ ማደያ ያለባቸው ከተሞች ከጥር 30/2017 ዓ.ም ጀምሮ የትኛውም ተሽከርካሪ በኩፖን ብቻ እንዲስተናገድ እና ታርጋ የሌላቸው ተሽከርካሪዎች ሀጋዊ የተሽከርካሪ ሠሌዳ እስኪያወጡ ድረስ የግልም ሆነ የመንግስት ተሽከርካሪዎች እንዳይስተናገዱ ሲል በደብዳቤው ጠቅሷል።

ቢሮው አክሎም "ህገ-ወጥ የሆኑትን ማክሰም አስፈላጊ በመሆኑ ተግባራዊ እንዲደረግ እየገለጽን የነዳጅ ምርት ሽያጭም ቢሆን በኤሌክትሮኒክስ ቴሌ ብር እና ሲቢኢ ብር/ የመገበያያ መንገዶች ብቻ እንዲፈጸም በጥብቅ እናሳስባለን፡፡" ሲል በሰርኩላር ደብዳቤው አስታውቋል።

ከዚህ ቀደም ወላይታ ሶዶ ከተማ፤ ወራቤ ከተማ፤ ዲላ ከተማ በዚሁ መልኩ ሲጠቀሙ ቆይተዋል። በክልሉ ይተግበር ስለተባለው የኩፖን አሰራር ዙሪያ የሚመለከታቸውን አካላት አናግረን ተጨማሪ መረጃዎችን የምናደርሳችሁ ይሆናል።

💬 ለመሆኑ የኩፖን አሰራር ተግባራዊ በተደረገባቸው ከተሞች ምን ለውጥ ነበረው በአከባቢው ያላችሁ የቲክቫህ ቤተሰቦች ተሞክሯችሁን አካፍሉን

@tikvahethmagazine

BY TIKVAH-MAGAZINE






Share with your friend now:
tgoop.com/tikvahethmagazine/23937

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

Earlier, crypto enthusiasts had created a self-described “meme app” dubbed “gm” app wherein users would greet each other with “gm” or “good morning” messages. However, in September 2021, the gm app was down after a hacker reportedly gained access to the user data. During the meeting with TSE Minister Edson Fachin, Perekopsky also mentioned the TSE channel on the platform as one of the firm's key success stories. Launched as part of the company's commitments to tackle the spread of fake news in Brazil, the verified channel has attracted more than 184,000 members in less than a month. Ng, who had pleaded not guilty to all charges, had been detained for more than 20 months. His channel was said to have contained around 120 messages and photos that incited others to vandalise pro-government shops and commit criminal damage targeting police stations. Hui said the messages, which included urging the disruption of airport operations, were attempts to incite followers to make use of poisonous, corrosive or flammable substances to vandalize police vehicles, and also called on others to make weapons to harm police. The Channel name and bio must be no more than 255 characters long
from us


Telegram TIKVAH-MAGAZINE
FROM American