tgoop.com/tikvahethmagazine/24013
Last Update:
ልጆችን ሥርዐት ስናስተምር መከተል የሚገቡን መርሆች
1፡ ተከታታይነት /be consistent/ እና ግልጽነት ሊኖር ይገባል
ልጆችን ሥርዐት ለማስያዝ ተከታታይነትና ግልጽነት ሁለት ቁልፍ ነገሮች ናቸው። ህጻናት በቤት አከባቢ ሊከውኑት የሚችሉትን ተግባር መስጠት ተገቢ ሲሆን ህጻናት የተጫወቱበትን እቃ እንዲሰበስቡ ማስተማር ተገቢ ነው።
በመጀመሪያው የተግባር ወቅት አብሮ መሳተፍ ያስፈልጋል፣ ቦኃላ ላይ ለነሱም ይቀላቸዋል። ልጆች ሃላፊነታቸውንንና ገደባቸውን እንዲሁም ወላጅ ከነሱ የሚጠብቀውን ነገር በደንብ ማሳወቅ አለብን።
2፡ ጽኑና የማያወላዉል አፍቃሪ መሆን አለብን
በሚያጠፉበትና ትዛዝን በማይቀበሉበት ጊዜ ጽኑና ሚዛናዊ መሆን፤ ቅጣታችንንም በፍቅር ማድረግ ይገባናል። በምንቀጣቸው ጊዜ እንዲታረሙና እንዲስተካከሉ እንደሆነ በመጀመሪያ ላይገነዘቡ ይችላሉ፣ ነገር ግን እንደምንወዳቸው ና እንዲታረሙ እንደሆነ ልንገልጽላቸው ያስፈልጋል። የምንወስዳቸዉ እርምጃዎች ተደጋጋሚና ጽኑ ከሆኑ ልጆች ትዛዝን ይከተላሉ።
3፡ አካላዊ ቅጣትን ማስወገድ
አካላዊ ቅጣት ብዙን ጊዜ ክርክርን ያስነሳል፣ ትክክልም ነው፣ ጥናቶች እንደሚጠቁሙት የበዛ አካላዊ ቅጣት በልጆች አካል ላይ ጉዳት ከማድረሱም በላይ ልጆች በማኅረሰቡ ላይ እንዲያምጹ ሊደርጋቸው ይችላል። ከአካላዊ ቅጣት ይልቅ ሌሎች የቅጣት አይነቶችን ብንተገብር ይመረጣል።
[ @BikuZega ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር የቀረበ ]
@tikvahethmagazine
BY TIKVAH-MAGAZINE
![](https://photo2.tgoop.com/u/cdn4.cdn-telegram.org/file/PINVXmwm80IjIcdIkTSP4dj4aWqyouMl599QEWoiBDctqLX05vOI2St1ASfkJNfKON57fE_pU89BfNE1mC1NBTppaPzSiKIPWf9Y8cfEybt7w32gK0CVeFCbDFxxLrkXXmuaZkM_mSqGgLLc6PjF-6GvXJsctFmmMTGK4svxg28Z2fC7UCTc9Btqxwn2ZWB4LCPSBBWzD4Bm7KDDoz-f-pV6_WTU_JSQaj8XVe8rKZheNV95Z5sd46mQMHv98sPHVzegB93n2KaChIwb3wbNE-LoYrHJK-DDyTWnoxl22-draAOe5KneHmQytOswDb9lOxq1mYgzKOZn0K4HeM2njw.jpg)
Share with your friend now:
tgoop.com/tikvahethmagazine/24013