TIKVAHETHMAGAZINE Telegram 24020
TIKVAH-MAGAZINE
Photo
"ከ10 ሄክታር በላይ የፓርኩ ክፍል በቃጠሎ ወድሟል" የማዜ ብሔራዊ ፓርክ

ትናት ማምሻውን በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋሞ ዞን ቁጫ ወረዳ የማዜ ብሔራዊ ፓርክ አከባቢ የተነሳዉ እሳት ሌሊቱን ሙሉ ሳይጠፋ ማደሩንና በፓርኩ ላይ ከፍተኛ ጉዳት ማድረሱን የማዜ ብሔራዊ ፓርክ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ መስፍን ጬማ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

በአከባቢው ከፓርኩ አቅራቢያ ከሚገኝ ሞርካ ቀበሌ አንድ አርሶ አደር የማሳ ዝግጅት በሚያደርግበት ወቅት እያካሄደ ከነበረዉ ቃጠሎ የወጣ እሳት ምሽት 12 ሰዓት አከባቢ በፓርኩ ዙሪያ የሚገኝን 5  ሄክታር ቦታ ካወደመ በኋላ ከሌሊቱ 8 ሰዓት ገደማ የፓርኩን ክፍል ማዉደም መጀመሩን የገለፁት አቶ መስፍን ከወቅቱ ነፋሻማነትና የሰዓቱ ምቹ አለመሆን የእሳት ማጥፋትን ስራ ፈትኖት እንደነበር አስታዉቀዋል።

የእሳት ማጥፋት ስራዉ ከዛሬ ማለዳ ከ12 ሰዓት ጀምሮ በተደራጀ መልኩ በአከባቢው ነዋሪዎች፣በፀጥታ መዋቅርና በእሳት አደጋ ብርጌድ ርብርብ ሲደረግበት ቆይቶ ከፓርኩ ዉጪ 5 ሄክታር ከፓርኩ ክፍል ደግም 10 ሄክታር በላይ ካወደመ በኋላ ረፋዱ አራት አከባቢ በቁጥጥር ስር መዋሉን አቶ መስፍን አስታዉቀዋል።

አቶ መስፍን አክለዉም እስካሁን በተደረገዉ ማጣራት ከፓርኩ ስነ ምህደር ዉድመት ባሻገር በአራዊቱ ላይ ጉዳት አለመድረሱን ገልፀዉ በእሳት ማጥፋቱ ስራ ከተሳተፉት የአከባቢዉ ነዋሪዎች ፣የፀጥታ መዋቅር አባላትና በሃይለማርያምና ሮማን ፋዉንዴሽን የተቋቋመው የእሳት አደጋ ብርጌድ በተጨማሪ ከወላይታ ወደ ሳዉላ ይንቀሳቀሱ የነበሩ የግልና ትራንስፖርት ተሽከርካሪዎች ሕዝቡን በማጓጓዝ ያደረጉት አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑን ጠቁመው ምስጋና አቅርበዋል።

የማዜ ብሔራዊ ፓርክ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋሞ እና ጎፋ ዞኖች መካከል ቁጫ ወረዳ አከባቢ የሚገኝ ሲሆን ከአዲስ አበባ 460 ፣ከሐዋሳ 235 እንዲሁም ከጋሞ ዞን አርባምንጭ ከተማ 196 ኪ.ሜ ርቀት ላይ ይገኛል።

የፓርኩ አጠቃላይ ስፋት 220 ስኩዌር ኪሎ ሜትር የሚሸፍን ሲሆንበሀገራችን በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኘዉ የስዋይኔ ቆርኬ ጨምሮ አንበሳ፣ አቦሸማኔ፣ የቆላና ትልልቆቹ አጋዘኖች፣ አምባራይሌና ከርከሮን ጨምሮ 39 የተለያዩ አጥቢ እንስሳቶች፣ 196 የአዕዋፋት ዝርያዎች እና ከ80 በላይ የእፅዋት አይነቶ እንደሚገኙበት ከማዜ ብሔራዊ ፓርክ ያገኘነዉ መረጃ ያመላክታል።

#TikvahEthiopiaFamilyHawassa

@tikvahethmagazine



tgoop.com/tikvahethmagazine/24020
Create:
Last Update:

"ከ10 ሄክታር በላይ የፓርኩ ክፍል በቃጠሎ ወድሟል" የማዜ ብሔራዊ ፓርክ

ትናት ማምሻውን በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋሞ ዞን ቁጫ ወረዳ የማዜ ብሔራዊ ፓርክ አከባቢ የተነሳዉ እሳት ሌሊቱን ሙሉ ሳይጠፋ ማደሩንና በፓርኩ ላይ ከፍተኛ ጉዳት ማድረሱን የማዜ ብሔራዊ ፓርክ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ መስፍን ጬማ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

በአከባቢው ከፓርኩ አቅራቢያ ከሚገኝ ሞርካ ቀበሌ አንድ አርሶ አደር የማሳ ዝግጅት በሚያደርግበት ወቅት እያካሄደ ከነበረዉ ቃጠሎ የወጣ እሳት ምሽት 12 ሰዓት አከባቢ በፓርኩ ዙሪያ የሚገኝን 5  ሄክታር ቦታ ካወደመ በኋላ ከሌሊቱ 8 ሰዓት ገደማ የፓርኩን ክፍል ማዉደም መጀመሩን የገለፁት አቶ መስፍን ከወቅቱ ነፋሻማነትና የሰዓቱ ምቹ አለመሆን የእሳት ማጥፋትን ስራ ፈትኖት እንደነበር አስታዉቀዋል።

የእሳት ማጥፋት ስራዉ ከዛሬ ማለዳ ከ12 ሰዓት ጀምሮ በተደራጀ መልኩ በአከባቢው ነዋሪዎች፣በፀጥታ መዋቅርና በእሳት አደጋ ብርጌድ ርብርብ ሲደረግበት ቆይቶ ከፓርኩ ዉጪ 5 ሄክታር ከፓርኩ ክፍል ደግም 10 ሄክታር በላይ ካወደመ በኋላ ረፋዱ አራት አከባቢ በቁጥጥር ስር መዋሉን አቶ መስፍን አስታዉቀዋል።

አቶ መስፍን አክለዉም እስካሁን በተደረገዉ ማጣራት ከፓርኩ ስነ ምህደር ዉድመት ባሻገር በአራዊቱ ላይ ጉዳት አለመድረሱን ገልፀዉ በእሳት ማጥፋቱ ስራ ከተሳተፉት የአከባቢዉ ነዋሪዎች ፣የፀጥታ መዋቅር አባላትና በሃይለማርያምና ሮማን ፋዉንዴሽን የተቋቋመው የእሳት አደጋ ብርጌድ በተጨማሪ ከወላይታ ወደ ሳዉላ ይንቀሳቀሱ የነበሩ የግልና ትራንስፖርት ተሽከርካሪዎች ሕዝቡን በማጓጓዝ ያደረጉት አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑን ጠቁመው ምስጋና አቅርበዋል።

የማዜ ብሔራዊ ፓርክ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋሞ እና ጎፋ ዞኖች መካከል ቁጫ ወረዳ አከባቢ የሚገኝ ሲሆን ከአዲስ አበባ 460 ፣ከሐዋሳ 235 እንዲሁም ከጋሞ ዞን አርባምንጭ ከተማ 196 ኪ.ሜ ርቀት ላይ ይገኛል።

የፓርኩ አጠቃላይ ስፋት 220 ስኩዌር ኪሎ ሜትር የሚሸፍን ሲሆንበሀገራችን በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኘዉ የስዋይኔ ቆርኬ ጨምሮ አንበሳ፣ አቦሸማኔ፣ የቆላና ትልልቆቹ አጋዘኖች፣ አምባራይሌና ከርከሮን ጨምሮ 39 የተለያዩ አጥቢ እንስሳቶች፣ 196 የአዕዋፋት ዝርያዎች እና ከ80 በላይ የእፅዋት አይነቶ እንደሚገኙበት ከማዜ ብሔራዊ ፓርክ ያገኘነዉ መረጃ ያመላክታል።

#TikvahEthiopiaFamilyHawassa

@tikvahethmagazine

BY TIKVAH-MAGAZINE









Share with your friend now:
tgoop.com/tikvahethmagazine/24020

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

Just at this time, Bitcoin and the broader crypto market have dropped to new 2022 lows. The Bitcoin price has tanked 10 percent dropping to $20,000. On the other hand, the altcoin space is witnessing even more brutal correction. Bitcoin has dropped nearly 60 percent year-to-date and more than 70 percent since its all-time high in November 2021. Telegram desktop app: In the upper left corner, click the Menu icon (the one with three lines). Select “New Channel” from the drop-down menu. Just as the Bitcoin turmoil continues, crypto traders have taken to Telegram to voice their feelings. Crypto investors can reduce their anxiety about losses by joining the “Bear Market Screaming Therapy Group” on Telegram. Some Telegram Channels content management tips As of Thursday, the SUCK Channel had 34,146 subscribers, with only one message dated August 28, 2020. It was an announcement stating that police had removed all posts on the channel because its content “contravenes the laws of Hong Kong.”
from us


Telegram TIKVAH-MAGAZINE
FROM American