TIKVAHETHMAGAZINE Telegram 24028
የአሜሪካ የጦር ኃይል በሶማሊያ በሚገኘው የISIS ቡድን ላይ የአየር ጥቃት ፈጸመ።

ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በሶማሊያ በሚገኘው የ ISIS እንዲሁም ከሱ ጋር ግንኙነት ባላቸው አሸባሪ ቡድኖች ላይ ባስተላለፉት ወታደራዊ ትዕዛዝ የአየር ጥቃት ተፈጽሟል።

"በዋሻ ውስጥ ተደብቀው ያገኘናቸው እነዚህ ገዳዮች ለአሜሪካ እና ለአጋሮቻችን ስጋት ነበሩ" ሲሉ ፕረዚዳንቱ በትሩዝ ሶሻል ገጻቸው ላይ አስፍረዋል። 

አክለውም፥ "በጥቃቱ አሸባሪዎችን ገድለናል፤ የሚኖሩባቸውን ዋሻዎችም አውድመናል። ይህም ሰላማዊ ዜጎችን ሳይጎዳ የተፈጸመ ነው" ሲሉ ገልጸዋል።

ጥቃቱ የተፈጸመው የተካሄደው በጎሊስ ተራሮች (ሰሜናዊ ሶማሊያ) አካባቢ ሲሆን የተፈጸመውም ጠዋት አከባቢ ነው ተብሏል።

ስማቸው እንዳይገለጽ የፈለጉ የሶማሊያ የፕሬዝዳንት ጽ/ቤት ባለስልጣን ጥቃቱ መፈጸሙን አረጋግጠው፤ የሶማሊያ መንግስት ድርጊቱን እንደሚቀበል ገልጸዋል። “ሶማሊያ የአሸባሪዎች መሸሸጊያ ልትሆን አትችልም” ሲሉም ነው የገለጹት።

የሶማሊያ ፕረዚዳንት ጽ/ቤትም በX ገጹ ጥቃቱ መፈጸሙን ገልጾ ፕሬዚዳንት ሀሰን ሼክ መሐሙድ አሜሪካ ዓለም አቀፍ ሽብርተኝነትን ለመዋጋት የምታደርገውን ጥረት እንደግፋለን ሲል ገልጿል።

የአሜሪካው ፕረዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ፥ "የእኛ ወታደራዊ ኃይል ይህን ጥቃት ከዓመታት በፊት አቅዶት የነበረ ቢሆንም ነገር ግን ባይደን እና አጋሮቹ ፈጥነው እርምጃ አልወሰዱም። እኔ ግን አደረግኩት" ሲሉም ነው የጠቀሱት።

በጹሑፋቸው ላይም ለISIS እና ለሌሎች አሜሪካ ላይ ጥቃት ለሚሰነዝሩ ሰዎች ሁሉ ያለን መልዕክት “እናገኛችኋለን፣ እናም እንገድላችኋለን!” የሚል ነው። ሲሉ ነው የገለጹት።

አሜሪካ በሶማሊያ ለዓመታት በሪፐብሊካን እና በዲሞክራቲክ አስተዳደር ሥር የአየር ጥቃትን ስታደርግ ቆይታለች። ባለፈው ዓመት ከሶማሊያ ጋር በመተባበር በፈጸመችው በአሸባሪዎች ላይ ባነጣጠረው ጥቃትም የቡድኑን ሦስት አባላት መገደላቸውን የአሜሪካ ጦር ኃይል አስታውቆ ነበር።

Credit : Reuters , VOA , 📸 U.S.Africa Command

@tikvahethmagazine



tgoop.com/tikvahethmagazine/24028
Create:
Last Update:

የአሜሪካ የጦር ኃይል በሶማሊያ በሚገኘው የISIS ቡድን ላይ የአየር ጥቃት ፈጸመ።

ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በሶማሊያ በሚገኘው የ ISIS እንዲሁም ከሱ ጋር ግንኙነት ባላቸው አሸባሪ ቡድኖች ላይ ባስተላለፉት ወታደራዊ ትዕዛዝ የአየር ጥቃት ተፈጽሟል።

"በዋሻ ውስጥ ተደብቀው ያገኘናቸው እነዚህ ገዳዮች ለአሜሪካ እና ለአጋሮቻችን ስጋት ነበሩ" ሲሉ ፕረዚዳንቱ በትሩዝ ሶሻል ገጻቸው ላይ አስፍረዋል። 

አክለውም፥ "በጥቃቱ አሸባሪዎችን ገድለናል፤ የሚኖሩባቸውን ዋሻዎችም አውድመናል። ይህም ሰላማዊ ዜጎችን ሳይጎዳ የተፈጸመ ነው" ሲሉ ገልጸዋል።

ጥቃቱ የተፈጸመው የተካሄደው በጎሊስ ተራሮች (ሰሜናዊ ሶማሊያ) አካባቢ ሲሆን የተፈጸመውም ጠዋት አከባቢ ነው ተብሏል።

ስማቸው እንዳይገለጽ የፈለጉ የሶማሊያ የፕሬዝዳንት ጽ/ቤት ባለስልጣን ጥቃቱ መፈጸሙን አረጋግጠው፤ የሶማሊያ መንግስት ድርጊቱን እንደሚቀበል ገልጸዋል። “ሶማሊያ የአሸባሪዎች መሸሸጊያ ልትሆን አትችልም” ሲሉም ነው የገለጹት።

የሶማሊያ ፕረዚዳንት ጽ/ቤትም በX ገጹ ጥቃቱ መፈጸሙን ገልጾ ፕሬዚዳንት ሀሰን ሼክ መሐሙድ አሜሪካ ዓለም አቀፍ ሽብርተኝነትን ለመዋጋት የምታደርገውን ጥረት እንደግፋለን ሲል ገልጿል።

የአሜሪካው ፕረዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ፥ "የእኛ ወታደራዊ ኃይል ይህን ጥቃት ከዓመታት በፊት አቅዶት የነበረ ቢሆንም ነገር ግን ባይደን እና አጋሮቹ ፈጥነው እርምጃ አልወሰዱም። እኔ ግን አደረግኩት" ሲሉም ነው የጠቀሱት።

በጹሑፋቸው ላይም ለISIS እና ለሌሎች አሜሪካ ላይ ጥቃት ለሚሰነዝሩ ሰዎች ሁሉ ያለን መልዕክት “እናገኛችኋለን፣ እናም እንገድላችኋለን!” የሚል ነው። ሲሉ ነው የገለጹት።

አሜሪካ በሶማሊያ ለዓመታት በሪፐብሊካን እና በዲሞክራቲክ አስተዳደር ሥር የአየር ጥቃትን ስታደርግ ቆይታለች። ባለፈው ዓመት ከሶማሊያ ጋር በመተባበር በፈጸመችው በአሸባሪዎች ላይ ባነጣጠረው ጥቃትም የቡድኑን ሦስት አባላት መገደላቸውን የአሜሪካ ጦር ኃይል አስታውቆ ነበር።

Credit : Reuters , VOA , 📸 U.S.Africa Command

@tikvahethmagazine

BY TIKVAH-MAGAZINE







Share with your friend now:
tgoop.com/tikvahethmagazine/24028

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

In handing down the sentence yesterday, deputy judge Peter Hui Shiu-keung of the district court said that even if Ng did not post the messages, he cannot shirk responsibility as the owner and administrator of such a big group for allowing these messages that incite illegal behaviors to exist. Informative In the “Bear Market Screaming Therapy Group” on Telegram, members are only allowed to post voice notes of themselves screaming. Anything else will result in an instant ban from the group, which currently has about 75 members. Among the requests, the Brazilian electoral Court wanted to know if they could obtain data on the origins of malicious content posted on the platform. According to the TSE, this would enable the authorities to track false content and identify the user responsible for publishing it in the first place. Read now
from us


Telegram TIKVAH-MAGAZINE
FROM American