የአሜሪካ የጦር ኃይል በሶማሊያ በሚገኘው የISIS ቡድን ላይ የአየር ጥቃት ፈጸመ።
ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በሶማሊያ በሚገኘው የ ISIS እንዲሁም ከሱ ጋር ግንኙነት ባላቸው አሸባሪ ቡድኖች ላይ ባስተላለፉት ወታደራዊ ትዕዛዝ የአየር ጥቃት ተፈጽሟል።
"በዋሻ ውስጥ ተደብቀው ያገኘናቸው እነዚህ ገዳዮች ለአሜሪካ እና ለአጋሮቻችን ስጋት ነበሩ" ሲሉ ፕረዚዳንቱ በትሩዝ ሶሻል ገጻቸው ላይ አስፍረዋል።
አክለውም፥ "በጥቃቱ አሸባሪዎችን ገድለናል፤ የሚኖሩባቸውን ዋሻዎችም አውድመናል። ይህም ሰላማዊ ዜጎችን ሳይጎዳ የተፈጸመ ነው" ሲሉ ገልጸዋል።
ጥቃቱ የተፈጸመው የተካሄደው በጎሊስ ተራሮች (ሰሜናዊ ሶማሊያ) አካባቢ ሲሆን የተፈጸመውም ጠዋት አከባቢ ነው ተብሏል።
ስማቸው እንዳይገለጽ የፈለጉ የሶማሊያ የፕሬዝዳንት ጽ/ቤት ባለስልጣን ጥቃቱ መፈጸሙን አረጋግጠው፤ የሶማሊያ መንግስት ድርጊቱን እንደሚቀበል ገልጸዋል። “ሶማሊያ የአሸባሪዎች መሸሸጊያ ልትሆን አትችልም” ሲሉም ነው የገለጹት።
የሶማሊያ ፕረዚዳንት ጽ/ቤትም በX ገጹ ጥቃቱ መፈጸሙን ገልጾ ፕሬዚዳንት ሀሰን ሼክ መሐሙድ አሜሪካ ዓለም አቀፍ ሽብርተኝነትን ለመዋጋት የምታደርገውን ጥረት እንደግፋለን ሲል ገልጿል።
የአሜሪካው ፕረዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ፥ "የእኛ ወታደራዊ ኃይል ይህን ጥቃት ከዓመታት በፊት አቅዶት የነበረ ቢሆንም ነገር ግን ባይደን እና አጋሮቹ ፈጥነው እርምጃ አልወሰዱም። እኔ ግን አደረግኩት" ሲሉም ነው የጠቀሱት።
በጹሑፋቸው ላይም ለISIS እና ለሌሎች አሜሪካ ላይ ጥቃት ለሚሰነዝሩ ሰዎች ሁሉ ያለን መልዕክት “እናገኛችኋለን፣ እናም እንገድላችኋለን!” የሚል ነው። ሲሉ ነው የገለጹት።
አሜሪካ በሶማሊያ ለዓመታት በሪፐብሊካን እና በዲሞክራቲክ አስተዳደር ሥር የአየር ጥቃትን ስታደርግ ቆይታለች። ባለፈው ዓመት ከሶማሊያ ጋር በመተባበር በፈጸመችው በአሸባሪዎች ላይ ባነጣጠረው ጥቃትም የቡድኑን ሦስት አባላት መገደላቸውን የአሜሪካ ጦር ኃይል አስታውቆ ነበር።
Credit : Reuters , VOA , 📸 U.S.Africa Command
@tikvahethmagazine
ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በሶማሊያ በሚገኘው የ ISIS እንዲሁም ከሱ ጋር ግንኙነት ባላቸው አሸባሪ ቡድኖች ላይ ባስተላለፉት ወታደራዊ ትዕዛዝ የአየር ጥቃት ተፈጽሟል።
"በዋሻ ውስጥ ተደብቀው ያገኘናቸው እነዚህ ገዳዮች ለአሜሪካ እና ለአጋሮቻችን ስጋት ነበሩ" ሲሉ ፕረዚዳንቱ በትሩዝ ሶሻል ገጻቸው ላይ አስፍረዋል።
አክለውም፥ "በጥቃቱ አሸባሪዎችን ገድለናል፤ የሚኖሩባቸውን ዋሻዎችም አውድመናል። ይህም ሰላማዊ ዜጎችን ሳይጎዳ የተፈጸመ ነው" ሲሉ ገልጸዋል።
ጥቃቱ የተፈጸመው የተካሄደው በጎሊስ ተራሮች (ሰሜናዊ ሶማሊያ) አካባቢ ሲሆን የተፈጸመውም ጠዋት አከባቢ ነው ተብሏል።
ስማቸው እንዳይገለጽ የፈለጉ የሶማሊያ የፕሬዝዳንት ጽ/ቤት ባለስልጣን ጥቃቱ መፈጸሙን አረጋግጠው፤ የሶማሊያ መንግስት ድርጊቱን እንደሚቀበል ገልጸዋል። “ሶማሊያ የአሸባሪዎች መሸሸጊያ ልትሆን አትችልም” ሲሉም ነው የገለጹት።
የሶማሊያ ፕረዚዳንት ጽ/ቤትም በX ገጹ ጥቃቱ መፈጸሙን ገልጾ ፕሬዚዳንት ሀሰን ሼክ መሐሙድ አሜሪካ ዓለም አቀፍ ሽብርተኝነትን ለመዋጋት የምታደርገውን ጥረት እንደግፋለን ሲል ገልጿል።
የአሜሪካው ፕረዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ፥ "የእኛ ወታደራዊ ኃይል ይህን ጥቃት ከዓመታት በፊት አቅዶት የነበረ ቢሆንም ነገር ግን ባይደን እና አጋሮቹ ፈጥነው እርምጃ አልወሰዱም። እኔ ግን አደረግኩት" ሲሉም ነው የጠቀሱት።
በጹሑፋቸው ላይም ለISIS እና ለሌሎች አሜሪካ ላይ ጥቃት ለሚሰነዝሩ ሰዎች ሁሉ ያለን መልዕክት “እናገኛችኋለን፣ እናም እንገድላችኋለን!” የሚል ነው። ሲሉ ነው የገለጹት።
አሜሪካ በሶማሊያ ለዓመታት በሪፐብሊካን እና በዲሞክራቲክ አስተዳደር ሥር የአየር ጥቃትን ስታደርግ ቆይታለች። ባለፈው ዓመት ከሶማሊያ ጋር በመተባበር በፈጸመችው በአሸባሪዎች ላይ ባነጣጠረው ጥቃትም የቡድኑን ሦስት አባላት መገደላቸውን የአሜሪካ ጦር ኃይል አስታውቆ ነበር።
Credit : Reuters , VOA , 📸 U.S.Africa Command
@tikvahethmagazine
tgoop.com/tikvahethmagazine/24028
Create:
Last Update:
Last Update:
የአሜሪካ የጦር ኃይል በሶማሊያ በሚገኘው የISIS ቡድን ላይ የአየር ጥቃት ፈጸመ።
ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በሶማሊያ በሚገኘው የ ISIS እንዲሁም ከሱ ጋር ግንኙነት ባላቸው አሸባሪ ቡድኖች ላይ ባስተላለፉት ወታደራዊ ትዕዛዝ የአየር ጥቃት ተፈጽሟል።
"በዋሻ ውስጥ ተደብቀው ያገኘናቸው እነዚህ ገዳዮች ለአሜሪካ እና ለአጋሮቻችን ስጋት ነበሩ" ሲሉ ፕረዚዳንቱ በትሩዝ ሶሻል ገጻቸው ላይ አስፍረዋል።
አክለውም፥ "በጥቃቱ አሸባሪዎችን ገድለናል፤ የሚኖሩባቸውን ዋሻዎችም አውድመናል። ይህም ሰላማዊ ዜጎችን ሳይጎዳ የተፈጸመ ነው" ሲሉ ገልጸዋል።
ጥቃቱ የተፈጸመው የተካሄደው በጎሊስ ተራሮች (ሰሜናዊ ሶማሊያ) አካባቢ ሲሆን የተፈጸመውም ጠዋት አከባቢ ነው ተብሏል።
ስማቸው እንዳይገለጽ የፈለጉ የሶማሊያ የፕሬዝዳንት ጽ/ቤት ባለስልጣን ጥቃቱ መፈጸሙን አረጋግጠው፤ የሶማሊያ መንግስት ድርጊቱን እንደሚቀበል ገልጸዋል። “ሶማሊያ የአሸባሪዎች መሸሸጊያ ልትሆን አትችልም” ሲሉም ነው የገለጹት።
የሶማሊያ ፕረዚዳንት ጽ/ቤትም በX ገጹ ጥቃቱ መፈጸሙን ገልጾ ፕሬዚዳንት ሀሰን ሼክ መሐሙድ አሜሪካ ዓለም አቀፍ ሽብርተኝነትን ለመዋጋት የምታደርገውን ጥረት እንደግፋለን ሲል ገልጿል።
የአሜሪካው ፕረዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ፥ "የእኛ ወታደራዊ ኃይል ይህን ጥቃት ከዓመታት በፊት አቅዶት የነበረ ቢሆንም ነገር ግን ባይደን እና አጋሮቹ ፈጥነው እርምጃ አልወሰዱም። እኔ ግን አደረግኩት" ሲሉም ነው የጠቀሱት።
በጹሑፋቸው ላይም ለISIS እና ለሌሎች አሜሪካ ላይ ጥቃት ለሚሰነዝሩ ሰዎች ሁሉ ያለን መልዕክት “እናገኛችኋለን፣ እናም እንገድላችኋለን!” የሚል ነው። ሲሉ ነው የገለጹት።
አሜሪካ በሶማሊያ ለዓመታት በሪፐብሊካን እና በዲሞክራቲክ አስተዳደር ሥር የአየር ጥቃትን ስታደርግ ቆይታለች። ባለፈው ዓመት ከሶማሊያ ጋር በመተባበር በፈጸመችው በአሸባሪዎች ላይ ባነጣጠረው ጥቃትም የቡድኑን ሦስት አባላት መገደላቸውን የአሜሪካ ጦር ኃይል አስታውቆ ነበር።
Credit : Reuters , VOA , 📸 U.S.Africa Command
@tikvahethmagazine
ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በሶማሊያ በሚገኘው የ ISIS እንዲሁም ከሱ ጋር ግንኙነት ባላቸው አሸባሪ ቡድኖች ላይ ባስተላለፉት ወታደራዊ ትዕዛዝ የአየር ጥቃት ተፈጽሟል።
"በዋሻ ውስጥ ተደብቀው ያገኘናቸው እነዚህ ገዳዮች ለአሜሪካ እና ለአጋሮቻችን ስጋት ነበሩ" ሲሉ ፕረዚዳንቱ በትሩዝ ሶሻል ገጻቸው ላይ አስፍረዋል።
አክለውም፥ "በጥቃቱ አሸባሪዎችን ገድለናል፤ የሚኖሩባቸውን ዋሻዎችም አውድመናል። ይህም ሰላማዊ ዜጎችን ሳይጎዳ የተፈጸመ ነው" ሲሉ ገልጸዋል።
ጥቃቱ የተፈጸመው የተካሄደው በጎሊስ ተራሮች (ሰሜናዊ ሶማሊያ) አካባቢ ሲሆን የተፈጸመውም ጠዋት አከባቢ ነው ተብሏል።
ስማቸው እንዳይገለጽ የፈለጉ የሶማሊያ የፕሬዝዳንት ጽ/ቤት ባለስልጣን ጥቃቱ መፈጸሙን አረጋግጠው፤ የሶማሊያ መንግስት ድርጊቱን እንደሚቀበል ገልጸዋል። “ሶማሊያ የአሸባሪዎች መሸሸጊያ ልትሆን አትችልም” ሲሉም ነው የገለጹት።
የሶማሊያ ፕረዚዳንት ጽ/ቤትም በX ገጹ ጥቃቱ መፈጸሙን ገልጾ ፕሬዚዳንት ሀሰን ሼክ መሐሙድ አሜሪካ ዓለም አቀፍ ሽብርተኝነትን ለመዋጋት የምታደርገውን ጥረት እንደግፋለን ሲል ገልጿል።
የአሜሪካው ፕረዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ፥ "የእኛ ወታደራዊ ኃይል ይህን ጥቃት ከዓመታት በፊት አቅዶት የነበረ ቢሆንም ነገር ግን ባይደን እና አጋሮቹ ፈጥነው እርምጃ አልወሰዱም። እኔ ግን አደረግኩት" ሲሉም ነው የጠቀሱት።
በጹሑፋቸው ላይም ለISIS እና ለሌሎች አሜሪካ ላይ ጥቃት ለሚሰነዝሩ ሰዎች ሁሉ ያለን መልዕክት “እናገኛችኋለን፣ እናም እንገድላችኋለን!” የሚል ነው። ሲሉ ነው የገለጹት።
አሜሪካ በሶማሊያ ለዓመታት በሪፐብሊካን እና በዲሞክራቲክ አስተዳደር ሥር የአየር ጥቃትን ስታደርግ ቆይታለች። ባለፈው ዓመት ከሶማሊያ ጋር በመተባበር በፈጸመችው በአሸባሪዎች ላይ ባነጣጠረው ጥቃትም የቡድኑን ሦስት አባላት መገደላቸውን የአሜሪካ ጦር ኃይል አስታውቆ ነበር።
Credit : Reuters , VOA , 📸 U.S.Africa Command
@tikvahethmagazine
BY TIKVAH-MAGAZINE
Share with your friend now:
tgoop.com/tikvahethmagazine/24028