tgoop.com/tmhrtegeeze/10028
Last Update:
ካህኑ ለምን በእጁ ያሳልሙናል ?
የካህኑን እጅ መሳለም አንዳንድ ሰዎች ካህኑ ለምን በእጁ ያሳልመናል ይላሉ። ነገር ግን ሚስጢሩ ይህ ነው
የካህኑ እጅ እኮ እሳታዊያን የሆኑ መላእክት መንካት
የማይቻላቸውን ቅዱስ ሥጋውን ክብር ደሙን የዳሰሱበት
ነው።
በቅዳሴ ላይ ቅዱስ ሥጋውን መንካት የሚችለው ዋናው ካህን ብቻ ነው ፤ ሁለተኛው ካህን እንኳን መንካት አይችልም።
ቅዱስ ሥጋውን ክብር ደሙን የዳሰሰበት ስለሆነም ካህኑ በእጁ ያሳልመናል እኛም የተቀደሰውን የጌታ ስጋና ደም
የዳሰሱበት እጅ እየተሳለምን አሜን አሜን አሜን እንላለን።
ድንቅ መለኮታዊ ሚስጥር ማለት
እንዲህ ነው
አንሥኡ እደዊክሙ ቀሳዉስ
ዲያቆኑ ይህን በሚልበት ጊዜ ንፍቀ ካህኑ ማሕፈዱን
ከጻሕሉ ላይ ያነሳል ፤ ይህም የጌታ መላአክ የመቃብሩን
ድንጋይ የማከባለሉ ምሳሌ ነው።ከዚህ በኋላ ጌታችን
በምሴተ ሐሙስ ሕብስቱን እንደያዘው ዋናዉ ካህንም
ሕብስቱን ከፍ አድርጎ ይይዘዋል ፤ ይህም የጌታ ትንሳኤ ምሳሌ ነው።
እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ
በእግዚኦታ ላይ ካህኑ ሕብስቱን ይበልጥ ከፍ አድርጎ
ይይዘዋል ይህም የዕርገቱ ምሳሌ ነው።ከካህኑ ጋር ሆነን
41 ግዜ እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ እንላለን ፤ ይህም አርባው እግዚኦታ አይሁድ ጌታችንን 40 ግዜ እንገርፋለን ብለው እያዛቡ ብዙ ጊዜ የመግረፋቸው ምሳሌ ሲሆን በመጨረሻ ካህኑ ብቻውን የሚላት እግዚኦታ ደግሞ የአዳምና የሔዋን የንስሃ ምሳሌ ነው። 12 ግዜ እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ ስንል ደግሞ ስለስምህ ብለህ ይቅር በለን ነው። አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ የሚለውን እያንዳንዱን ፊደል ስንቆጥር 12 ይሆናል!!! እንዲሁም 12 ጊዜ በእንተ እግዚትነ ማርያም መሐረነ ክርስቶስ ስንልም ደግሞ ስለእናትህ ብለህ ማረን ማለታችን ሲሆን ቅድስት ድንግል ማርያም የሚለውን እያንዳንዱን ፊደል ስንቆጥር 12 ይሆናልና
ወንጌል
የመጀመሪያዉ መልዕክት ሲነበብ ዲያቆኑ ፊቱን ወደ ምዕራብ አዙሮ ያነባል፡ ሁለተኛው ዲያቆን ፊቱን ወደ ሴሜን አዙሮ ያነባል ፡ ንፍቀ ካህኑ ወደ ደቡብ ዙሮ ያነባል የሐዋርያት ሥራ ሲያነብ ዋናው ካህን ደግሞ ወደ ምስራቅ ዙሮ ወንጌል ያነባል ፤ ይህም ግሩም የሆነ ምሳሌ አለው አንድም ወንጌል በአራቱም አቅጣጫ መስበኩን ለመግለጽ ነው አንድም ገነትን የሚጠጡ 4 ወንዞች አሉ ኤፍራጠስ ጤግሮስ ጊዮን (አባይ) እና ፊሶን ናቸው። ገነትን አጠጥተው ለምለም እንደሚያደርጓት ጌታችንም የተጠማ ቢኖር የህይወት ውሃ በነፃ ይጠጣና ይርካ እንዳለው ወንጌልም እንዲሁ ያለመልማል ሲሉ ነው።
ቤተክርስቲያን ከጣራዋ እስከ መሬቷ ሁሉም ስርዓቷ
ያስተምራል ፤ ባህረ ጥበብ ቤተክርስቲያን እየተናገረች
ታስተምራለች ሳትናገርም ዝም ብላ ታስተምራለች!!!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ወለ ወላዲቱ ድንግል
ወለ መስቀሉ ክብር ይቆየን
https://www.tgoop.com/sratebetkrstyane
BY ✝️(ትምህርተ ግዕዝ)✝️
Share with your friend now:
tgoop.com/tmhrtegeeze/10028