TMHRTEGEEZE Telegram 10228
●       #የግዝት_በዓላት (#የማይሰገድባቸው_ጊዜያት)

     የሚሰገድባቸው ጊዜያት እንዳሉት ሁሉ የማይሰገድባቸው ጊዜያትም አሉ። የግዝት በዓላት 5 ሲሆኑ #የወልድ_በዓል፣ #የእመቤታችን_በዓል፣ #የቅዱስ_ሚካኤል በዓል፣ #ቀዳሚት_ሰንበትና_እሑድ_ሰንበት ናቸው። ከነዚህ በተጨማሪ #ከቁርባን በኋላና የበዓለ #ሐምሳ ወራትም የማይሰገድባቸው ጊዜያት ናቸው። እነዚህ ስግደት የተገዘተባቸው ጊዜያት የሚከተሉት ናቸው።
         1ኛ       #በዕለተ_እሑድ

ከአልቦ ነገር ወይም ከምንም (ex- nihilo - from nothingness) ሁሉ ክርስቶስ ዳግም ሲመጣ ጠፍቶ ወደ ምንምነት ሲቀየር ከማይጠፉ ከአምስቱ ፍጥረታት አንዷ ሰንበት ናት። ጌታ የተነሣባት ፣ ዳግምም የሚመጣባት ዕለት ናት። በዚህና በሌሎች ምክንያቶችም ሰንበተ ክርስቲያን እሑድ በዓል ነች። ስለዚህ በዕለተ እሑድ መስገድ የተከለከለ ነው።
            2ኛ     #በዕለተ_ቅዳሜ

    ሌላው ከዕለታት መካከል ቅዳሜ የግዝት በዓል ተብሎ የተመረጠበት ምክንያት የሁሉ ባለቤት የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር ዓለማትን ሁሉ በስድስት ቀናት ውስጥ ፈጥሮ ከፈጸመ በኋላ በሰባተኛው ቀን አረፈ። ይህችንም ቀን ቀደሳት ለሰው ልጆችም በዓል አድርጎ ሰጠን። “በሰንበትም እንደ ትእዛዙ ዐረፉ።” ሉቃ 23፥56
3ኛ            #በጌታችን_በዓላት

    ፍትሐ ነገሥቱ “በእሑድና በተከበሩት በዓላት ቀን ስግደት አይገባም፤ እነዚህ የደስታ ቀኖች ናቸውና” (ፍት.መን. አን. 19 ቁ. 715) ካለ በኋላ “የተከበሩት በዓላት” ያላቸው የትኞቹን እንደሆነ ሲዘረዝር ትስብእት/ጽንሰት ፣ ልደት ፣ ጥምቀት ፣ ሆሣዕና ፣ ትንሣኤ ፣ ዕርገት ፣ በዓለ ሃምሳ ፣ ደብረ ታቦር በማለት ከጌታ ዘጠኝ ዐበይት በዓላት 8ቱን ይገልፃል። ሳይገለፅ የቀረው ስቅለት ነው፤ ያልተገለፀበትም ምክንያት በስቅለት ስግደት ስለማይከለከል ነው። ስለዚህ ከስቅለት በቀር በጌታ ዐበይት በዓላት (በተቀሩት በ8ቱ) ስግደት የተከለከለ ነው።
4ኛ.            #በእመቤታችን_በዓላት

በፍት. መን. አን. 14 ቁ. 536-537 ድረስ በጌታ በዓላት መስገድ እንደተከለከለው ሁሉ በእመቤታችን በዓላትም መከልከሉን ይጠቁመናል። የወልድ በዓልን እንደምናከብረው የእመቤታችንንም በዓል በ21 አስበን አንሰግድም። ስለዚህ ወር በገባ በ21 ሁሌም የግዝት በዓል ነው፤ አይሰገድበትም።

5ኛ.           #በቅዱስ_ሚካኤል_በዓል

የቅዱስ ሚካኤል በዓል ከሌሎች የመላእክት በዓላት ተለይቶ መከበሩ ለምንድነው ቢሉ

“የቅዱስ ሚካኤል በዓል መላእክትን ወክሎ ወርኃዊ ሆኖ እንዲከበር ታዟል” (በዓላት ፣ ዲ.ን. ብርሃኑ አድማስ ፣ ገጽ 124)። ስለዚህ ቤተ ክርስቲያን በ12 እንዳይሰገድና እንደ ታላላቅ በዓላት በደስታ እንዲከበር ሥርዐትን ሠርታለች።
6ኛ.          #ሥጋና_ደሙን_ከተቀበሉ_በኋላ

የሥርዐት ምንጫችን የሆነው ፍትሐ ነገሥት አሁንም በዚህ ዙሪያ እንዲህ ብሏል፦ “መስገድን የሚተዉባቸው የታወቁ በዓላት እነዚህ ናቸው… ሥጋውንና ደሙን ከተቀበሉ በኋላ” ይላል። ፍት. መን. አን. 14 ቁ. 536- 537። ሥጋውንና ደሙን ከተቀበልን በኋላ ከሚሰገድለት እንጂ ከማይሰግደው ጋር አንድ መሆናችንን ለማጠየቅና ለቅዱስ ሥጋውና ለክቡር ደሙ ክብር ስንል ዝቅ ብለን አንሰግድም።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
#ሼር በማድረግ ለጓደኞቻችሁ አካፍሉ።
https://www.tgoop.com/tmhrtegeeze



tgoop.com/tmhrtegeeze/10228
Create:
Last Update:

●       #የግዝት_በዓላት (#የማይሰገድባቸው_ጊዜያት)

     የሚሰገድባቸው ጊዜያት እንዳሉት ሁሉ የማይሰገድባቸው ጊዜያትም አሉ። የግዝት በዓላት 5 ሲሆኑ #የወልድ_በዓል፣ #የእመቤታችን_በዓል፣ #የቅዱስ_ሚካኤል በዓል፣ #ቀዳሚት_ሰንበትና_እሑድ_ሰንበት ናቸው። ከነዚህ በተጨማሪ #ከቁርባን በኋላና የበዓለ #ሐምሳ ወራትም የማይሰገድባቸው ጊዜያት ናቸው። እነዚህ ስግደት የተገዘተባቸው ጊዜያት የሚከተሉት ናቸው።
         1ኛ       #በዕለተ_እሑድ

ከአልቦ ነገር ወይም ከምንም (ex- nihilo - from nothingness) ሁሉ ክርስቶስ ዳግም ሲመጣ ጠፍቶ ወደ ምንምነት ሲቀየር ከማይጠፉ ከአምስቱ ፍጥረታት አንዷ ሰንበት ናት። ጌታ የተነሣባት ፣ ዳግምም የሚመጣባት ዕለት ናት። በዚህና በሌሎች ምክንያቶችም ሰንበተ ክርስቲያን እሑድ በዓል ነች። ስለዚህ በዕለተ እሑድ መስገድ የተከለከለ ነው።
            2ኛ     #በዕለተ_ቅዳሜ

    ሌላው ከዕለታት መካከል ቅዳሜ የግዝት በዓል ተብሎ የተመረጠበት ምክንያት የሁሉ ባለቤት የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር ዓለማትን ሁሉ በስድስት ቀናት ውስጥ ፈጥሮ ከፈጸመ በኋላ በሰባተኛው ቀን አረፈ። ይህችንም ቀን ቀደሳት ለሰው ልጆችም በዓል አድርጎ ሰጠን። “በሰንበትም እንደ ትእዛዙ ዐረፉ።” ሉቃ 23፥56
3ኛ            #በጌታችን_በዓላት

    ፍትሐ ነገሥቱ “በእሑድና በተከበሩት በዓላት ቀን ስግደት አይገባም፤ እነዚህ የደስታ ቀኖች ናቸውና” (ፍት.መን. አን. 19 ቁ. 715) ካለ በኋላ “የተከበሩት በዓላት” ያላቸው የትኞቹን እንደሆነ ሲዘረዝር ትስብእት/ጽንሰት ፣ ልደት ፣ ጥምቀት ፣ ሆሣዕና ፣ ትንሣኤ ፣ ዕርገት ፣ በዓለ ሃምሳ ፣ ደብረ ታቦር በማለት ከጌታ ዘጠኝ ዐበይት በዓላት 8ቱን ይገልፃል። ሳይገለፅ የቀረው ስቅለት ነው፤ ያልተገለፀበትም ምክንያት በስቅለት ስግደት ስለማይከለከል ነው። ስለዚህ ከስቅለት በቀር በጌታ ዐበይት በዓላት (በተቀሩት በ8ቱ) ስግደት የተከለከለ ነው።
4ኛ.            #በእመቤታችን_በዓላት

በፍት. መን. አን. 14 ቁ. 536-537 ድረስ በጌታ በዓላት መስገድ እንደተከለከለው ሁሉ በእመቤታችን በዓላትም መከልከሉን ይጠቁመናል። የወልድ በዓልን እንደምናከብረው የእመቤታችንንም በዓል በ21 አስበን አንሰግድም። ስለዚህ ወር በገባ በ21 ሁሌም የግዝት በዓል ነው፤ አይሰገድበትም።

5ኛ.           #በቅዱስ_ሚካኤል_በዓል

የቅዱስ ሚካኤል በዓል ከሌሎች የመላእክት በዓላት ተለይቶ መከበሩ ለምንድነው ቢሉ

“የቅዱስ ሚካኤል በዓል መላእክትን ወክሎ ወርኃዊ ሆኖ እንዲከበር ታዟል” (በዓላት ፣ ዲ.ን. ብርሃኑ አድማስ ፣ ገጽ 124)። ስለዚህ ቤተ ክርስቲያን በ12 እንዳይሰገድና እንደ ታላላቅ በዓላት በደስታ እንዲከበር ሥርዐትን ሠርታለች።
6ኛ.          #ሥጋና_ደሙን_ከተቀበሉ_በኋላ

የሥርዐት ምንጫችን የሆነው ፍትሐ ነገሥት አሁንም በዚህ ዙሪያ እንዲህ ብሏል፦ “መስገድን የሚተዉባቸው የታወቁ በዓላት እነዚህ ናቸው… ሥጋውንና ደሙን ከተቀበሉ በኋላ” ይላል። ፍት. መን. አን. 14 ቁ. 536- 537። ሥጋውንና ደሙን ከተቀበልን በኋላ ከሚሰገድለት እንጂ ከማይሰግደው ጋር አንድ መሆናችንን ለማጠየቅና ለቅዱስ ሥጋውና ለክቡር ደሙ ክብር ስንል ዝቅ ብለን አንሰግድም።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
#ሼር በማድረግ ለጓደኞቻችሁ አካፍሉ።
https://www.tgoop.com/tmhrtegeeze

BY ✝️(ትምህርተ ግዕዝ)✝️




Share with your friend now:
tgoop.com/tmhrtegeeze/10228

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

End-to-end encryption is an important feature in messaging, as it's the first step in protecting users from surveillance. You can invite up to 200 people from your contacts to join your channel as the next step. Select the users you want to add and click “Invite.” You can skip this step altogether. Ng was convicted in April for conspiracy to incite a riot, public nuisance, arson, criminal damage, manufacturing of explosives, administering poison and wounding with intent to do grievous bodily harm between October 2019 and June 2020. There have been several contributions to the group with members posting voice notes of screaming, yelling, groaning, and wailing in different rhythms and pitches. Calling out the “degenerate” community or the crypto obsessives that engage in high-risk trading, Co-founder of NFT renting protocol Rentable World emiliano.eth shared this group on his Twitter. He wrote: “hey degen, are you stressed? Just let it out all out. Voice only tg channel for screaming”. Telegram channels fall into two types:
from us


Telegram ✝️(ትምህርተ ግዕዝ)✝️
FROM American