#ይሉኝታ
በቤተ ክርስቲያን ጉዳይ ይሉኝታና ኩርፊያ አይሠራም። ቅድሚያ የሚሰጠው እግዚአብሔራዊው እውነት ነው። ዮናስ "ሐሰተኛ ነቢይ" እባላለሁ ብሎ እግዚአብሔራዊውን እውነት ላለመናገር በመርከብ ተጭኖ ሲሄድ ለብዙ ሰዎች ንብረት ውድመት ምክንያት ሆኗል። ሰዎች የሌለህን ማንነት ነህ ብለው በይሉኝታ አጥረው ክፋታቸውን ሲሠሩ ዝም እንድትል ሊፈልጉ ይችላሉ። በዚህ ጊዜ ይሉኝታ አያስፈልግም። የፈለገ ክብር ቢኖርህ ስለቤተ ክርስቲያን ብለህ ክብርህን ትተህ እውነታውን መጋፈጥ አስፈላጊ ነው።
ኢየሱስ ክርስቶስን በጩኸታቸው ብዛት በደለኛ ነው ይሰቀል ቢሉም እርሱ ግን ንጹሐ ባሕርይ ነበር። ብዙዎች በሐሰት ስለጮሁ የሚቀየር ማንነት ሊኖረን አይገባም። በጥበብና በፍቅር እውነታውን ማስረዳት ከሁላችንም ይጠበቃል። አንዳንዶች ዘረኛ እንባላለን ብለው ሰግተው የተወለዱበት አካባቢ ብዙ መከራ ሲደርስበት ድምፅ አይሆኑም። በዚህ ጊዜ ግን እውነታውን ተናግሮ ዘረኛ መባል የተሻለ ነው። ሰው እውነትን በመናገሩ ማንኛውንም ዓይነት ስም ቢሰጠው ማፈርም መፍራትም አይገባውም። ቅድሚያ ለእውነት። የቤተክርስቲያንም የማንኛውም ሰውም ባለቤቱ እግዚአብሔር ነው። ስለዚህ ከእኛ የሚጠበቀው እውነታውን መናገር ነው። የእኛ ደስታ እውነትን በመናገር የሚገኝ ነው። ቅዱሳን ሰማዕታት እውነትን በመናገራቸው የተለያዩ መከራዎች ደርሶባቸዋል። ያ መከራ ግን የክብር ምንጭ ነው።
በእውነትና በውሸት መካከል ሌላ ሦስተኛ ነገር የለም። እውነትንና ውሸትን አቻችለን እንኑር አይባልም። እውነት ከውሸት በላይ ገዢ ሆና እንድትኖር መሥራት ከሁሉም ይጠበቃል።
©በትረማርያም አበባው
በቤተ ክርስቲያን ጉዳይ ይሉኝታና ኩርፊያ አይሠራም። ቅድሚያ የሚሰጠው እግዚአብሔራዊው እውነት ነው። ዮናስ "ሐሰተኛ ነቢይ" እባላለሁ ብሎ እግዚአብሔራዊውን እውነት ላለመናገር በመርከብ ተጭኖ ሲሄድ ለብዙ ሰዎች ንብረት ውድመት ምክንያት ሆኗል። ሰዎች የሌለህን ማንነት ነህ ብለው በይሉኝታ አጥረው ክፋታቸውን ሲሠሩ ዝም እንድትል ሊፈልጉ ይችላሉ። በዚህ ጊዜ ይሉኝታ አያስፈልግም። የፈለገ ክብር ቢኖርህ ስለቤተ ክርስቲያን ብለህ ክብርህን ትተህ እውነታውን መጋፈጥ አስፈላጊ ነው።
ኢየሱስ ክርስቶስን በጩኸታቸው ብዛት በደለኛ ነው ይሰቀል ቢሉም እርሱ ግን ንጹሐ ባሕርይ ነበር። ብዙዎች በሐሰት ስለጮሁ የሚቀየር ማንነት ሊኖረን አይገባም። በጥበብና በፍቅር እውነታውን ማስረዳት ከሁላችንም ይጠበቃል። አንዳንዶች ዘረኛ እንባላለን ብለው ሰግተው የተወለዱበት አካባቢ ብዙ መከራ ሲደርስበት ድምፅ አይሆኑም። በዚህ ጊዜ ግን እውነታውን ተናግሮ ዘረኛ መባል የተሻለ ነው። ሰው እውነትን በመናገሩ ማንኛውንም ዓይነት ስም ቢሰጠው ማፈርም መፍራትም አይገባውም። ቅድሚያ ለእውነት። የቤተክርስቲያንም የማንኛውም ሰውም ባለቤቱ እግዚአብሔር ነው። ስለዚህ ከእኛ የሚጠበቀው እውነታውን መናገር ነው። የእኛ ደስታ እውነትን በመናገር የሚገኝ ነው። ቅዱሳን ሰማዕታት እውነትን በመናገራቸው የተለያዩ መከራዎች ደርሶባቸዋል። ያ መከራ ግን የክብር ምንጭ ነው።
በእውነትና በውሸት መካከል ሌላ ሦስተኛ ነገር የለም። እውነትንና ውሸትን አቻችለን እንኑር አይባልም። እውነት ከውሸት በላይ ገዢ ሆና እንድትኖር መሥራት ከሁሉም ይጠበቃል።
©በትረማርያም አበባው
❤4🙏1
በአዳማ ከተማ የመስቀል አደባባይን መጠቀም አትችሉም።
-በ27/09/2017 ዓ.ም የአዳማ ከተማ ከንቲባ የደብር አስተዳዳሪዎችን፣ የሀገረ ስብከት ኃላፊዎችን፣ የሰንበት ትምህርት ቤት ተወካዮችን ሰብስበው "ለሥራ ፈልገነዋል የመስቀል አደባባይን ከዚህ በኋላ መጠቀም አትችሉም። ሌላ እንሰጣችኋለን። ቀጣይ ዓመት ጀምራችሁ መጠቀም አትችሉም" ብለዋል። የደብር አስተዳዳሪዎችና የሀገረ ስብከት ኃላፊዎች መንግሥት ያለውን ተቀብለው ተስማምተው አመስግነው ከስብሰባ ወጥተዋል።
-መስቀል አደባባይ ከተማው ከተቆረቆረ ጀምሮ ካህናትና ምዕመናን ሲጠቀሙበት የነበረ ነው። ከንቲባው ከሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ጋር ለረጅም ጊዜ አውርተናል ሲል ነበር። ለማንኛውም በ2018 ዓ.ም በአዳማ ከተማ በተለመደው የመስቀል አደባባይ የመስቀል በዓል አይከበርም። በተለይ የከተማው ነዋሪዎች አካባቢውን የምታውቁ ስለ መስቀል አደባባዩ ነገር ንገሩን። ቦታ መቀየሩ ምን ያህል ተገቢና ምክንያታዊ ነው?
©ዮሴፍ ፍስሐ
-በ27/09/2017 ዓ.ም የአዳማ ከተማ ከንቲባ የደብር አስተዳዳሪዎችን፣ የሀገረ ስብከት ኃላፊዎችን፣ የሰንበት ትምህርት ቤት ተወካዮችን ሰብስበው "ለሥራ ፈልገነዋል የመስቀል አደባባይን ከዚህ በኋላ መጠቀም አትችሉም። ሌላ እንሰጣችኋለን። ቀጣይ ዓመት ጀምራችሁ መጠቀም አትችሉም" ብለዋል። የደብር አስተዳዳሪዎችና የሀገረ ስብከት ኃላፊዎች መንግሥት ያለውን ተቀብለው ተስማምተው አመስግነው ከስብሰባ ወጥተዋል።
-መስቀል አደባባይ ከተማው ከተቆረቆረ ጀምሮ ካህናትና ምዕመናን ሲጠቀሙበት የነበረ ነው። ከንቲባው ከሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ጋር ለረጅም ጊዜ አውርተናል ሲል ነበር። ለማንኛውም በ2018 ዓ.ም በአዳማ ከተማ በተለመደው የመስቀል አደባባይ የመስቀል በዓል አይከበርም። በተለይ የከተማው ነዋሪዎች አካባቢውን የምታውቁ ስለ መስቀል አደባባዩ ነገር ንገሩን። ቦታ መቀየሩ ምን ያህል ተገቢና ምክንያታዊ ነው?
©ዮሴፍ ፍስሐ
❤5
የሐዋርያት ጾም(ጾመ ሐዋርያት)
ጾመ ሐዋርያት ከሰባቱ የአዋጅ አጿማት መካከል አንዱ ሲሆን ቅዱሳን ሐዋርያት የእግዚአብሔርን ሥራ ወንጌልን መስበክ ከመጀመራቸው በፊት የሥራቸው መጀመሪያ ያደረጉት ጾምና ጸሎት ነበር። ከዚያ በኋላም ቅዱሳን አበው ቀኖና ሲሰሩ በቅዱስ ሲኖዶስ ከአጿማት አንዱ እንዲሆንና ክርስቲያኖች ሁሉ እንዲጾሙት ወስነዋል። (ሐዋ•፲፫፣፪-፫)13:2-3)
በመሆኑም ጾመ ሐዋርያት ሁሌ እንደ የዓመቱ መግቢያው የተለያየ ነው። ነገር ግን መፍቺያው ግን ሁልጊዜ ሐምሌ ፭(5) ሊቀ ሐዋርያት ቅዱስ ጴጥሮስ እና ብርሃነ አለም ማኅቶተ ቤተከርስቲያን ቅዱስ ጳውሎስ በሚታሰቡበት ዕለት ይፈታል።
እንደ ሥርዓት ጾመ ሐዋርያት የሚጾመው እስከ ዘጠኝ ሰዓት ነው። ይህ ጾም በቀመረ ባሕረ ሐሳብ የአጽዋማት አወጣጥ ቀመር መሰረት ጾሙ ዝቅተኛ ቀን ከሰኔ ፳ (20)ገብቶ እስከ ሐምሌ ፬(4) የሚጾም ሲሆን በሐምሌ ፭(5) ቀን የሚፈታበት ቀን የጾሙ ብዛት ፲፭ (15)ቀን ብቻ ይሆናል ማለት ነው።
የጾሙ ከፍተኛ ቀን ግንቦት ፲፮(16) ገብቶ እስከ ሐምሌ ፬ የሚጾም ሲሆን በሐምሌ ፭(5) ቀን የሚፈታበት ቀን የጾሙ ብዛት ፵፱ (49)ቀን ይሆናል ማለት ነው። ስለዚህም የጾመ
ሐዋርያት የቀን ብዛት ፲፭(15) ቀን እስከ ፵፱(49) ቀን ይሆናል ማለት ነው።
በዘንድሮው የባህረ ሃሳብ ዘመን ጾመ ሐዋርያት በሰኔ ፪(2) ይገባል የአርብ እና የረቡዕ ጾም ሰኔ ፬(4) ይጀምራል ጾመ ሐዋርያት ከሰኔ ፪(2) እስከ ሐምሌ4(፬) የሚጾም ሲሆን በሐምሌ ፭(5) ቀን ይፈታል በዚህም መሰረት በዚህ ዘመን የጾሙ ቀን ብዛት ፴፫(33) ነው።
እግዚአብሔር አምላክ በቸርነቱ በረከት ለምናገኝበት ለከበረው ጾመ ሐዋርያት በሠላም ያድርሰን ያድርሳቹሁ።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር።
ጾመ ሐዋርያት ከሰባቱ የአዋጅ አጿማት መካከል አንዱ ሲሆን ቅዱሳን ሐዋርያት የእግዚአብሔርን ሥራ ወንጌልን መስበክ ከመጀመራቸው በፊት የሥራቸው መጀመሪያ ያደረጉት ጾምና ጸሎት ነበር። ከዚያ በኋላም ቅዱሳን አበው ቀኖና ሲሰሩ በቅዱስ ሲኖዶስ ከአጿማት አንዱ እንዲሆንና ክርስቲያኖች ሁሉ እንዲጾሙት ወስነዋል። (ሐዋ•፲፫፣፪-፫)13:2-3)
በመሆኑም ጾመ ሐዋርያት ሁሌ እንደ የዓመቱ መግቢያው የተለያየ ነው። ነገር ግን መፍቺያው ግን ሁልጊዜ ሐምሌ ፭(5) ሊቀ ሐዋርያት ቅዱስ ጴጥሮስ እና ብርሃነ አለም ማኅቶተ ቤተከርስቲያን ቅዱስ ጳውሎስ በሚታሰቡበት ዕለት ይፈታል።
እንደ ሥርዓት ጾመ ሐዋርያት የሚጾመው እስከ ዘጠኝ ሰዓት ነው። ይህ ጾም በቀመረ ባሕረ ሐሳብ የአጽዋማት አወጣጥ ቀመር መሰረት ጾሙ ዝቅተኛ ቀን ከሰኔ ፳ (20)ገብቶ እስከ ሐምሌ ፬(4) የሚጾም ሲሆን በሐምሌ ፭(5) ቀን የሚፈታበት ቀን የጾሙ ብዛት ፲፭ (15)ቀን ብቻ ይሆናል ማለት ነው።
የጾሙ ከፍተኛ ቀን ግንቦት ፲፮(16) ገብቶ እስከ ሐምሌ ፬ የሚጾም ሲሆን በሐምሌ ፭(5) ቀን የሚፈታበት ቀን የጾሙ ብዛት ፵፱ (49)ቀን ይሆናል ማለት ነው። ስለዚህም የጾመ
ሐዋርያት የቀን ብዛት ፲፭(15) ቀን እስከ ፵፱(49) ቀን ይሆናል ማለት ነው።
በዘንድሮው የባህረ ሃሳብ ዘመን ጾመ ሐዋርያት በሰኔ ፪(2) ይገባል የአርብ እና የረቡዕ ጾም ሰኔ ፬(4) ይጀምራል ጾመ ሐዋርያት ከሰኔ ፪(2) እስከ ሐምሌ4(፬) የሚጾም ሲሆን በሐምሌ ፭(5) ቀን ይፈታል በዚህም መሰረት በዚህ ዘመን የጾሙ ቀን ብዛት ፴፫(33) ነው።
እግዚአብሔር አምላክ በቸርነቱ በረከት ለምናገኝበት ለከበረው ጾመ ሐዋርያት በሠላም ያድርሰን ያድርሳቹሁ።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር።
❤2
በዩናይትድ ኪንግደም የሚገኙ ምዕመናን በአካባቢው የቤተክርስቲያን አንድነት እና መዋቅር በከፍተኛ ደረጃ ለአደጋ መጋረጡን ለቅዱስ ሲኖዶስ በጻፉት ደብዳቤ ገለጹ !
ሰኔ 1 ቀን 2017 ዓ.ም (ተ.ሚ.ማ/አዲስ አበባ)
ወቅታዊ የቤተ ክርስቲያናንን ጉዳይ መነሻ በማድረግ ለቅዱስ ሲኖዶስ የቀረበ ጥሪ በሚል ግንቦት 30 ቀን 2017 ዓ.ም በተጻፈ ደብዳቤ በዩናይትድ ኪንግደም የሚገኙ ምእመናን የቤተ ክርስቲያን አንድነት አደጋ ውስጥ መግባቱን ነው የገለጹት።
“የዩናይትድ ኪንግደም ምዕመናኑን በቤተ ክርስቲያን ውስጥ በሚኖረው የአገልግሎት ተሳትፎ አማካይነት አላስፈላጊ ጉዳዮችን ወደ ቤተ ክርስቲያን በማምጣት የምዕመኑን አንድነት ከማጠናከር ይልቅ ወደ መለያየት በማድረግ ምዕመናኑ በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ልዩነት ቢኖረውም በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ልዩነቶችን በማንፀባረቅ ምዕመናኑን በዘር፣በፖለቲካና በተለያየ አስተሳሰብ እንዲለያይ ተደርጓል" ብለዋል ምእመናኑ።
በሀገረ ስብከቱ ውስጥ በልዩነቶችና ባለመግባባት ፤በማንችስተር፣ በሼፊልድ፣በሊድስ፤ በለንደን፤ በቅርቡ ጊዜ ደግሞ በስቶክ ኦን ትሬንት ከተማ በመለያየት የተለያዩ መንፈሳዊ ማህበራትና ደብራትን ሲያቋቁሙ ታይቷል ያሉት ምእመናኑ ሀገረ ስብከቱ በስያሜ ደረጃ ካልሆነ በቀር በተግባር ሙሉ በሙሉ አለመኖሩና ለዚህ ከፍተኛ ተጽዕኖ የፈጠረው በቅዱስ ሲኖዶስ ተሰይመው በዩናይትድ ኪንግደምና አየርላንድ ሀገረ ስብከት በሚል የበላይ ጠባቂ ሊቀጳጳስ ተመድቦ የነበረ ቢሆንም በሀገረ ስብከታችን የተመደቡት ሊቀጳጳስ በተመደቡበት መንበረ ጵጵስናቸው አለመኖር እና የምዕመናኑ ድምጽ የሚያዳምጥ አባት አለመኖሩ ግልጽ ማሳያ ነው ብለዋል።
ምዕመናኑ በሚኖርበት ከተማና በሚገለገልበት ደብር ላይ ሰላሙን ሊያደፈርስ ወይም ምዕመናን ወደመለያየት የሚያደርሱ ጉዳዮች ሲከሰት ምዕመናኑ በህብረት ችግሩን በመጋፈጥ የችግር ፈጣሪዎችን ለይቶ በማውጣት የራሱን ሰላም ሊያስጠብቅ ይገባል ነው ያሉት ምእመናኑ ፤ ምእመናኑ በተጨማሪም የቤተ ክርስቲያን ልዩነት በእጅጉ ገዝፎ በሚታይበት ሀገረ ስብከታችን ውስጥ እንደመገኘታችን የሀገረ ስብከታችን አለመጠናከርና ሀገረ ስብከታችን በአገልግሎቱ ህልው ባለመሆኑ እንደስያሜው ተገቢውን ተግባራት ባለማከናወኑ በኃላፊነት ላይ የተሰየሙት ግለሰቦች የቤተ ክርስቲያንን ጥቅም ከማስቀድ ይልቅ ግለሰባዊና የሥልጣን ጥማታቸውን ብቻ ለመጠቀም ፍላጎት በማሳየታቸው በመላው ዩኬ ለሚገኝ ምዕመናን መለየያየት ግድ የሌሽ መሆን የቤተ ክርስቲያናችንን ችግር ወደ ባሰ አዘቅት ውስጥ እየጨመረ መሆኑ ለማወቅ አያዳግተንም ነው ያሉት።
የምእመናን ሕብረቱም ለቅዱስ ሲኖዶስ
1ኛ. እንደቀደሙት አባቶቻችን ለቤተ ክርስቲያን እና ለመንጋችሁ ስትሉ ከቤተ ክርስቲያን እና ከመንጋው የሚበልጥ ምንም ስለሌለ ጉዳዩን በጥልቅ መክራችሁ በሀገረ ስብከታችን መንጋውን የሚጠብቅና የሚባርክ በጸሎት የሚያስቡንን አባት
በመንበረ ጵጵስናቸው እንዲቀመጡልን በልጅነት መንፈስ እንማጸናለን።
2ኛ. በየደብራቱ ( በየከተማ) የተፈጠረው ልዩነት ተወግዶ ቤተ ክርስቲያንን ወደ አንድነት ሊያመጣ የሚችል ጥንቃቄ የተሞላበት የሀገረ ስብከት አስተዳደር ደካማ እንቅስቃሴዎችንና ብልሹ አሰራሩ መፍትሄ በመስጠት ውሳኔ እንድትወስኑ አደራ
እንላለን።
3ኛ በቅርብ ጊዜያት በብፁዕ እቡነ ያዕቆብ ሰብሳቢነት በዩኬና አየርላንድ የሚገኙትን አገልጋይ ካህናት ዲያቆናት በመጥራት በተደረገው የሀገረ ስብከታችን ብልሹ አሰራርን በተመለከተ በተደረገው ውይይት ላይ ሰፊ ማብራሪያ እና ጥናት ተካሂዶ ሀገረ ስብከቱን በጥሩ አስተዳደር ለመተካትና በሀገሪቱ ያለችውን የቤተ ክርስቲያና አስተዳደራዊ ክንዋኔዎች በሕገ ቤተ ክርስቲያን ለማስቀጠልና ምዕመናኑን ከልዩነትና ከመከፋፍል ለመታደግ በተያዘው የሥራ ክንዋኔ በተመለከተ የጥናት አድራጊ ኮሚቴ የተከተውን ተልዕኮ እንዲያስፈጽምና የሀገረ ስብከታችንን አስተዳደራዊ ክፍተት በማደስ ወደ አንድነት መንፈሳዊ ጉዞአችን እንድንቀጥልና ስርዐተ አምልኮአችን በአግባቡ ለመፈጸም ያስችለን ዘንድ የቋሚ ቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ እና እርዳታ እንድናገኝ በማለት ጥያቄ ማቅረቡን ለተ.ሚ.ማ በላከው ደብዳቤ አስታውቋል።
ሰኔ 1 ቀን 2017 ዓ.ም (ተ.ሚ.ማ/አዲስ አበባ)
ወቅታዊ የቤተ ክርስቲያናንን ጉዳይ መነሻ በማድረግ ለቅዱስ ሲኖዶስ የቀረበ ጥሪ በሚል ግንቦት 30 ቀን 2017 ዓ.ም በተጻፈ ደብዳቤ በዩናይትድ ኪንግደም የሚገኙ ምእመናን የቤተ ክርስቲያን አንድነት አደጋ ውስጥ መግባቱን ነው የገለጹት።
“የዩናይትድ ኪንግደም ምዕመናኑን በቤተ ክርስቲያን ውስጥ በሚኖረው የአገልግሎት ተሳትፎ አማካይነት አላስፈላጊ ጉዳዮችን ወደ ቤተ ክርስቲያን በማምጣት የምዕመኑን አንድነት ከማጠናከር ይልቅ ወደ መለያየት በማድረግ ምዕመናኑ በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ልዩነት ቢኖረውም በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ልዩነቶችን በማንፀባረቅ ምዕመናኑን በዘር፣በፖለቲካና በተለያየ አስተሳሰብ እንዲለያይ ተደርጓል" ብለዋል ምእመናኑ።
በሀገረ ስብከቱ ውስጥ በልዩነቶችና ባለመግባባት ፤በማንችስተር፣ በሼፊልድ፣በሊድስ፤ በለንደን፤ በቅርቡ ጊዜ ደግሞ በስቶክ ኦን ትሬንት ከተማ በመለያየት የተለያዩ መንፈሳዊ ማህበራትና ደብራትን ሲያቋቁሙ ታይቷል ያሉት ምእመናኑ ሀገረ ስብከቱ በስያሜ ደረጃ ካልሆነ በቀር በተግባር ሙሉ በሙሉ አለመኖሩና ለዚህ ከፍተኛ ተጽዕኖ የፈጠረው በቅዱስ ሲኖዶስ ተሰይመው በዩናይትድ ኪንግደምና አየርላንድ ሀገረ ስብከት በሚል የበላይ ጠባቂ ሊቀጳጳስ ተመድቦ የነበረ ቢሆንም በሀገረ ስብከታችን የተመደቡት ሊቀጳጳስ በተመደቡበት መንበረ ጵጵስናቸው አለመኖር እና የምዕመናኑ ድምጽ የሚያዳምጥ አባት አለመኖሩ ግልጽ ማሳያ ነው ብለዋል።
ምዕመናኑ በሚኖርበት ከተማና በሚገለገልበት ደብር ላይ ሰላሙን ሊያደፈርስ ወይም ምዕመናን ወደመለያየት የሚያደርሱ ጉዳዮች ሲከሰት ምዕመናኑ በህብረት ችግሩን በመጋፈጥ የችግር ፈጣሪዎችን ለይቶ በማውጣት የራሱን ሰላም ሊያስጠብቅ ይገባል ነው ያሉት ምእመናኑ ፤ ምእመናኑ በተጨማሪም የቤተ ክርስቲያን ልዩነት በእጅጉ ገዝፎ በሚታይበት ሀገረ ስብከታችን ውስጥ እንደመገኘታችን የሀገረ ስብከታችን አለመጠናከርና ሀገረ ስብከታችን በአገልግሎቱ ህልው ባለመሆኑ እንደስያሜው ተገቢውን ተግባራት ባለማከናወኑ በኃላፊነት ላይ የተሰየሙት ግለሰቦች የቤተ ክርስቲያንን ጥቅም ከማስቀድ ይልቅ ግለሰባዊና የሥልጣን ጥማታቸውን ብቻ ለመጠቀም ፍላጎት በማሳየታቸው በመላው ዩኬ ለሚገኝ ምዕመናን መለየያየት ግድ የሌሽ መሆን የቤተ ክርስቲያናችንን ችግር ወደ ባሰ አዘቅት ውስጥ እየጨመረ መሆኑ ለማወቅ አያዳግተንም ነው ያሉት።
የምእመናን ሕብረቱም ለቅዱስ ሲኖዶስ
1ኛ. እንደቀደሙት አባቶቻችን ለቤተ ክርስቲያን እና ለመንጋችሁ ስትሉ ከቤተ ክርስቲያን እና ከመንጋው የሚበልጥ ምንም ስለሌለ ጉዳዩን በጥልቅ መክራችሁ በሀገረ ስብከታችን መንጋውን የሚጠብቅና የሚባርክ በጸሎት የሚያስቡንን አባት
በመንበረ ጵጵስናቸው እንዲቀመጡልን በልጅነት መንፈስ እንማጸናለን።
2ኛ. በየደብራቱ ( በየከተማ) የተፈጠረው ልዩነት ተወግዶ ቤተ ክርስቲያንን ወደ አንድነት ሊያመጣ የሚችል ጥንቃቄ የተሞላበት የሀገረ ስብከት አስተዳደር ደካማ እንቅስቃሴዎችንና ብልሹ አሰራሩ መፍትሄ በመስጠት ውሳኔ እንድትወስኑ አደራ
እንላለን።
3ኛ በቅርብ ጊዜያት በብፁዕ እቡነ ያዕቆብ ሰብሳቢነት በዩኬና አየርላንድ የሚገኙትን አገልጋይ ካህናት ዲያቆናት በመጥራት በተደረገው የሀገረ ስብከታችን ብልሹ አሰራርን በተመለከተ በተደረገው ውይይት ላይ ሰፊ ማብራሪያ እና ጥናት ተካሂዶ ሀገረ ስብከቱን በጥሩ አስተዳደር ለመተካትና በሀገሪቱ ያለችውን የቤተ ክርስቲያና አስተዳደራዊ ክንዋኔዎች በሕገ ቤተ ክርስቲያን ለማስቀጠልና ምዕመናኑን ከልዩነትና ከመከፋፍል ለመታደግ በተያዘው የሥራ ክንዋኔ በተመለከተ የጥናት አድራጊ ኮሚቴ የተከተውን ተልዕኮ እንዲያስፈጽምና የሀገረ ስብከታችንን አስተዳደራዊ ክፍተት በማደስ ወደ አንድነት መንፈሳዊ ጉዞአችን እንድንቀጥልና ስርዐተ አምልኮአችን በአግባቡ ለመፈጸም ያስችለን ዘንድ የቋሚ ቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ እና እርዳታ እንድናገኝ በማለት ጥያቄ ማቅረቡን ለተ.ሚ.ማ በላከው ደብዳቤ አስታውቋል።
❤1
የእውነት ክርስቲያን ነህ?
፦አንድ እግዚአብሔር ያለው ኦርቶዶክሳዊ ነህ? ኤፌ.፬፥፭
፦አንድ እናት አንድ አባት ያለው ጥሙቅ ነህ? ማር.፲፮፥፲፮
፦አንድ ሙሽራ ያላት አንዲት ሙሽሪት ነህ? ማቴ.፳፪፥፩-፯
፦አንድ መምህር ያላት አንዲት ደቀመዝሙር ነህ? ማቴ.፳፰፥፲፱
፦አንድ መሥዋዕት ያላት አንድ ተቀባይ ነህ?፤ ዕብ.፩፥፩፣ዮሐ፮፥፶፮
፦አንድ ክህነት ያላት አንድት ተባራኪ ነህ? ማቴ.፲፮፥፲፰
፦አንድ ራስ ያላት ህዋስ ነህ? ቆላ.፩፥፲፰
፦ከማይጠፋ ዘር የተወለድህ ልዩ አካል ነህ?፤ ዮሐ.፫፥፬
፦አንድ ዐላማ ያላት ተስፈኛ ነህ?፤ (ግዕዝ ርትዕት) ማቴ.፲፫፥፮
፦ግእዛን ያላቸው ፍጥረታት እና የፈጣሪ ግንኙነት ኅብረት ባለቤት ነህ?
፦አንድ ቀዛፊ ብዙ ተሳፋሪ ባያላት መርከብ ውስጥ ነህ?ዘፍ.፮፥፲፭
፦አንድ የክርስቶስን መስቀል የተሸከምህ ክርስቶሳዊ ነህ? ማቴ.፲፮፥፳፬
፦ሐዋርያዊት፣ቅድስት፣አንዲት፣ኲላዊት በሆነች ቤተ ክርስቲያን ሥር ነህ? ማቴ.፲፰፥፲፯
.....ይሄንን ሁሉ ከሆንህ በጣም ጥሩ።
ክርስቲያን ከሆንህ እያደረግህ ያለኸው ምንድን ነው?
እየመከርህ ያለኸው ከማን ጋር ነው?
በቤተ ክርስቲናን ላይ እየሆነ ያለውን እንዴት ታየዋለህ?
ክርስቲዮኖቹ ሁሉ አካሌ ናቸው ብለህ ታስባለህ?
ትንሣኤ ሙታንን የማምን ርቱዕ ኦርቶዶክሳዊ ነኝ ብለህ ታስባለህ?
የምኖርበት ትክክለኛ ኦርቶዶክሳዊ ሕይወት ነው ብለህ ታምናለህ?
የምታምነውና የምትኖረው አንድ ነው? አፍህና ልብህ የተስማሙ ናቸው?
የእውነት የክርስቶስን መስቀል የተሸከመ ክርስቲያን ነህ?
በመንደር፣በቋንቋ፣በጎሳ፣በሥሁት ፖለቲካ፣በአስመሳይነት፣በግብዝነት፣በስግብግብነት ውስጥ የለህበትም?
አንድ ክርስቶሳዊ ወንድምህን ስታይ ክርስቶስ ይታሰብሀል?
የቤተ ክርስቲያን መዋረድ፣መሳደድ፣በመንደርተኞች ምክንያት መለያየት፣የቀኖናው መጣስ፣የምእመናን መከራ ያስጨንቅሀል?
የእውነት ክርስቲያን ነህ?
የኔታ ገብረመድኅን እንየው
፦አንድ እግዚአብሔር ያለው ኦርቶዶክሳዊ ነህ? ኤፌ.፬፥፭
፦አንድ እናት አንድ አባት ያለው ጥሙቅ ነህ? ማር.፲፮፥፲፮
፦አንድ ሙሽራ ያላት አንዲት ሙሽሪት ነህ? ማቴ.፳፪፥፩-፯
፦አንድ መምህር ያላት አንዲት ደቀመዝሙር ነህ? ማቴ.፳፰፥፲፱
፦አንድ መሥዋዕት ያላት አንድ ተቀባይ ነህ?፤ ዕብ.፩፥፩፣ዮሐ፮፥፶፮
፦አንድ ክህነት ያላት አንድት ተባራኪ ነህ? ማቴ.፲፮፥፲፰
፦አንድ ራስ ያላት ህዋስ ነህ? ቆላ.፩፥፲፰
፦ከማይጠፋ ዘር የተወለድህ ልዩ አካል ነህ?፤ ዮሐ.፫፥፬
፦አንድ ዐላማ ያላት ተስፈኛ ነህ?፤ (ግዕዝ ርትዕት) ማቴ.፲፫፥፮
፦ግእዛን ያላቸው ፍጥረታት እና የፈጣሪ ግንኙነት ኅብረት ባለቤት ነህ?
፦አንድ ቀዛፊ ብዙ ተሳፋሪ ባያላት መርከብ ውስጥ ነህ?ዘፍ.፮፥፲፭
፦አንድ የክርስቶስን መስቀል የተሸከምህ ክርስቶሳዊ ነህ? ማቴ.፲፮፥፳፬
፦ሐዋርያዊት፣ቅድስት፣አንዲት፣ኲላዊት በሆነች ቤተ ክርስቲያን ሥር ነህ? ማቴ.፲፰፥፲፯
.....ይሄንን ሁሉ ከሆንህ በጣም ጥሩ።
ክርስቲያን ከሆንህ እያደረግህ ያለኸው ምንድን ነው?
እየመከርህ ያለኸው ከማን ጋር ነው?
በቤተ ክርስቲናን ላይ እየሆነ ያለውን እንዴት ታየዋለህ?
ክርስቲዮኖቹ ሁሉ አካሌ ናቸው ብለህ ታስባለህ?
ትንሣኤ ሙታንን የማምን ርቱዕ ኦርቶዶክሳዊ ነኝ ብለህ ታስባለህ?
የምኖርበት ትክክለኛ ኦርቶዶክሳዊ ሕይወት ነው ብለህ ታምናለህ?
የምታምነውና የምትኖረው አንድ ነው? አፍህና ልብህ የተስማሙ ናቸው?
የእውነት የክርስቶስን መስቀል የተሸከመ ክርስቲያን ነህ?
በመንደር፣በቋንቋ፣በጎሳ፣በሥሁት ፖለቲካ፣በአስመሳይነት፣በግብዝነት፣በስግብግብነት ውስጥ የለህበትም?
አንድ ክርስቶሳዊ ወንድምህን ስታይ ክርስቶስ ይታሰብሀል?
የቤተ ክርስቲያን መዋረድ፣መሳደድ፣በመንደርተኞች ምክንያት መለያየት፣የቀኖናው መጣስ፣የምእመናን መከራ ያስጨንቅሀል?
የእውነት ክርስቲያን ነህ?
የኔታ ገብረመድኅን እንየው
❤5🙏3
ዜና ሹመት
ብፀዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ለተለያዩ የሥራ ኀላፊዎች ሹመቶችን ሰጡ።
( ሰኔ 09 2017 ዓ.ም)
በዛሬው ዕለት ብፀዕ አቡነ ሳዊሮስ
የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ለመምሪያ ኀላፊዎች ዝውውር እና ለአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሥራ ኀላፊዎች ሹመቶችን ሰጥተዋል።
በዚህም መሠረት፦
፩ኛ. መልአከ ሰላም ዳዊት ያሬድ ከጠቅላይ ቤተክህነት ቅርስ ጥበቃ ቤተ መጻሕፍት ወመዘክር መምሪያ ወደ ጠ/ቤ/ክህነት ስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ ተልእኮ መምሪያ፤
፪ኛ. መ/ር ዶ/ር አካለወልድ ተሰማ ከጠቅላይ ቤተክህነት አስተዳደር መምሪያ ወደ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የመገናኛ ብዙኃን ሥርጭት ድርጅት EOTC TV ዋና ሥራ አስኪያጅ፤
፫ኛ. ሊ/መ ሐረገወይን ጫኔ ከሰበካ ጉባኤ ማደራጃ መምሪያ ወደ ጠቅላይ ቤተክህነት አስተዳደር መምሪያ፤
፬ ዶ/ር አባ ቃለጽድቅ ሙሉጌታ ከጠቅላይ ቤተክህነት ስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ ተልእኮ መምሪያ ወደ ጠ/ቤ/ክህነት የሰበካ ጉባኤ ማደራጃ መምሪያ፤
፭ኛ. መ/ር ምትኩ ከንቲባ ከጠቅላይ ቤተክህነት ስብከተ ወንጌል መምሪያ ተዘዋዋሪ ሰባኪነት ወደ ጠቅላይ ቤተክህነት የቅርሳቅርስ ጥበቃ ቤተ መጻሕፍት ወመዘክር መምሪያ፤
፮ኛ. ቀሲስ ዶ/ር መዝገቡ ካሳ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቴሌቪዥን ሥርጭት ድርጅት ወደ ቅ/ሥላሴ ዩኒቨርስቲ ተዛውረው እንዲሠሩ ተመድበዋል።
በሌላ በኩል ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ ለአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅነት ጨምሮ የተወሰኑ አዳዲስ ዋና ክፍሎችን በመምረጥ በብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ ፊርማ እንዲመደቡ አድርገዋል።
በዚህም መሠረት፦
፩ኛ. መ/ም አባ ገ/መድኅን ንጉሤ ከም/ሸዋ ሀገረ ስብከት ወደ ከዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ተዛውረው የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ሆነው እንዲሠሩ ተመድበዋል።
፪ኛ. መ/አእላፍ ማሙዬ ሸዋፈራው ከጠቅላይ ቤተክህነት ትንሣኤ ማሳተሚያ ድርጅት ምክትል ኀላፊ ወደ አዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ጸሐፊ፤
፫ኛ. መምህር አስናቀ ሸዋዬ ከጠቅላይ ቤተክህነት ቁጥጥር መምሪያ ተቆጣጣሪነት ወደ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከ ሂሳብ እና በጀት ዋና ኃላፊ፤
፬ኛ. ሊ/ኅሩያን ባዩ ተዘራ ከአዲስ ከተማ ቂርቆስ ልደታ ክፍለ ከተማ ቤተክህነት የሰንበት ትምህር ቤቶች ክፍል ኀላፊ ወደ የሀ/ስብከቱ የሰው ኀይል አስተዳደር ዋና ክፍል ኀላፊ፤
፭ኛ. መ/ሰላም ጽጌ ከበረ ከጠቅላይ ቤተክህነት ሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ምክትል ኀላፊ ወደ አዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የማኅበራት ማደራጃ ዋና ክፍል ኀላፊ፤
፮ኛ. ሊቀ ሥልጣናት አባ ጥዑመ ልሳን ኪዳነ ማርያም ከመንበረ መንግሥት ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን አስተዳዳሪነት ወደ አዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ገዳማት ዋና ክፍል ኀላፊ፤
፯ኛ. መ/ስብሐት ዐቢይ ዘለቀ ከቤቶችና ሕንጻዎች አስተዳደርና ልማት ድርጅት ወደ አዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ተዛውረው የሀገረ ስብከቱ ብፁዕ ሊቀ ጳጳስ ልዩ ጸሐፊ ሆነው እንዲሠሩ ተመድበዋል።
መረጃው፡-የኢ/ኦ/ተ/ ቤተ ክርስቲያን የሕዝብ ግንኘነት መምሪያ ነው፡፡
ብፀዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ለተለያዩ የሥራ ኀላፊዎች ሹመቶችን ሰጡ።
( ሰኔ 09 2017 ዓ.ም)
በዛሬው ዕለት ብፀዕ አቡነ ሳዊሮስ
የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ለመምሪያ ኀላፊዎች ዝውውር እና ለአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሥራ ኀላፊዎች ሹመቶችን ሰጥተዋል።
በዚህም መሠረት፦
፩ኛ. መልአከ ሰላም ዳዊት ያሬድ ከጠቅላይ ቤተክህነት ቅርስ ጥበቃ ቤተ መጻሕፍት ወመዘክር መምሪያ ወደ ጠ/ቤ/ክህነት ስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ ተልእኮ መምሪያ፤
፪ኛ. መ/ር ዶ/ር አካለወልድ ተሰማ ከጠቅላይ ቤተክህነት አስተዳደር መምሪያ ወደ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የመገናኛ ብዙኃን ሥርጭት ድርጅት EOTC TV ዋና ሥራ አስኪያጅ፤
፫ኛ. ሊ/መ ሐረገወይን ጫኔ ከሰበካ ጉባኤ ማደራጃ መምሪያ ወደ ጠቅላይ ቤተክህነት አስተዳደር መምሪያ፤
፬ ዶ/ር አባ ቃለጽድቅ ሙሉጌታ ከጠቅላይ ቤተክህነት ስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ ተልእኮ መምሪያ ወደ ጠ/ቤ/ክህነት የሰበካ ጉባኤ ማደራጃ መምሪያ፤
፭ኛ. መ/ር ምትኩ ከንቲባ ከጠቅላይ ቤተክህነት ስብከተ ወንጌል መምሪያ ተዘዋዋሪ ሰባኪነት ወደ ጠቅላይ ቤተክህነት የቅርሳቅርስ ጥበቃ ቤተ መጻሕፍት ወመዘክር መምሪያ፤
፮ኛ. ቀሲስ ዶ/ር መዝገቡ ካሳ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቴሌቪዥን ሥርጭት ድርጅት ወደ ቅ/ሥላሴ ዩኒቨርስቲ ተዛውረው እንዲሠሩ ተመድበዋል።
በሌላ በኩል ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ ለአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅነት ጨምሮ የተወሰኑ አዳዲስ ዋና ክፍሎችን በመምረጥ በብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ ፊርማ እንዲመደቡ አድርገዋል።
በዚህም መሠረት፦
፩ኛ. መ/ም አባ ገ/መድኅን ንጉሤ ከም/ሸዋ ሀገረ ስብከት ወደ ከዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ተዛውረው የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ሆነው እንዲሠሩ ተመድበዋል።
፪ኛ. መ/አእላፍ ማሙዬ ሸዋፈራው ከጠቅላይ ቤተክህነት ትንሣኤ ማሳተሚያ ድርጅት ምክትል ኀላፊ ወደ አዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ጸሐፊ፤
፫ኛ. መምህር አስናቀ ሸዋዬ ከጠቅላይ ቤተክህነት ቁጥጥር መምሪያ ተቆጣጣሪነት ወደ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከ ሂሳብ እና በጀት ዋና ኃላፊ፤
፬ኛ. ሊ/ኅሩያን ባዩ ተዘራ ከአዲስ ከተማ ቂርቆስ ልደታ ክፍለ ከተማ ቤተክህነት የሰንበት ትምህር ቤቶች ክፍል ኀላፊ ወደ የሀ/ስብከቱ የሰው ኀይል አስተዳደር ዋና ክፍል ኀላፊ፤
፭ኛ. መ/ሰላም ጽጌ ከበረ ከጠቅላይ ቤተክህነት ሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ምክትል ኀላፊ ወደ አዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የማኅበራት ማደራጃ ዋና ክፍል ኀላፊ፤
፮ኛ. ሊቀ ሥልጣናት አባ ጥዑመ ልሳን ኪዳነ ማርያም ከመንበረ መንግሥት ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን አስተዳዳሪነት ወደ አዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ገዳማት ዋና ክፍል ኀላፊ፤
፯ኛ. መ/ስብሐት ዐቢይ ዘለቀ ከቤቶችና ሕንጻዎች አስተዳደርና ልማት ድርጅት ወደ አዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ተዛውረው የሀገረ ስብከቱ ብፁዕ ሊቀ ጳጳስ ልዩ ጸሐፊ ሆነው እንዲሠሩ ተመድበዋል።
መረጃው፡-የኢ/ኦ/ተ/ ቤተ ክርስቲያን የሕዝብ ግንኘነት መምሪያ ነው፡፡
❤3
Forwarded from ዮሐንስ ጌታቸው
+++#የባሕራን_ደብዳቤ#+++
በሰኔ 12 ታላቁ መልአክ ቅዱስ ሚካኤል ከሚከበርበት ምክንያቶች ውስጥ አንዱ የባሕራንን ደብዳቤ የሚመለከት ነው። ባሕራን መመጽወትና መዘከር ጽኑዕ አገልግሎቱ ከኾነ አባት የተወለደ ነው። እናቱም በዚያ መልካም ግብር ተጸምዳ ትኖር የነበረች ናት። አባትና እናት በአስተሳሰባቸው አንድ ኾነው እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኝ ሥራ ሲሠሩ ፡ ጎረቤታቸው ያለው ክፉ ባለ ጸጋ የመልካምነት ክንፉን በቅምጥልነት ሕይወቱ ስላጣው፡ በአስተሳሰብ ልዕልና ከመገኘት ይልቅ መሬታዊ በኾነ ክፋት ቆሳስሏል። የቅዱስ ሚካኤልን መክበር በፍጹም አካሉ፣ በፍጹም ነፍሱና በፍጹም ልቡናው ተጸይፏል። ይህ ሰው ከቤቱ ደጅ ያለውን የመልካምነት ትምህርት ቤት (የባሕራንን ቤተሰብ ሕይወት) ለመማር ባለመፈለግ ደንቁሯል! ይህ በእጅጉ አሳዛኝ የኾነ ሕይወት ነው። የተሰጠውን ሀብት አለመጠቀሙ! ያሳዝናል፤ ያስቆጫልም! ምናልባትም የእኛ ምሳሌ ኾኖ እርሱ ራሱ በአኗኗሩ እንዳይገስጸን እንመርምር!
ባሕራን ስሙን የወረሰው ከተገኘበት ባሕር የተነሣ ነው። ከባሕር ተገኝቶ የተገኘባትን ባሕር በስሙ ተሸክሟት ኖረ። ተወዳጅች ሆይ የተገኘንባትን ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ተሸክመናት ይኾን? ወይስ አኹንም በላዩአ ተንሳፈን እየተጓዝን። ማለትም ተኝተንባት! ንስሓ ላይ ተኝተን፤ ቅድስና ላይ ተኝተን፤ ምጽዋዕት ላይ ተኝተን፤ ክብረ መላእክት ላይ ተኝተን፤ ፈቃደ እግዚአብሔርና ሕገ እግዚአብሔር ላይ ተኝተን የምንጓዘው እስከ መቼ?! ባሕራንን ባሕራን ብሎ የሰየመው የበጎች ጠባቂ እረኛ የነበረው አሳዳጊው ነው። ክርስቲያኖች የኾነውን እኛንም ክርስቲያን ያሰኘን ስለ እኛ የቅድስት ድንግል ማርያምን ፍጹም ሥጋና ነፍስ ነሥቶ በተዋሕዶ ሰው የኾነው ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። ከእርሱ ፈቃድ መውጣት ክርስትናን ማጣት መኾኑን ልብ ይሏል።
ከዕለታት አንድ ቀን ባሕራን የጨካኙ ጎረቤታቸውን ሀብት ንብረት የሚወርስ መኾኑ በእግዚአብሔር መልአክ ተነገረ። ከተወሰኑ ጊዜያት በኋላ የባሕራን አባት ሞተ። ባሕራንም የባለ ጸጋውን ሀብት የሚረከብ መኾኑን ባለጸጋው እንዲያውቅ እግዚአብሔር ፈቀደ። ሀብቱ የተሰጠው እንዲጠቀምበት ነበራ! በእጃችን ያለው ገንዘብ እንደ እውነቱ ከኾነ እኛ ጋር ያስቀመጠው የእግዚአብሔር ነው። የተሰጠንን ቍሳዊ ሀብት በፍትሐዊነትና እግዚአብሔር በሚፈቅደው መንገድ ካልተጠቀምን የሚወሰድብን መኾኑን ልብ እንበል! አስተውሉ!እኛ ራሳችን የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ መኾናችን ከገባን ሀብት ንብረታችንማ እንዴት የእርሱ አይኾን! አብርሃምን ባለ ጸጋ ያደረገው በተሰጠው ነገር ኹሉ በቅንነት እግዚአብሔርን ማገልገሉ መኾኑን አንድም ከባለ ጸጋው ከእግዚአብሔር ጋር ተስማምቶ መኖሩ መኾኑን ልብ ይሏል። ባለ ጸጋው ከባሕራን እናት ልጇን የሚንከባከብ መስሎ ተረከበው፤ ወደ ባሕርም በሳጥን አድርጎ አስወረወረው። ከዚያን ባሕራንን ባሕራን ባለው በግ ጠባቂ ባሕራን ባሕር ዳር ላይ ተገኘ። ባሕራንም ተባለ!
ከ20 ዓመት በኋላ ባለጸጋው መንገድ ሲሄድ ባሕራን ካለበት ድንገት ደረሰ። ከአሳዳጊው ታሪኩን ሲሰማ ቀድሞ ያስጣለው መኾኑን ተረዳ፤ የሞት ደብዳቤ አስይዞ ባሕራንን ላከው። የራሱን የሞት ደብዳቤ ይዞ የሚጓዘው ባሕራን ቅዱስ ሚካኤል ተገልጦ ወደ ሕይወት ደብዳቤ ገለበጠለት። ብዙዎቻችን ባለማወቃችን ምክንያት የሞት ደብዳቤ ይዘን ወደ ሲዖል እንፈጥናለን። በጭካኔ፣ በጥላቻ፣ ባልተገባ ትችት፣ በሐሜት፣ በሌሎች ሰዎች ውድቀት በመደሰትና በመሳሰሉት የሞት ደብዳቤ ወደ ጥፋት እንፈጥናለን። የዕለት ዕለት የሕይወት መርሐችን ወደ ሞት የሚወስድ እንጂ ወደ ሕይወት የሚያደርስ አይመስልም። ምክንያቱም ዕለት ዕለት እንደ ምግብ ኃጢአትን እየደጋገምን እንፈጽማለንና። እንግዲህ መልአኩ የልቡናችንን ሐሳብ በምልጃው ባያቀናልን ኖሮ እየገሠገሠን ያለነው ወደ ዘረኝነት ሞት፣ ወደ ድንቁርናና ስንፍና ሞት፣ ወደ ቅናትና ትዕቢት ሞት መኾኑን ልብ እንበል!
ቅዱስ ሚካኤል በኃጢአታችን ምክንያት ወደ ተስፋ መቍረጥ የምንጓዘውን ከመንገድ ያግኘን። ከሞት አፋፍ በምልጃው ይታደገን። ወደ ሕይወት የምንገባበትን መልካም ሥራ በሰውነታችን ውስጥ ያለምልምልን። እንግዲህ ያ የባሕራንን ደብዳቤ የሚቀለበስልን በምንሠራው ሥራ አማካኝነት መኾኑን እንረዳ፤ ወደ ጽድቅ እንሩጥ፤ ከጥላቻ ሰውነታችንን እናላቅቅ! ጣዕሙ እጅግ ደስ የሚያሰኘውን የፍቅር ደብዳቤ ከልቡናችን መዝገብ አጽፈን፤ ወደ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን እንገሥግስ። በሕይወታችን ሊገጥሙን የሚችሉትን መሰናክሎች እኛ ባናያቸውም እንኳን መልአኩ ቅዱስ ሚካኤል ይለውጥልናል። ሕይወታችንን በለመለመ የውኃ መስክ አጠገብ የበቀለች ተክል አድርጎ ያሳምረዋል። እንግዲህ የባሕራን ደብዳቤ መነሻዋ ጥፋት መድረሻዋ ግን ሕይወት ኾኗል። አምላካችን እግዚአብሔርም በሊቀ መላእክት በቅዱስ ሚካኤል ምልጃ የኃጢአት ደብዳቤያችንን ሰርዞ የጽድቅ ያድርግልን አሜን!
በሰኔ 12 ታላቁ መልአክ ቅዱስ ሚካኤል ከሚከበርበት ምክንያቶች ውስጥ አንዱ የባሕራንን ደብዳቤ የሚመለከት ነው። ባሕራን መመጽወትና መዘከር ጽኑዕ አገልግሎቱ ከኾነ አባት የተወለደ ነው። እናቱም በዚያ መልካም ግብር ተጸምዳ ትኖር የነበረች ናት። አባትና እናት በአስተሳሰባቸው አንድ ኾነው እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኝ ሥራ ሲሠሩ ፡ ጎረቤታቸው ያለው ክፉ ባለ ጸጋ የመልካምነት ክንፉን በቅምጥልነት ሕይወቱ ስላጣው፡ በአስተሳሰብ ልዕልና ከመገኘት ይልቅ መሬታዊ በኾነ ክፋት ቆሳስሏል። የቅዱስ ሚካኤልን መክበር በፍጹም አካሉ፣ በፍጹም ነፍሱና በፍጹም ልቡናው ተጸይፏል። ይህ ሰው ከቤቱ ደጅ ያለውን የመልካምነት ትምህርት ቤት (የባሕራንን ቤተሰብ ሕይወት) ለመማር ባለመፈለግ ደንቁሯል! ይህ በእጅጉ አሳዛኝ የኾነ ሕይወት ነው። የተሰጠውን ሀብት አለመጠቀሙ! ያሳዝናል፤ ያስቆጫልም! ምናልባትም የእኛ ምሳሌ ኾኖ እርሱ ራሱ በአኗኗሩ እንዳይገስጸን እንመርምር!
ባሕራን ስሙን የወረሰው ከተገኘበት ባሕር የተነሣ ነው። ከባሕር ተገኝቶ የተገኘባትን ባሕር በስሙ ተሸክሟት ኖረ። ተወዳጅች ሆይ የተገኘንባትን ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ተሸክመናት ይኾን? ወይስ አኹንም በላዩአ ተንሳፈን እየተጓዝን። ማለትም ተኝተንባት! ንስሓ ላይ ተኝተን፤ ቅድስና ላይ ተኝተን፤ ምጽዋዕት ላይ ተኝተን፤ ክብረ መላእክት ላይ ተኝተን፤ ፈቃደ እግዚአብሔርና ሕገ እግዚአብሔር ላይ ተኝተን የምንጓዘው እስከ መቼ?! ባሕራንን ባሕራን ብሎ የሰየመው የበጎች ጠባቂ እረኛ የነበረው አሳዳጊው ነው። ክርስቲያኖች የኾነውን እኛንም ክርስቲያን ያሰኘን ስለ እኛ የቅድስት ድንግል ማርያምን ፍጹም ሥጋና ነፍስ ነሥቶ በተዋሕዶ ሰው የኾነው ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። ከእርሱ ፈቃድ መውጣት ክርስትናን ማጣት መኾኑን ልብ ይሏል።
ከዕለታት አንድ ቀን ባሕራን የጨካኙ ጎረቤታቸውን ሀብት ንብረት የሚወርስ መኾኑ በእግዚአብሔር መልአክ ተነገረ። ከተወሰኑ ጊዜያት በኋላ የባሕራን አባት ሞተ። ባሕራንም የባለ ጸጋውን ሀብት የሚረከብ መኾኑን ባለጸጋው እንዲያውቅ እግዚአብሔር ፈቀደ። ሀብቱ የተሰጠው እንዲጠቀምበት ነበራ! በእጃችን ያለው ገንዘብ እንደ እውነቱ ከኾነ እኛ ጋር ያስቀመጠው የእግዚአብሔር ነው። የተሰጠንን ቍሳዊ ሀብት በፍትሐዊነትና እግዚአብሔር በሚፈቅደው መንገድ ካልተጠቀምን የሚወሰድብን መኾኑን ልብ እንበል! አስተውሉ!እኛ ራሳችን የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ መኾናችን ከገባን ሀብት ንብረታችንማ እንዴት የእርሱ አይኾን! አብርሃምን ባለ ጸጋ ያደረገው በተሰጠው ነገር ኹሉ በቅንነት እግዚአብሔርን ማገልገሉ መኾኑን አንድም ከባለ ጸጋው ከእግዚአብሔር ጋር ተስማምቶ መኖሩ መኾኑን ልብ ይሏል። ባለ ጸጋው ከባሕራን እናት ልጇን የሚንከባከብ መስሎ ተረከበው፤ ወደ ባሕርም በሳጥን አድርጎ አስወረወረው። ከዚያን ባሕራንን ባሕራን ባለው በግ ጠባቂ ባሕራን ባሕር ዳር ላይ ተገኘ። ባሕራንም ተባለ!
ከ20 ዓመት በኋላ ባለጸጋው መንገድ ሲሄድ ባሕራን ካለበት ድንገት ደረሰ። ከአሳዳጊው ታሪኩን ሲሰማ ቀድሞ ያስጣለው መኾኑን ተረዳ፤ የሞት ደብዳቤ አስይዞ ባሕራንን ላከው። የራሱን የሞት ደብዳቤ ይዞ የሚጓዘው ባሕራን ቅዱስ ሚካኤል ተገልጦ ወደ ሕይወት ደብዳቤ ገለበጠለት። ብዙዎቻችን ባለማወቃችን ምክንያት የሞት ደብዳቤ ይዘን ወደ ሲዖል እንፈጥናለን። በጭካኔ፣ በጥላቻ፣ ባልተገባ ትችት፣ በሐሜት፣ በሌሎች ሰዎች ውድቀት በመደሰትና በመሳሰሉት የሞት ደብዳቤ ወደ ጥፋት እንፈጥናለን። የዕለት ዕለት የሕይወት መርሐችን ወደ ሞት የሚወስድ እንጂ ወደ ሕይወት የሚያደርስ አይመስልም። ምክንያቱም ዕለት ዕለት እንደ ምግብ ኃጢአትን እየደጋገምን እንፈጽማለንና። እንግዲህ መልአኩ የልቡናችንን ሐሳብ በምልጃው ባያቀናልን ኖሮ እየገሠገሠን ያለነው ወደ ዘረኝነት ሞት፣ ወደ ድንቁርናና ስንፍና ሞት፣ ወደ ቅናትና ትዕቢት ሞት መኾኑን ልብ እንበል!
ቅዱስ ሚካኤል በኃጢአታችን ምክንያት ወደ ተስፋ መቍረጥ የምንጓዘውን ከመንገድ ያግኘን። ከሞት አፋፍ በምልጃው ይታደገን። ወደ ሕይወት የምንገባበትን መልካም ሥራ በሰውነታችን ውስጥ ያለምልምልን። እንግዲህ ያ የባሕራንን ደብዳቤ የሚቀለበስልን በምንሠራው ሥራ አማካኝነት መኾኑን እንረዳ፤ ወደ ጽድቅ እንሩጥ፤ ከጥላቻ ሰውነታችንን እናላቅቅ! ጣዕሙ እጅግ ደስ የሚያሰኘውን የፍቅር ደብዳቤ ከልቡናችን መዝገብ አጽፈን፤ ወደ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን እንገሥግስ። በሕይወታችን ሊገጥሙን የሚችሉትን መሰናክሎች እኛ ባናያቸውም እንኳን መልአኩ ቅዱስ ሚካኤል ይለውጥልናል። ሕይወታችንን በለመለመ የውኃ መስክ አጠገብ የበቀለች ተክል አድርጎ ያሳምረዋል። እንግዲህ የባሕራን ደብዳቤ መነሻዋ ጥፋት መድረሻዋ ግን ሕይወት ኾኗል። አምላካችን እግዚአብሔርም በሊቀ መላእክት በቅዱስ ሚካኤል ምልጃ የኃጢአት ደብዳቤያችንን ሰርዞ የጽድቅ ያድርግልን አሜን!
❤5