🔴ብታምኑም ባታምኑም ይሄ ፈረንሳይ ነው🔴
የግብፅ ኦርቶዶክስ እጅግ የተሳካ ኦርትዶክሳዊ የወንጌል አገልግሎት በፈረንሳይ እያካሄደች ነው ። #ወደ_17_ሺህ የሚጠጉ ፈረንሳዊያን ባለፈው ዓመት በጥምቀት ወደ አማናዊቱ ቤተክርስቲያን መጨመራቸው ይታወቃል ።
➨ድንግል ማርያም በፈረንሳይ በተዋህዶ ልጇች ከበረች♥️
➨የፓሪስ እና የሰሜን ፈረንሳይ ሀገረ ስብከት የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ዓመታዊ ክብረ በዓል በቅድስት ድንግል ማርያም ካቴድራል እና በሊቀ መላእክት ሩፋኤል (የሀገረ ስብከቱ መንበር) ድራቪ። የእየሩሳሌም እና የቅርቡ ምስራቅ መንበር ሜትሮፖሊታን ብፁዕ አቡነ አንቶኒዮስ ከጸጋው ጳጳስ ማ ጋር ተሳትፈዋል።
©ayu prince fb
የግብፅ ኦርቶዶክስ እጅግ የተሳካ ኦርትዶክሳዊ የወንጌል አገልግሎት በፈረንሳይ እያካሄደች ነው ። #ወደ_17_ሺህ የሚጠጉ ፈረንሳዊያን ባለፈው ዓመት በጥምቀት ወደ አማናዊቱ ቤተክርስቲያን መጨመራቸው ይታወቃል ።
➨ድንግል ማርያም በፈረንሳይ በተዋህዶ ልጇች ከበረች♥️
➨የፓሪስ እና የሰሜን ፈረንሳይ ሀገረ ስብከት የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ዓመታዊ ክብረ በዓል በቅድስት ድንግል ማርያም ካቴድራል እና በሊቀ መላእክት ሩፋኤል (የሀገረ ስብከቱ መንበር) ድራቪ። የእየሩሳሌም እና የቅርቡ ምስራቅ መንበር ሜትሮፖሊታን ብፁዕ አቡነ አንቶኒዮስ ከጸጋው ጳጳስ ማ ጋር ተሳትፈዋል።
©ayu prince fb
❤3
ከመ ትንሣኤ ወልዳ👏
ስለ እመቤታችን ትንሣኤና ዕርገት ከመ ትንሣኤ ወልዳ የተባለውን ይዘው ብዙዎች ብዙ ሐሳብ ይሰጣሉ በተለይም ሱባዔው በ14 አልቆ በ16 ከማክበራችን ጋር ተያይዞ በተቀበረች በ3ኛው ቀን እንደተነሣች የሚያስቡ አሉ በዚህም ዙሪያ በተቀበረች በ3ኛው ቀን ተነሣች የሚል ሐሳብ የያዙ መጻሕፍቶች አሉ አብዛኞች ሊቃውንትና መተርጉማን ግን የሚናገሩትና የሚያስተምሩት በ14 ሐዋርያት ሥጋዋን ተቀብለው በክብር ከቀበሯት በኋላ ዕለቱኑ ቶማስ በደመና ሲመለስ እመቤታችን በይባቤ መላእክት ስታርግ አገኛት መች? በ14 ይህንንም ቶማስ ተመልሶ ለሐዋርያት ካሳያቸው በኋላ እነርሱም ቶማስ ያየውን ትንሣኤዋንና ዕርገቷን ለማየት በዓመቱ ሱባዔ ገቡ
በ14 ሁለት ሱባዔ ቢጨርሱም እመቤታችን የተገለጸችላቸው ግን በ16 ስለሆነ በዓለ ዕርገቷን ልክ እንደ ሐዋርያት በ16 እናከብራለን እንጂ የተነሣችውና ያረገችው በ14 ነው ብለዋል
ትንሣኤዋ ከመ ትንሣኤ ወልዳ መባሉ ግን
1ኛ የተፈጸመበት ቀን ዕለተ ሰንበት በመሆኑ ዕለቱ እንደ ጌታ ትንሣኤ አማናዊው ትንሣኤ በተፈጸመበትና ትንሣኤ ዘጉባኤ የሚፈጸምበት ዕለትን ሳይለቅ በዕለተ ሰንበት በመሆኑ
እመቤታችን ያረፈችው ጥር 21 ቀን ዕለተ እሑድ እንደነበር ታሪኳ ይናገራል ቀኑ ሲቆጠር ደግሞ ነሐሴ 14 በዕለተ ሰንበት ሲውል ነሐሴ 16 ቀን ግን ማክሰኞ ይሆናል ስለዚህም የተነሣችው በተቀበረች በሦስተኛው ቀን በ16 ቀን ነው ካልን ከመ ትንሣኤ ወልዳ የሚለውን በዕለተ ሰንበት መነሣቷን ይቀይረዋል
2ኛ የክብርና ብርሃናዊ ትንሣኤ መሆኑ እንደነ አልዓዛር ዳግም ምት ያለበት ሳይሆን በትንሣኤ ዘጉባኤ እንደምንነሣው ያለ ክርስቶስ በትንሣኤው የሰጠን የክብር ትንሣኤን በመነሣቷ
3ኛ እንደ ልጇ ትንሣኤ ዕርገት የሚከተለውና ወደ መንግሥተ ሰማያት ማረግ ያለበት ትንሣኤ በመሆኑና ወደ መንግሥተ ሰማያት ያረገችበት በመሆኑ ከመ ትንሣኤ ወልዳ አለ እንጂ ትንሣኤና ዕርገቷ ልክ ጌታ በተቀበረ በ3ኛው ቀን እንደተነሣ ያለ አይደለም ያ ቢሆንማ ጥንተ ትንሣኤዋ እሑድን ትቶ ማክሰኞ ይሆን ነበር
ዕርገቷም አርባ ቀን በጠበቀ ነበር ብለው መተርጉማን አብራርተው ተናግረዋል።
በተለይ በጥሩ ስንክሳር ላይ ከቀበሯት በኋላ ሦስት ቀን በዚያ ቆዩ የሚለውን ይዘው በሦስተኛው ቀን ነው የተነሣችው ትንሣኤዋና ዕርገቷ የሆነው በ16 ነው የሚሉም አሉ ነገር ግን በዚያ ሦስት ቀን ቆዩ አለ እንጂ የእርሷን ዕርገት በዚያ ቀን ነው አላለም ቶማስ ወደ እነርሱ እስኪመጣ አላወቁም ነበር
ያም ሆነ ይህ ቀኑ ሳያጣላን እኛም ትንሣኤዋና ዕርገቷ ለሐዋርያት ሁሉ በተገለጠበትና ጌታ እርሷን ያገናኛቸው እርሱም የተገለጠላቸው በ16 መሆኑ እኛም በ16 እንድናከብር ፈቃዱ ቢሆን ነው ብለን በፍጹም እምነትና በታላቅ ሐሴት ነሐሴ 16 ልክ እንደ ሐዋርያት በዓለ ትንሣኤዋንና ዕርገቷን እናከብራለን
የእመቤታችን ረድኤት በረከቷ ይደርብን ጸጋዋ ይከልለን👏
እንኳን አደረሳችሁ❤
©መጋቤ ሐዲስ ዘለዓለም ሐሳቤ እንደጻፉት
ስለ እመቤታችን ትንሣኤና ዕርገት ከመ ትንሣኤ ወልዳ የተባለውን ይዘው ብዙዎች ብዙ ሐሳብ ይሰጣሉ በተለይም ሱባዔው በ14 አልቆ በ16 ከማክበራችን ጋር ተያይዞ በተቀበረች በ3ኛው ቀን እንደተነሣች የሚያስቡ አሉ በዚህም ዙሪያ በተቀበረች በ3ኛው ቀን ተነሣች የሚል ሐሳብ የያዙ መጻሕፍቶች አሉ አብዛኞች ሊቃውንትና መተርጉማን ግን የሚናገሩትና የሚያስተምሩት በ14 ሐዋርያት ሥጋዋን ተቀብለው በክብር ከቀበሯት በኋላ ዕለቱኑ ቶማስ በደመና ሲመለስ እመቤታችን በይባቤ መላእክት ስታርግ አገኛት መች? በ14 ይህንንም ቶማስ ተመልሶ ለሐዋርያት ካሳያቸው በኋላ እነርሱም ቶማስ ያየውን ትንሣኤዋንና ዕርገቷን ለማየት በዓመቱ ሱባዔ ገቡ
በ14 ሁለት ሱባዔ ቢጨርሱም እመቤታችን የተገለጸችላቸው ግን በ16 ስለሆነ በዓለ ዕርገቷን ልክ እንደ ሐዋርያት በ16 እናከብራለን እንጂ የተነሣችውና ያረገችው በ14 ነው ብለዋል
ትንሣኤዋ ከመ ትንሣኤ ወልዳ መባሉ ግን
1ኛ የተፈጸመበት ቀን ዕለተ ሰንበት በመሆኑ ዕለቱ እንደ ጌታ ትንሣኤ አማናዊው ትንሣኤ በተፈጸመበትና ትንሣኤ ዘጉባኤ የሚፈጸምበት ዕለትን ሳይለቅ በዕለተ ሰንበት በመሆኑ
እመቤታችን ያረፈችው ጥር 21 ቀን ዕለተ እሑድ እንደነበር ታሪኳ ይናገራል ቀኑ ሲቆጠር ደግሞ ነሐሴ 14 በዕለተ ሰንበት ሲውል ነሐሴ 16 ቀን ግን ማክሰኞ ይሆናል ስለዚህም የተነሣችው በተቀበረች በሦስተኛው ቀን በ16 ቀን ነው ካልን ከመ ትንሣኤ ወልዳ የሚለውን በዕለተ ሰንበት መነሣቷን ይቀይረዋል
2ኛ የክብርና ብርሃናዊ ትንሣኤ መሆኑ እንደነ አልዓዛር ዳግም ምት ያለበት ሳይሆን በትንሣኤ ዘጉባኤ እንደምንነሣው ያለ ክርስቶስ በትንሣኤው የሰጠን የክብር ትንሣኤን በመነሣቷ
3ኛ እንደ ልጇ ትንሣኤ ዕርገት የሚከተለውና ወደ መንግሥተ ሰማያት ማረግ ያለበት ትንሣኤ በመሆኑና ወደ መንግሥተ ሰማያት ያረገችበት በመሆኑ ከመ ትንሣኤ ወልዳ አለ እንጂ ትንሣኤና ዕርገቷ ልክ ጌታ በተቀበረ በ3ኛው ቀን እንደተነሣ ያለ አይደለም ያ ቢሆንማ ጥንተ ትንሣኤዋ እሑድን ትቶ ማክሰኞ ይሆን ነበር
ዕርገቷም አርባ ቀን በጠበቀ ነበር ብለው መተርጉማን አብራርተው ተናግረዋል።
በተለይ በጥሩ ስንክሳር ላይ ከቀበሯት በኋላ ሦስት ቀን በዚያ ቆዩ የሚለውን ይዘው በሦስተኛው ቀን ነው የተነሣችው ትንሣኤዋና ዕርገቷ የሆነው በ16 ነው የሚሉም አሉ ነገር ግን በዚያ ሦስት ቀን ቆዩ አለ እንጂ የእርሷን ዕርገት በዚያ ቀን ነው አላለም ቶማስ ወደ እነርሱ እስኪመጣ አላወቁም ነበር
ያም ሆነ ይህ ቀኑ ሳያጣላን እኛም ትንሣኤዋና ዕርገቷ ለሐዋርያት ሁሉ በተገለጠበትና ጌታ እርሷን ያገናኛቸው እርሱም የተገለጠላቸው በ16 መሆኑ እኛም በ16 እንድናከብር ፈቃዱ ቢሆን ነው ብለን በፍጹም እምነትና በታላቅ ሐሴት ነሐሴ 16 ልክ እንደ ሐዋርያት በዓለ ትንሣኤዋንና ዕርገቷን እናከብራለን
የእመቤታችን ረድኤት በረከቷ ይደርብን ጸጋዋ ይከልለን👏
እንኳን አደረሳችሁ❤
©መጋቤ ሐዲስ ዘለዓለም ሐሳቤ እንደጻፉት
+ ማርያማዊ ደስታ +
ድንግል ማርያም ‘መንፈሴም በመድኃኒቴ በእግዚአብሔር ደስ ይላታል’ አለች፡፡ የድንግሊቱን ጥበብ ተመልከቱ፡፡ ‘በመልአክ በመመስገኔ ደስ ይለኛል ፣ ከሴቶች ሁሉ የተባረከች በመባሌ ደስ ይለኛል ፣ አምላክን ለመውለድ በመመረጤ ደስ ይለኛል’ አላለችም፡፡ የእርስዋ የደስታ ምንጭ ከእግዚአብሔር የተሠጣት ነገር ሳይሆን ራሱ እግዚአብሔር ነው፡፡
እግዚአብሔር የደስታህ ምንጭ ከሆነ በሕይወትህ ምንም ነገር ቢከሰት ደስታህን አይነካብህም፡፡ ድንግሊቱ ከሴቶች ሁሉ የተባረከች በመሆንዋ ደስ ያላት ብትሆን ኖሮ ከዚያ በኋላ ከሴቶች ሁሉ የተንከራተተች ፣ ከሴቶች ሁሉ ያዘነች ፣ ከሴቶች ሁሉ በዲያብሎስና ጭፍሮቹ የተጠላች ፣ በሔሮድስ በአይሁድ የተነቀፈች መሆንዋን ስታይ ደስታዋ በጠፋ ነበር፡፡
እርስዋ ግን ደስታዋ የመነጨው ከአምላክዋ ብቻ ነበር፡፡ ፍጹም የሆነ ውስጣዊ ደስታን ማግኘት የሰው ልጅ ትልቅ ምኞቱ ነው፡፡ ሰዎች ደስታን ፍለጋ ብዙ ይደክማሉ፡፡ ድንግሊቱ ግን የደስታ ሁሉ ምንጭ የሆነው አምላክ ከእርስዋ ጋር ነውና በፍጹም ደስታ ደስ ይላታል፡፡ የድንግል ማርያም ደስታ ልጅዋ ‘ደስታችሁን የሚወስድባችሁ የለም’ ያለው ዓይነት ደስታ ነበር፡፡ ዮሐ. ፲፮፥፳፪
‘ተፈሥሒ ፍስሕት’ (ደስተኛይቱ ሆይ ደስ ይበልሽ) ፤ ሙኃዘ
ፍሥሓ (የደስታ መፍሰሻ ሆይ) ብለን የምናመሰግናት እመቤታችን ከማንም የሚበልጥ ደስታ በእርስዋ ዘንድ ነበረ፡፡ ደስተኛ የነበረችው በምድር በነበራት ቆይታ የሚያስደስት ኑሮ ስለነበራት አይደለም፡፡ እንደ እርስዋ የተሰደደ ፣ ያለቀሰ ፣ የተጨነቀ ፍጡር የለም፡፡ እንደ ክርስቶስ መከራ የተቀበለ እንደሌለ እንደ ድንግል ማርያምም ያዘነ የለም፡፡ እርስዋ ግን ለሌሎች የሚተርፍ ወደ ኤልሳቤጥ የሚሸጋገር ፣ ሆድ ውስጥ ወዳለ
ፅንስ የሚጋባ ጥልቅ ደስታ ነበራት፡፡ ቅዱስ ያሬድ ‘ተፈሢሓ በነፍሳ ፆረቶ በከርሣ’ ‘በነፍስዋ ደስ ተሰኝታ በሆድዋ ተሸከመችው’ እንዳለ እርስዋ የተደሰተችው ሥጋዊ ደስታን አልነበረም፡፡ (ድጓ ዘቅዱስ ገብርኤል )ከመንፈስ ቅዱስ ፍሬዎች አንዱ ደስታ ነውና ቅድስቲቱ ማንም ጋር ያልነበረ ደስታ ነበራት፡፡ ገላ. ፭፥፳፪
በእርግጥም ደስታን ወልዳ ደስ ባይላት ይደንቅ ነበር፡፡ እርስዋ የወለደችው ‘የመላእክት ተድላ ደስታቸው’ ነው ፤ እርስዋ የወለደችው መወለዱ ‘ለሰው ሁሉ ደስታ የሚሆን ታላቅ የምሥራች’ የሚሆን ልጅን አይደለምን?
እግዚአብሔር አብ ‘በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወድደው ልጄ ይህ ነው’ ያለውን አንድያ ልጁን ልጅዋ እንዲሆን ሠጥቶአታልና እርስዋም በምትወደው በልጅዋ ደስ ይላታል፡፡ ንጉሥ ዳዊት ‘ወደ እግዚአብሔር ቤት እንሒድ ባሉኝ ጊዜ ደስ አለኝ’ ካለ እግዚአብሔር የዘጠኝ ወር ቤቱ አድርጎ ያደረባት ድንግል ምንኛ ደስ ይላት ይሆን? መወለዱ ሰውና መላእክትን በደስታ እንዲዘምሩ ካደረገ የወለደችው ድንግል ምንኛ ደስ ይላት ይሆን?
ጌታ ለሐዋርያቱ ‘ስማችሁ በሰማይ ስለተጻፈ ደስ ይበላችሁ’ ካላቸው እግዚአብሔር ሁለተኛ ሰማዩ አድርጎ ዙፋን ያደረጋት በምድር ያለች የጠፈር ባልንጀራ ፣ የአርያም እኅት ማርያም ምንኛ ደስ ይላት ይሆን?
እመቤታችን ሆይ እባክሽን በአንቺ ላይ ከፈሰሰው ደስታ ቀድተሽ ወደ እኛ ወደ ኀዘንተኞቹ አፍስሺ፡፡ ኖኅ እንደ ላካት ርግብ የመከራችን ውኃ ጎደለ ብለሽ ታበሥሪን ዘንድ ወደ እኛ ነይ ‘ንዒ ርግብየ ትናዝዝኒ ኀዘነ ልብየ’ ‘ርግቤ ሆይ ከኀዘኔ ታረጋጊኝ ዘንድ ነይ’ እንዳለ ሊቁ፡፡
ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
ለበዓለ ዕርገታ ዝክር
ከብርሃን እናት ገጾች የተቆረሰ
ፎቶ :- የ2017 ደብረ ታቦር ከሞገስነ ክቡር የኔታ ሊቀ ጠበብት ሐረገ ወይን አገዘ ጋር
ድንግል ማርያም ‘መንፈሴም በመድኃኒቴ በእግዚአብሔር ደስ ይላታል’ አለች፡፡ የድንግሊቱን ጥበብ ተመልከቱ፡፡ ‘በመልአክ በመመስገኔ ደስ ይለኛል ፣ ከሴቶች ሁሉ የተባረከች በመባሌ ደስ ይለኛል ፣ አምላክን ለመውለድ በመመረጤ ደስ ይለኛል’ አላለችም፡፡ የእርስዋ የደስታ ምንጭ ከእግዚአብሔር የተሠጣት ነገር ሳይሆን ራሱ እግዚአብሔር ነው፡፡
እግዚአብሔር የደስታህ ምንጭ ከሆነ በሕይወትህ ምንም ነገር ቢከሰት ደስታህን አይነካብህም፡፡ ድንግሊቱ ከሴቶች ሁሉ የተባረከች በመሆንዋ ደስ ያላት ብትሆን ኖሮ ከዚያ በኋላ ከሴቶች ሁሉ የተንከራተተች ፣ ከሴቶች ሁሉ ያዘነች ፣ ከሴቶች ሁሉ በዲያብሎስና ጭፍሮቹ የተጠላች ፣ በሔሮድስ በአይሁድ የተነቀፈች መሆንዋን ስታይ ደስታዋ በጠፋ ነበር፡፡
እርስዋ ግን ደስታዋ የመነጨው ከአምላክዋ ብቻ ነበር፡፡ ፍጹም የሆነ ውስጣዊ ደስታን ማግኘት የሰው ልጅ ትልቅ ምኞቱ ነው፡፡ ሰዎች ደስታን ፍለጋ ብዙ ይደክማሉ፡፡ ድንግሊቱ ግን የደስታ ሁሉ ምንጭ የሆነው አምላክ ከእርስዋ ጋር ነውና በፍጹም ደስታ ደስ ይላታል፡፡ የድንግል ማርያም ደስታ ልጅዋ ‘ደስታችሁን የሚወስድባችሁ የለም’ ያለው ዓይነት ደስታ ነበር፡፡ ዮሐ. ፲፮፥፳፪
‘ተፈሥሒ ፍስሕት’ (ደስተኛይቱ ሆይ ደስ ይበልሽ) ፤ ሙኃዘ
ፍሥሓ (የደስታ መፍሰሻ ሆይ) ብለን የምናመሰግናት እመቤታችን ከማንም የሚበልጥ ደስታ በእርስዋ ዘንድ ነበረ፡፡ ደስተኛ የነበረችው በምድር በነበራት ቆይታ የሚያስደስት ኑሮ ስለነበራት አይደለም፡፡ እንደ እርስዋ የተሰደደ ፣ ያለቀሰ ፣ የተጨነቀ ፍጡር የለም፡፡ እንደ ክርስቶስ መከራ የተቀበለ እንደሌለ እንደ ድንግል ማርያምም ያዘነ የለም፡፡ እርስዋ ግን ለሌሎች የሚተርፍ ወደ ኤልሳቤጥ የሚሸጋገር ፣ ሆድ ውስጥ ወዳለ
ፅንስ የሚጋባ ጥልቅ ደስታ ነበራት፡፡ ቅዱስ ያሬድ ‘ተፈሢሓ በነፍሳ ፆረቶ በከርሣ’ ‘በነፍስዋ ደስ ተሰኝታ በሆድዋ ተሸከመችው’ እንዳለ እርስዋ የተደሰተችው ሥጋዊ ደስታን አልነበረም፡፡ (ድጓ ዘቅዱስ ገብርኤል )ከመንፈስ ቅዱስ ፍሬዎች አንዱ ደስታ ነውና ቅድስቲቱ ማንም ጋር ያልነበረ ደስታ ነበራት፡፡ ገላ. ፭፥፳፪
በእርግጥም ደስታን ወልዳ ደስ ባይላት ይደንቅ ነበር፡፡ እርስዋ የወለደችው ‘የመላእክት ተድላ ደስታቸው’ ነው ፤ እርስዋ የወለደችው መወለዱ ‘ለሰው ሁሉ ደስታ የሚሆን ታላቅ የምሥራች’ የሚሆን ልጅን አይደለምን?
እግዚአብሔር አብ ‘በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወድደው ልጄ ይህ ነው’ ያለውን አንድያ ልጁን ልጅዋ እንዲሆን ሠጥቶአታልና እርስዋም በምትወደው በልጅዋ ደስ ይላታል፡፡ ንጉሥ ዳዊት ‘ወደ እግዚአብሔር ቤት እንሒድ ባሉኝ ጊዜ ደስ አለኝ’ ካለ እግዚአብሔር የዘጠኝ ወር ቤቱ አድርጎ ያደረባት ድንግል ምንኛ ደስ ይላት ይሆን? መወለዱ ሰውና መላእክትን በደስታ እንዲዘምሩ ካደረገ የወለደችው ድንግል ምንኛ ደስ ይላት ይሆን?
ጌታ ለሐዋርያቱ ‘ስማችሁ በሰማይ ስለተጻፈ ደስ ይበላችሁ’ ካላቸው እግዚአብሔር ሁለተኛ ሰማዩ አድርጎ ዙፋን ያደረጋት በምድር ያለች የጠፈር ባልንጀራ ፣ የአርያም እኅት ማርያም ምንኛ ደስ ይላት ይሆን?
እመቤታችን ሆይ እባክሽን በአንቺ ላይ ከፈሰሰው ደስታ ቀድተሽ ወደ እኛ ወደ ኀዘንተኞቹ አፍስሺ፡፡ ኖኅ እንደ ላካት ርግብ የመከራችን ውኃ ጎደለ ብለሽ ታበሥሪን ዘንድ ወደ እኛ ነይ ‘ንዒ ርግብየ ትናዝዝኒ ኀዘነ ልብየ’ ‘ርግቤ ሆይ ከኀዘኔ ታረጋጊኝ ዘንድ ነይ’ እንዳለ ሊቁ፡፡
ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
ለበዓለ ዕርገታ ዝክር
ከብርሃን እናት ገጾች የተቆረሰ
ፎቶ :- የ2017 ደብረ ታቦር ከሞገስነ ክቡር የኔታ ሊቀ ጠበብት ሐረገ ወይን አገዘ ጋር
ለብፁዕ አቡነ ቄርሎስ ሊቀ ጳጳስ የምስጋና መርሐ ግብር ተካሄደ።
ነሐሴ 17 ቀን 2017 ዓ.ም(ተ.ሚ.ማ/አዲስ አበባ)
በሰሜን ወሎ መንበረ ጵጵስና ሀገረ ስብከት የወልድያ ከተማ አስተዳደር ቤተክህነት መንበረ ንግሥት ኪዳነ ምሕረት ቤተክርስቲያን ሰበካ ጉባኤ ከደብሩ ሰንበት ትምህርት ቤት ጋር በመተባበር ለብፁዕ አቡነ ቄርሎስ የምስጋና መርሐ ግብር አካሂዷል።
በሰንበት ትምህርት ቤቱ ሀሳብ አመንጭነት ትናንት ነሐሴ 16 ቀን 2017 ዓ.ም በተደረገው በዚሁ የምስጋናና የእውቅና መርሐ ግብር ብፁዕ አቡነ ኤርምያስን ጨምሮ ተጋባዥ እንግዶች፣ የሀገረ ስብከት፣ የወረዳ አብያተክህነት የሥራ ኅላፊች፣ የአድባራት አስተዳዳሪዎች፣ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያንና በርካታ ምእመናን/ት ተገኝተዋል።
በእውቅና መርሐ ግብሩ ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ ሊቀ ጳጳስ ባስተላለፉት ቃለ ምእዳን ብፁዕ አቡነ ቄርሎስ ከልጅነታቸው ጀምሮ ለቤተክርስቲያን አገልግሎት ዋጋ መክፈላቸውን ገልጸዋል።
ከመቅደላ እስከ ብልባላ፣ ከወሎ እስከ ጎንደር፣ ከሸዋ እስከ ወላይታና ሲዳሞ ክፍላተ ሀገር በእግር እየተጓዙ ያሳለፉትን ውጣ ውረድ፣ የቀሰሙትን የቤተክርስቲያን እውቀት፣ በተለያየ የአገልግሎት ደረጃ ያደረጉትን ሃይማኖታዊ ተጋድሎም አስታውሰዋል።
ብፁዕነታቸው ኹሉን ተምረው የተሾሙ በመሆናቸው በቤተክርስቲያኗ አገልግሎት ያስቀመጡት ታሪካዊ አሻራ ሳይደበዝዝ ሕያው ሁኖ እንደሚኖርም ተናግረዋል።
የመሠረ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት የብፁዕነታቸውን የማይረሳ አገልግሎት ኹልጊዜ ለማውሳትና ለሕፃናትና ማእከላውያን የነበራቸው፤ አሁንም ድረስ ያልነጠፈው ፍቅራቸውና ጸሎታቸው እንዲበዛላቸው የሰንበት ትምህርት ቤቱን ባለ ሁለት ወለል ኹለገብ ሕንጻ "ብፁዕ አቡነ ቄርሎስ ኹለገብ ሕንጻ" ተብሎ እንዲጠራ የስም ስጦታ አበርከቷል፡፡
የብፁዕነታቸውን ዐለም አቀፍ ሐዋርያዊ አገልግሎት የሚያወሱ ቅኔ፣ ያሬዳዊ ዝማሬና ሌሎች ዝግጅቶች የቀረቡ ሲሆን ሰንበት ትምህርት ቤቱና ሰበካ ጉባኤው ምእመናንን በማስተባብር ለብፁዕነታቸው ያዘጋጀውን ልዩ ስጦታ በብፁዕ አቡነ ኤርምያስ በኩል አበርክቷል።
ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ ሊቀ ጳጳስ ሰንበት ትምህርት ቤቱ ሀሳቡን በማመንጨት መርሐ ግብሩን በማዘጋጀታቸው አመስግነው ብፁዕ አቡነ ቄርሎስ ከምሥረታ ጀምሮ ሕጻናቱን በመንፈሳዊ ሕይወት ኮትኩተው ለማሳደግ ብዙ የደከሙ በመሆኑና ውለታቸውን ለማስታወስ ሰንበት ትምህርት ቤቱ ተክለ ቄርሎስ ተብሎ እንዲጠራ ሰይመውታል።
©የሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት
ነሐሴ 17 ቀን 2017 ዓ.ም(ተ.ሚ.ማ/አዲስ አበባ)
በሰሜን ወሎ መንበረ ጵጵስና ሀገረ ስብከት የወልድያ ከተማ አስተዳደር ቤተክህነት መንበረ ንግሥት ኪዳነ ምሕረት ቤተክርስቲያን ሰበካ ጉባኤ ከደብሩ ሰንበት ትምህርት ቤት ጋር በመተባበር ለብፁዕ አቡነ ቄርሎስ የምስጋና መርሐ ግብር አካሂዷል።
በሰንበት ትምህርት ቤቱ ሀሳብ አመንጭነት ትናንት ነሐሴ 16 ቀን 2017 ዓ.ም በተደረገው በዚሁ የምስጋናና የእውቅና መርሐ ግብር ብፁዕ አቡነ ኤርምያስን ጨምሮ ተጋባዥ እንግዶች፣ የሀገረ ስብከት፣ የወረዳ አብያተክህነት የሥራ ኅላፊች፣ የአድባራት አስተዳዳሪዎች፣ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያንና በርካታ ምእመናን/ት ተገኝተዋል።
በእውቅና መርሐ ግብሩ ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ ሊቀ ጳጳስ ባስተላለፉት ቃለ ምእዳን ብፁዕ አቡነ ቄርሎስ ከልጅነታቸው ጀምሮ ለቤተክርስቲያን አገልግሎት ዋጋ መክፈላቸውን ገልጸዋል።
ከመቅደላ እስከ ብልባላ፣ ከወሎ እስከ ጎንደር፣ ከሸዋ እስከ ወላይታና ሲዳሞ ክፍላተ ሀገር በእግር እየተጓዙ ያሳለፉትን ውጣ ውረድ፣ የቀሰሙትን የቤተክርስቲያን እውቀት፣ በተለያየ የአገልግሎት ደረጃ ያደረጉትን ሃይማኖታዊ ተጋድሎም አስታውሰዋል።
ብፁዕነታቸው ኹሉን ተምረው የተሾሙ በመሆናቸው በቤተክርስቲያኗ አገልግሎት ያስቀመጡት ታሪካዊ አሻራ ሳይደበዝዝ ሕያው ሁኖ እንደሚኖርም ተናግረዋል።
የመሠረ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት የብፁዕነታቸውን የማይረሳ አገልግሎት ኹልጊዜ ለማውሳትና ለሕፃናትና ማእከላውያን የነበራቸው፤ አሁንም ድረስ ያልነጠፈው ፍቅራቸውና ጸሎታቸው እንዲበዛላቸው የሰንበት ትምህርት ቤቱን ባለ ሁለት ወለል ኹለገብ ሕንጻ "ብፁዕ አቡነ ቄርሎስ ኹለገብ ሕንጻ" ተብሎ እንዲጠራ የስም ስጦታ አበርከቷል፡፡
የብፁዕነታቸውን ዐለም አቀፍ ሐዋርያዊ አገልግሎት የሚያወሱ ቅኔ፣ ያሬዳዊ ዝማሬና ሌሎች ዝግጅቶች የቀረቡ ሲሆን ሰንበት ትምህርት ቤቱና ሰበካ ጉባኤው ምእመናንን በማስተባብር ለብፁዕነታቸው ያዘጋጀውን ልዩ ስጦታ በብፁዕ አቡነ ኤርምያስ በኩል አበርክቷል።
ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ ሊቀ ጳጳስ ሰንበት ትምህርት ቤቱ ሀሳቡን በማመንጨት መርሐ ግብሩን በማዘጋጀታቸው አመስግነው ብፁዕ አቡነ ቄርሎስ ከምሥረታ ጀምሮ ሕጻናቱን በመንፈሳዊ ሕይወት ኮትኩተው ለማሳደግ ብዙ የደከሙ በመሆኑና ውለታቸውን ለማስታወስ ሰንበት ትምህርት ቤቱ ተክለ ቄርሎስ ተብሎ እንዲጠራ ሰይመውታል።
©የሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት
❤1