tgoop.com/yebirihan_lijoch/9937
Last Update:
#እንዲህም_ይፃፋል 👏👏👏👏👏👏👏
#ምድብ_A
ያንተ ፍቅር ደቀነኝ
የራኩትን ስትቀርበኝ
ትርጉማለው ጌታ
መዋለህ ጎልጎታ
ስለ ኃያሉ ፍቅርህ
ምላሽ አጣሁልህ
እርሱ አልሰሰተም ሲሰጠኝ እራሱን
በመስቀል ተሰቅሎ ሲያፈስ ደሙን
ክብሩን ለተወልኝ ክብሬን የምሰጠው
ለሞተልኝ ጌታ ለሱ ነው ምኖረው
በደም ነው የገዛኝ ዋጋየ ትልቅ ነው
የዚህ አለም ስሌት ፍፁም ማይመጥነው
ታዲያ እንዴት ልርሳ ያለብኝን ዕዳ
ቀድሞ የከፈለልኝን እኔ እንዳልጎዳ
ሞት የሚገባኝ ሳለው
ሞቴን በሂወት ቀየርከው
ውዳሴ ይፈልቃል ዛሬም ካንደበቴ
በደሙ ላነጻኝ ለመድሀኒቴ
ዛሬን አየው እየሱስ ጌታዬ
ክበር ንገስ ይኸው ምስጋናዬ
ወደዚህ መምጣትህ በምክንያት እኮነው
ለኔ ለጠፋሁት ህይወት ለመሥጠት ነው
በምህረትህ ታነሳለህ
በፍቅርህ ትደግፋለህ
እውነተኛ ወዳጅ አጣሁኝ እንዳንተ
ነፍሱን አሳልፎ ስለኔ የሰጠ
ደስ ይለኛል እኔ ሁሌም ባንተ ጌታ፤
ያደረከው ሳስብ የዋልከዉ ዉለታ
አረሳውም ውዴ የፋሲው አዳር
የተገለፀበት ለኔ ያለህ ፍቅር
መዳኔ በዋጋ ከፎሎ ከባለጋራዬ
ዳበቢሎስን አስመለጠኝ!
ማነሽ ይሉኛል ሰዎች እርስተውኝ
ግራ እስካጋባ እንዲ ለውጠኸኝ
ሳስበው ደነቀኝ የትናንት ህይወቴን
ለውጠኸው ጌታ መላ ማንነቴን
አይቀልብኝም መገኘትህ
ከኔጋ መዋል ማደርህ
አባብሎ የሚያስተኛ አባት
ለኔ እንዳንተ ማነው ልቤ ያረፈበት
ያኮራል የእሱ መወኔ
ኢየሱስ ይመሰገን አለው አለኝ፡፡
የማይንቀሳቀስ የዘላለም ነዋሪ
የማይዋሽ የተናገረውን አክባሪ።
አንድ እውነት አለ ሁሉን ጉድ ያስኘ
ከሞት የሚያድነው ከበረት ተገኘ
ምህረትህ ገርሞኛል ሌላ ምን እላለሁ
ወድደህ ስላዳንከኝ አመሠግናለሁ
የሞቴን ቀጠሮ የጥፋቴን ሰአት
በእጆቹ ሸሽጎ ጌታዬ አሳለፋት
ከአሁን በኀላ እኔ ጴንጤ ነኝ
ምን እንደነካኝ ሳላውቅ ያኔ ጌታ አገኘኝ
አፅናኝ ነህ ለሃዘኔ አማላጅ ነህ ለፀሎቴ
ውዱ ስጦታዬ እስትንፋስ ህይወቴ
ዶሮ ሳይጮህ 3 ጊዜ የካድኩህ ያኔ
ዶሮ ሳይጮህ አመሰግንሀለው መድህኔ
እንዳላለቅስ እንባ እንዳይወጣ ከዓይኔ
በመስቀል ሞቶ አዳነኝ መድህኔ!!
በደም ነው የገዛኝ ዋጋየ ትልቅ ነው
የዚህ አለም ስሌት ፍፁም ማይመጥነው
ንጋት ተጀምሮ ሰአታት ሲሄዱ ቀኑ ሲሆን ማታ
ልነሳ ልዘጋጅ ጌታን ልጠብቀው እያልኩ ማራናታ
የዚህ አለም ኑሮ በጣም ሰልችቶናል፤
መቼነዉ ምትወስደን የሱስ ናፍቀኸናል።
#ምድብ_A
BY የብርሃን ☀️☀️ ልጆች
Share with your friend now:
tgoop.com/yebirihan_lijoch/9937