tgoop.com/APOSTOLICsuccession/6649
Last Update:
በስመአብ ወ ወልድ ወ መንፈስቅዱስ ፩ አምላክ አሜን
ክርስቶስ ተንስዐ እሙታን
በዐብይ ኃይል ወስልጣን
አሰሮ ለሰይጣን
አግአዞ ለአዳም
ሰላም
እም እዝየሰ
ኮነ
ፍስሀ ወ ሰላም
"ከሲዖል እጅ እታደጋቸዋለሁ ከሞትም እቤዣቸዋለሁ ሞትሆይ ቸነፈርህ ወዴት አለ? ሞትሆይ ማጥፋትህ ወዴት አለ? ርህራሄ ከዓይኔ ተሰወረች" ሆሴ ፲፫፡፲፬
"እንደተናገረ ተነስቷል እንጂ በዚህ የለም" ማቴ ፳፰ እስከ ፍፃሜው ይነበብ
"እርሱ ግን አትደንግጡ የተሰቀለውን የናዝሬቱን ኢየሱስን ትፈልጋላችሁ ተነስቶአል በዚህ የለም" ማር ፲፮ እስከ ፍፃሜው ይነበብ
"ፈርተውም ፊታቸውን ወደ ምድር አቀርቅረው ሳሉ እንዲህ አሉአቸው ሕያውን ከሙታን ስለምን ትፈልጋላችሁ? ተነስቷል እንጂ በዚህ የለም" ሉቃ ፳፬ እስከ ፍፃሜው ይነበብ
እንኳን ለጌታችን ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ ክብርት ውድስት ቅድስት በዓለ ትንሳዔው በሰላም በጤና አደረሳችሁ አደረሰን
"ለመስቀልከ ንሰግድ ወለ ትንሳዔከ ቅድስት ንሴብህ ኩልነ ይእዜኒ ወዘልፈኒ"
ጌታዬ ሆይ ክቡር የሚሆን የመቃብርህ ጠባቂዎች ከድንጋፄ የተነሳ የትንሳዔህ ግርማ የገለባበጣቸው በሦሥተኛው ቀን ከሙታን ተለይተህ ለተነሳኽው ትንሳዔህ ሰላምታ ይገባል" (መልክዐ ኢየሱስ ለትንሳዔከ ቀዳማይ)
"ስለፍፁም ሃይማኖት በክብር ለሞቱ ቅዱሳን ሁሉ የትንሳዔያቸው መተማመኛ ለሆነው ትንሳዔህ ሰላምታ ይገባል"(መልክዐ ኢየሱስ ለትንሳዔከ ካልዕ)
"በአርብ ሙታን እና ህያዋን በድኅነታቸው ተደሰቱ በእኁድ ደግሞ በህይወት ያሉ አረጋገጡ እናም ትንሳዔያቸው በክርስቶስ ስጋ እንደሆነ አወቁ" (የኮፕቲክ ቤተክርስቲያ የመጋቢት፳፱ ስንክሳር )
"በእውነት እኛ ኦርቶዶክሳውያን የዘመናት ንጉስ ክርስቶስ ከሙታን ተነሳ ብለን እናምናለን ከእኛ ንጉስ አማኑኤል ከሞት መነሳት በኋላ ሁሉን ደስታ እና ሀሴት እግዚአብሔር"(የኮፕቲክ ቤተክርስቲያን የበዓለ ሃምሳ የሌሊት ምስጋንና)
"የእኛ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ እና ጥበቡን እኛ ክርስቶስ ከሙታን ተነሳ ብለን እናመሰግነዋለን እናም እሱ እንደተናገረው ነብያትም እንደተናገሩት በመቃብር ተቀበረ ከሦስት ቀንም በኋላ ተነሳ" (የኮፕቲክ ቤተክርስቲያን የበዓለ ሃምሳ የሌሊት ምስጋና)
"የደስታ እናት ድንግል ማርያም ተደሰቺ በእውነት ያንቺ ልጅ ኢየሱስ ክርስቶስ ከሙታን ተነስቷልና ዛሬ ሁላችን እንደሰት ደስተኛም እንሁን ምክንያቱም የንጉሦች ንጉሥ ኢየሱስ ክርስቶስ ከሙታን ተነስቷልና"(የኮፕቲክ ቤተክርስቲያን የበዓለ ሃምሳ የሌሊት ምስጋና)
"ጥበበኛው ሉቃስ እና ተወዳጁ ዮሐንስ ክርስቶስ ከሙታን ተነስቷልና በእውነቱ ወንጌልን ስበኩ ክርስቶስ ሆይ የማጠልቅ ፀሀይ ሆይ ና እኛም ኢየሱስ ክርስቶስ ከሙታን ተነስቷል ብለን እናመስግንህ"(የኮፕቲክ ቤተክርስቲያን የበዓለ ሃምሳ የሌሊት ምስጋና)
" ሞት በሞት ተያዘ ክርስቶስ ከሙታን ተነሳ እሱ በመቃብር ሆኖ ህይወትን ሰጠ"(የምስራቅ ኦርቶዶክሳውያን ስንክሳር የፋሲካ ስንክሳር)
"ይሄ የትንሳዔ ቀን ነው ሁላችንም በበዓሉ እናብራ(እንድመቅ) ሁላችንም እርስ በእርስ እንተቃቀፍ ሁላችንም የጠላነውንም ቢሆን እንኳ በትንሳዔው ይቅር እንበል ወንድሞቼ ተባብለንምእንጠራራ"(የምስራቅ ኦርቶዶክሳውያን ስንክሳር የፋሲካ ስንክሳር)
"ሞትሆይ መያዝህ የትአለ? መቃብር ሆይ ድል መንሳትህ የትአለ? ክርስቶስ ሲነሳ እና ሲነግስ ከስልጣንህ ተሻርክ፣ክርስቶስ ሲነሳ አጋንንት ወደቁ፣ ክርስቶስ ሲነሳ መላዕክት ተደሰቱ"
(ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ)
"ትላንት ከእርሱጋ ተሰቅዬ ነበር ዛሬ ከእርሱጋ እከብራለሁ ትላንት ከእርሱጋ ሞቼ ነበር ዛሬ ከእርሱጋ ህያው እሆናለሁ ትላንት ከእርሱ ጋ ተቀብሬ ነበር ዛሬ ከእርሱ ጋር እነሳለሁ"
(ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘእንዚናንዙ
"ምድር በክርስቶስ ደም ታጥባለችና ፋስካን ታደርጋለች"
(ቅዱስ ያሬድ ኢትዮጵያዊ)
ለሁላችሁም መልካም የፋሲካ በዓል ወንድሞቼ እኅቶቼ።
@APOSTOLICsuccession
BY የጥያቄዎቻችሁ መልስ
Share with your friend now:
tgoop.com/APOSTOLICsuccession/6649