tgoop.com/Abulabas/2269
Last Update:
የሠለፊዮች መለያየት ምክንያትና የድንበር አላፊዎች አይነት
የሠለፊዮች መለያየት እንደ ማንኛውም አይነት ሠው መለያየት ነው ። ምክንያቱም እነሱም ሠዎች ናቸው ።
ሠለፊዮች እንደ ነብያቸው صلى الله عليه ፍፁምና ጥቡቅ ጀመዓዎች ናቸው ያለ ማንም የለም ።
እንደ አጠቃላይ የሠለፊዮች ዳዕዋ ጥቡቅና ፍፁም ስለ መሆንዋ ጥርጥር የለውም ። ነገር ግን የተናጥል የዳዕዋ ሂደታቸው ፍፁም አይደለችም ።
የተናጥል የዳዕዋ ሂደት ላይ ልዩነት ይፈጠራል ። ነብያችንም صلى الله عليه وسلم የዚህ ኡማ መለያየት እንደሚያስጋቸው ጠቅሰዋል ።
ይህ ልዩነት ነቢያችን صلى الله عليه وسلم ያስጠነቀቁን ነገር ነው ። እውነታውም ይህ መለያየታ የሚወደው የለም ። ምክንያቱም
وَاعْتَصِمُوا بِحَبْلِ اللَّهِ جَمِيعًا وَلَا تَفَرَّقُوا ۚ وَاذْكُرُوا نِعْمَتَ اللَّهِ عَلَيْكُمْ إِذْ كُنتُمْ أَعْدَاءً فَأَلَّفَ بَيْنَ قُلُوبِكُمْ فَأَصْبَحْتُم بِنِعْمَتِهِ إِخْوَانًا وَكُنتُمْ عَلَىٰ شَفَا حُفْرَةٍ مِّنَ النَّارِ فَأَنقَذَكُم مِّنْهَا ۗ كَذَٰلِكَ يُبَيِّنُ اللَّهُ لَكُمْ آيَاتِهِ لَعَلَّكُمْ تَهْتَدُونَ
የአላህንም (የማመን) ገመድ ሁላችሁም ያዙ፡፡ አትለያዩም፡፡ ጠበኞችም በነበራችሁ ጊዜ በእናንተ ላይ (የዋለውን) የአላህን ጸጋ አስታውሱ፡፡ በልቦቻችሁም መካከል አስማማ፡፡ በጸጋውም ወንድማማቾች ኾናችሁ፡፡ በእሳት ጉድጓድ አፋፍም ላይ ነበራችሁ፡፡ ከእርስዋም አዳናችሁ፡፡ እንደዚሁ ትመሩ ዘንድ አላህ ለእናንተ አንቀጾቹን ያብራራል፡፡
የምትለዋን ትልቁ የሙስሊሞች መርህና መሰረት ሥለምታጠፋና ሥለምትንድ ነው ።
የሚያሳዝነው ግን ፦ አንዳንዶች መሀይማን ብቻ ሳይሆን አውቀው የመኸየሙ ወንድሞቻችን ብቅ ብለው አብዛኛው ሃሳብና ጭንቀታቸው በአህለል ሡና ወንድማቸው ላይ ረድ ማድረግ ሆነ ።
ሸይጧንም ትልቁ በአሏህ መንገድ ላይ የሚደረግ ትግል አድርጎም ሳለላቸው ።
ከተለያዩ ግልፅና ጥርት ካሉ የቢዳዓ አንጃዎች የተለያዪ ማምታቻዎችን እያዩ ምንም አይመስላቸውም ።
በሱናና በዓቂዳህ ከሚመሳሰለው ወንድሙ ዘንድ ግን አንድ የኢጅቲሃድ ( ልዩነትን የሚያስተናግድ) ነጥብ ካየ እጅጉን ይቃወማል ፣ ጉዳዩንም ያተልቀዋል እንዲሁም ይህን መታገል ትልቁ ጂሀድ ያስመስለዋል ።
ይህ ሚስኪን በዚህ በር በመግባት ሰለፊዮችን ይበታትናል ። ያለበት መንገድ ጥርት ያለቹ ሰለፊይነትም ትመስለዋለች ። እውነታው ግን የሰለፊዎችን አንድመስመር እየሰነጠቀ ነው ።
ነብያችን صلى الله عليه وسلمሥለ መለያየት በተናገሩ ጊዜ ያሉትን አስተውሉ። መለያየትን
"የ ም ት ላ ጭ" ብለው ሰየሟት ።
"ፀጉር የምትላጭ ማለቴ አይደለም ። ነገር ግን ዲንን ነው የምትላጨው " ብለዋል ።
ወደ አኼራ የሄዱ የዘመናችን ዑለማኦች እንደ እነ ሸይኽ አልባኒ ፣ ሸይኽ ኢብን ባዝ ሸይኽ ፣ ኢብኑ ኡስይሚንና ሸይኽ ሙቅቢል አሏህ ይዘንላቸውና ይህንን ኡማ እዚህ ደረጃ እንዲደርስ ብዙ ጥረት አድርገዋል ። አሏህ ምስጋና ይገባውና ሱናም ይፋ ሆነች ። ወዳጅ ይቅርና ተቀዋሚ እንኳን ራሱን ወደዚህ መንሃጅ ሲያስጠጋ ይደሰት ይኮራም ነበር ። ... .....
በጣም በሚያሳዝን መልኩ ግን አንዳንድ ወንድሞች መጥተው ( ይህንን መንገድ ) ጥፍሩን ቆረጡት ክንፋንም ሰበሩት አፈር ውስጥም መቅበር ፈለጉ ። በማያውቁት ሁኔታ የሐቅ ጀመዓዎችን መቅበር ጀመሩ ፡፡ እነሱ ጋር ያለው የእጅቲሓድ ነጥብ በሙሉ ሥሙን ቀይረው ቀዋዒድ ( መርህ) ብለው ይጠሩትም ጀመሩ ።
እነ እንትናየቢዳዓ ሠዎችን መርህ ወይም ቃዒዳ አለው ይላሉ ። ነገር ግን እነ እንትና ጋር ያለው የቢዳዓ ሠዎች መርሕ ምንድን ነው ?
ሲባል ዝም ይላሉ ።
ወንድሞች እውነታው ግን እኛ የሚያስተሳስረን የሰለፎች ፣ የአንሷሮችና የሙሃጅሮች ዓቂዳህ ነው ። እዚሁ ላይ ነው ውዴታና ጥላቻ የሚገነባው ።
እነዚህ ሠዎች ግን ጥላቻና ውዴታቸውን መሰረት የሚያደርጉት የኢጅቲሀድ ነጥብ ላይ ነው ።
ከእነሱ መካከል አንዱ ሌላ ሰው ላይ ከተናገረ ። ከእሱ ጋር ካልተስማማህ ከተናገረበት ሰው ጋር ይራጥፍሀል ።
እንዲህ አይነቱ አካሄድ የትኛው ዲን ላይ ነው ያገኛችሁት ?
የአንተ ንግግር ራሱ እኮ ኢጅቲሀድ ነው ። ምን አልባትም አሏህ ዘንድ ተሳሳች ነህ በጣም የሚገርም ነዉ ! ።
ያም ሆነ ይህ እነዚህ በዘመናችን ብቅ ያሉ ሠዎች በጣም በሚያዝነው መልኩ እነዚያ ጥርሳቸው የሚሰብሩላቸውና ጥፍራቸውን ሊቆርጡላቸው የሚችሉ ዑለማኦዎች በነበሩበት ዘመን አነበሩም ። ዛሬ ብቅ አሉ እንጂ ።
እነዚህ ሰዎች ሶስት አይነት ሠዎች ናቸው ።
1/ ያልተማሩ ተራ ስለፊዮች :- እነዚህ ደግሞ በፊት ያነበሩ አዲስ ትውልዶች ናቸው ። አህለል ሱናዎች ላይ ካልዘመቱ አህለል ሱና የማይሆኑ መሰሏቸዋል ።
እነሱ ብቻ አህለል ሱና ሌላው በአጠቃላይ የቢዳዓ በሚል ሰይሟል ። በጣም የሚያሳዝኑ ሚስኪን ፣ መሰረት የሌላቸውና ጭፍን ተከታዮች ናቸው ።
2/ መካከል ላይ ያሉ ራሳቸውን ወደ ሽይኽነት የሚያስጠጉ ዱዓቶች ናቸው ።
ይህንን መንገድ የሚከተሉት የመጣልና ዋጋ የማሳጣት ዘመቻ እንዳይደረግባቸ ፈርተው ነው ።
ካረፈች ገዳይ የሆነች ጨካኝ መዶሻ እንደታርባቸው ፈርተህ ታዘዝ ሰላም ትሆናለህ አሉ። ለሚተቸው ሁሉ ታዛዥ ሁን " የሚል ነው።
3 / አደገኛው ነው ።
እነሱም :- የዳዕዋ እንቅስቃሴ ነበራቸው ። ነገር ግን ዳዕዋቸው ብዙም ተቀባይነትና እውቅናን አላገኘችም። እንደ መፍትሄ የውስዱት ሰዎችን የመተቸት ፣የማዋረድ ፣ ያለአግባብ የመናገር ማእበል መከተል ነው።
ያኔ እላይ ይሰቀላሉ ። ተሰቀሉም ። ኡለማኦች ያለፉበት የትግል ፣ የሂፍዝ ፣ የመማር ፣ የዒባዳህ መንገዶች ሳያልፉ በአንዴ ኡለማእ ሆነው ተሰቀሉ ።
እነዚህ ግለሰቦች አካባቢያቸው ላይ ብቸኛ የጀርህ ወትታዕዲል መመለሻ ይሆናሉ።
የጀርህና ታዕዲል ኡለማእ በሰለፎች ዘመን ጥቂቶች ነበሩ ።
ምክንያቱም ዘሀቢ እንደ ገለጹት "ሙሉ እውቀትና ሙሉእ ጥንቃቄ ( ወረዕ) " ሥለሚፈልግ ነበር ። እነዚህ የዘመናችን ግን ብዙ ሆነው አረፋ ።
ይህ የሰለፎች እውቀትና ጥንቃቄ እነዚህ ዘንድ የት አለ ?
ይህ ሶስተኛው አይነት ችግር ከአሏህ እንጂ መፍትሄ የለውም ። ምክንያቱም በሽታው ያለው ልቡ ውስጥ ሥለ ሆነ ።
የታይታና የይስሙልኝ ሠዎች ናቸው ። ቫይረስ ልብ ካጠቃ ዱኣ ከማድረግ ውጪ መፍትሄ የለውም ።
ወንድሞቼ ሆይ ከእነዚህ ሶስት አይነት ሰዎች እንዳትሆኑ ተጠንቀቁ።
የአንሷሮችና የሙሀጅሮች መንገድ ላይ ሆኖ የምታውቁት ወንድማችሁ ከአቂዳ ውጪ ባለ ጉዳይ ምንም እንኳን ቢሳሳት አስጠጉት ፣ ለመመለስም ሞክሩ ፣ እቀፋት በወዳጅነት ላይ ታገሉ ። ..........
🎙️ ከሽይኽ አብዱልመሊክ ረመዷኒ ንግግር የተወሰደ
https://www.tgoop.com/twhidsunabegegnea
BY Abul Abas Nasir (አቡል ዓባስ)
Share with your friend now:
tgoop.com/Abulabas/2269