DNABEL Telegram 1637
ላትሞት ነው የምትፈታው?
(የሆሣዕና ፍትሐት)

ቤተ ክርስቲያናችን በበዓለ ሆሣዕና ቀን ከምታከናውናቸው ነገሮች መካከል አንዱ ለክርስተ‍ኢያኖች ሁሉ ፍትሐት ማድረግ ነው። ይኸውም ከሆሳዕና ቀጥሎ ባሉት ቀናት ሌሎቹን አገልግሎት ሁሉ ለጊዜው አቁማ ልክ እንደ ሰጎን ዕንቁላል ከክርስቶስ ሕማም እና ሞት ላይ ዓይኗን ስለማታነሣ፣ በዚህ ሳምንት የሚያንቀላፋ ቢኖሩ ቀድማ በዕለተ ሆሳዕና ፍትሐት ታደርግለታለች።

ይሁን እንጂ የፍትሐቱ ዋናው ምሥጢር ያለው ግን እዚህ ላይ ነው። ክርስቶስ የተቀበለው መከራ እና ሞቱ በሚታሰብበት በመጪው ሳምንት ልጆቿ ምእመናን የሥጋ ፈቃዳቸውን በመስቀል ሰቅለው ስለ እነርሱ ሲል ለሞተው አምላክ፣ እነርሱም ለዚህ ዓለም ፍትወት የሞቱ ሆነው እንዲያሳልፉ ለማሳሰብ ነው። ስለዚህም ክርስቲያኖችን ሁሉ በቁማቸው ሳሉ እንደ መነኮሳቱ (ለዓለሙ ፈቃድ እንደ ሞቱት) ፍትሐት ታደርግላቸዋለች። ታዲያ በሆሣዕና ሰንበት ወደ ቤተ ክርስቲያን ለፍትሐት ስትመጣ ለራስህ ፈቃድ ሙት ሆነህ ለክርስቶስ ለመኖር ወስነህ ነው? ወይስ ላትሞት ነው ለመፈታት የምትሄደው?

“በሕይወትም ያሉት ስለ እነርሱ ለሞተውና ለተነሣው እንጂ ወደ ፊት ለራሳቸው እንዳይኖሩ ስለ ሁሉ ሞተ”

2ኛ ቆሮ 5:15

ዲያቆን አቤል ካሳሁን

https://www.tgoop.com/Dnabel



tgoop.com/Dnabel/1637
Create:
Last Update:

ላትሞት ነው የምትፈታው?
(የሆሣዕና ፍትሐት)

ቤተ ክርስቲያናችን በበዓለ ሆሣዕና ቀን ከምታከናውናቸው ነገሮች መካከል አንዱ ለክርስተ‍ኢያኖች ሁሉ ፍትሐት ማድረግ ነው። ይኸውም ከሆሳዕና ቀጥሎ ባሉት ቀናት ሌሎቹን አገልግሎት ሁሉ ለጊዜው አቁማ ልክ እንደ ሰጎን ዕንቁላል ከክርስቶስ ሕማም እና ሞት ላይ ዓይኗን ስለማታነሣ፣ በዚህ ሳምንት የሚያንቀላፋ ቢኖሩ ቀድማ በዕለተ ሆሳዕና ፍትሐት ታደርግለታለች።

ይሁን እንጂ የፍትሐቱ ዋናው ምሥጢር ያለው ግን እዚህ ላይ ነው። ክርስቶስ የተቀበለው መከራ እና ሞቱ በሚታሰብበት በመጪው ሳምንት ልጆቿ ምእመናን የሥጋ ፈቃዳቸውን በመስቀል ሰቅለው ስለ እነርሱ ሲል ለሞተው አምላክ፣ እነርሱም ለዚህ ዓለም ፍትወት የሞቱ ሆነው እንዲያሳልፉ ለማሳሰብ ነው። ስለዚህም ክርስቲያኖችን ሁሉ በቁማቸው ሳሉ እንደ መነኮሳቱ (ለዓለሙ ፈቃድ እንደ ሞቱት) ፍትሐት ታደርግላቸዋለች። ታዲያ በሆሣዕና ሰንበት ወደ ቤተ ክርስቲያን ለፍትሐት ስትመጣ ለራስህ ፈቃድ ሙት ሆነህ ለክርስቶስ ለመኖር ወስነህ ነው? ወይስ ላትሞት ነው ለመፈታት የምትሄደው?

“በሕይወትም ያሉት ስለ እነርሱ ለሞተውና ለተነሣው እንጂ ወደ ፊት ለራሳቸው እንዳይኖሩ ስለ ሁሉ ሞተ”

2ኛ ቆሮ 5:15

ዲያቆን አቤል ካሳሁን

https://www.tgoop.com/Dnabel

BY Dn Abel Kassahun Mekuria




Share with your friend now:
tgoop.com/Dnabel/1637

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

Invite up to 200 users from your contacts to join your channel Hui said the messages, which included urging the disruption of airport operations, were attempts to incite followers to make use of poisonous, corrosive or flammable substances to vandalize police vehicles, and also called on others to make weapons to harm police. 3How to create a Telegram channel? Today, we will address Telegram channels and how to use them for maximum benefit. Telegram message that reads: "Bear Market Screaming Therapy Group. You are only allowed to send screaming voice notes. Everything else = BAN. Text pics, videos, stickers, gif = BAN. Anything other than screaming = BAN. You think you are smart = BAN.
from us


Telegram Dn Abel Kassahun Mekuria
FROM American