tgoop.com/DrYonasLakew/2589
Last Update:
የወንድማማች ፉክክርን በብልሀት የያዙ እናት
===========================
ስብሀት ለአብ ገብረእግዚአብሄር በአስር አመቱ ከወላጆቹ ተለይቶ ከርባ-ገረድ ወደ አዲስአበባ ቢመጣም በልጅነቱ ጥሩ ፍቅር ስለተሰጠው ለመልመድ እንዳልተቸገረ ይናገራል። በተለይ ለእናቱ ወ/ሮ መአዛ ተወልደ መድህንን ያለው ፍቅር ከፍተኛ ነው። እናቱን በስማቸው ሳይሆን "ወለላይ" እያለ ነው የሚጠራቸው።
ከዚህ በፊት የእትማማቾች (የወንድማማቾች) ፉክክር የልጆች ስነልቦና ላይ የሚያሳድረውን ዘላቂ አሉታዊ ተፅእኖ አይተናል። የነ ስብሀት እናት ወለላይ ግን በብልሀት ነበር ልጆቻቸውን ያሳደጉት። "ስብሀት ገ/ሄር ህይወትና ክህሎት" የሚለው የአለማየሁ ገላጋይ መፅሀፍ ገፅ 37 ላይ ስብሀት የሚከተለውን ይላል፦
"ለተቃና ስነ ልቦና ደግሞ የእናቴ ድርሻ ከፍተኛ ነው። በጣም ነበር የምትወደኝ። እኔ የራሴን ሳስታውስ እናታችን እኔን ከሁሉ አስበልጣ የምትወደኝ ነበር የሚመስለኝ፣ ትንሽ ካደግን በኋላ ተወልደ (ታናሽ ወንድም) ስጠይቀው "እኔን ከሁሉ አስበልጣ የምትወደኝ ይመስለኝ ነበር" አለኝ።ዮሴፍም (የታናሽ ታናሽ ወንድም) እንደዚሁ። ስለዚህ ጥበብ ነው ያ። እናቴ የጥሩ ተፅዕኖ ገድ ሆነችኝ። በመልካም ተፅእኖ በሩን ከፈተችልኝ።"
የወንድማማች (የእህትማማች) ፉክክርን ወላጆች በብልሀት ሲይዙት ይህንን ይመስላል።
በዩቲዩብ ተቀላቀሉን https://www.youtube.com/@dryonaslakew3386
ያለ አእምሮ ጤና፤ ጤና የለም!
ዶ/ር ዮናስ ላቀው
BY Mental wellness የአእምሮ ጤና
Share with your friend now:
tgoop.com/DrYonasLakew/2589