#እንኳን_ለአድዋ_ድል_በዓል_አደረሳችሁ
"ኦ ፍጡነ ረድኤት እምሩፀተ ነፋስ ወአውሎ ለዘይጼውአከ በተወክሎ #ጊዮርጊስ ቅረብ ለምሕረት ወለተሣህሎ ተወከፍ ወትረ ጸሎትየ ወቃለ ጽራህየ ኩሉ አስመ ልበ አምላክ ርህሩህ በኀቤከ ኀሎ"
ትርጉም:- ረድኤትህ ከነፋስ እና ከአውሎ የፈጠነ #ቅዱስ_ጊዮርጊስ_ሆይ ለሚማፀኑህ ሁሉ ለምሕረት ቅረብ የኔንም ፀሎቴን የመማፀኔን ቃላት ሁሉ ተቀበል የአምላክ ልብ በአንተ ለለመነው ሩህሩህ ነውና"
ለመቀላቀል👇👇👇👇
@Enatachn_mareyam
@Enatachn_mareyam
"ኦ ፍጡነ ረድኤት እምሩፀተ ነፋስ ወአውሎ ለዘይጼውአከ በተወክሎ #ጊዮርጊስ ቅረብ ለምሕረት ወለተሣህሎ ተወከፍ ወትረ ጸሎትየ ወቃለ ጽራህየ ኩሉ አስመ ልበ አምላክ ርህሩህ በኀቤከ ኀሎ"
ትርጉም:- ረድኤትህ ከነፋስ እና ከአውሎ የፈጠነ #ቅዱስ_ጊዮርጊስ_ሆይ ለሚማፀኑህ ሁሉ ለምሕረት ቅረብ የኔንም ፀሎቴን የመማፀኔን ቃላት ሁሉ ተቀበል የአምላክ ልብ በአንተ ለለመነው ሩህሩህ ነውና"
ለመቀላቀል👇👇👇👇
@Enatachn_mareyam
@Enatachn_mareyam
❤6👍2
🕊 💖 🕊
[ 🕊 ቅድስት 🕊 ]
💖
[ ቅድስና ምንድነው ? ]
ቅድስና ማለት ቀደስ ባረከ ፤ ለየ ፤ አከበረ ፤ አመሰገነ ፤ አነጻ ፤ ሰውነቱን ከርኩሰት ልቡን ከትዕቢት አራቀ ከሚለው ከግዕዝ ሥርወ ግሥ የተገኘ ኀይለ ቃል ሲሆን ቅድስና ማለት መለየት ፤ መክበር ፤ መመስገን ፣ መንጻትና መጽናት ማለት ነው፡፡
ሰውም ሆነ ሌላውም ነገር ቅዱስ የሚሆነው የእግዚአብሔር ስለሚሆን ብቻ ነው ፤ ሰው ሃይማኖት ይዞ በሥነ ምግባር እየተቀደሰ ሊሄድ ይችላል ፤ [ ዮሐ ፲፯ ፥ ፲፯ ] ዳግመኛ የሰው ልጅ ከመንፈስ ቅዱስ ሲወለድ የቅድስና ሥራ ይጀምራል ፤ በሕይወቱ ደግሞ ቅድስናውን እያሳደገ ይሄዳል ፤ በዕለተ ምጽአት ቅድስናው ፍጹም ይሆናል። [ ፩ኛ ቆሮ.፲፭ ፡ ፶፩ ፣ ፩ኛ ተሰ.፬ ፥ ፬ ]
ቅድስና በአማኝ ሕይወት ውስጥ የሚያድገው በእግዚአብሔር ኀይል ነው ፤ ነቢዩ ሕዝቅኤል " መቅደሴ ለዘለዓለም በመካከላቸው በሆነ ጊዜ እኔ እስራኤልን የምቀድሰው እግዚአብሔር እንደሆንኩ አሕዛብ ያውቃሉ::" በማለት ተናግሯል:: [ ሕዝ ፴፯ ፥ ፳፰ ]
የሰው ልጅ ለእግዚአብሔር አገልግሎት የተለየ በመሆኑ በፍጹም ኀይሉ በፍጹም ነፍሱ በፍጹም ልቡ እግዚአብሔርን መውደድ አለበት:: ቅድስናውና ፍቅሩ ደግሞ ትእዛዙን በመጠበቅ ይገለጣል። [ማር.፲፪ : ፴፫ ፣ ዮሐ.፲፬፥፳፩ ፣ ፊል.፪፥፲፪ ፣ ፩ኛዮሐ.፭፥፳፫ ፣ ዘሌዋ.፲፱፥፪ ፣ ፩ኛ ጴጥ.፩፥፲፭ ]
🕊 💖 🕊
[ 🕊 ቅድስት 🕊 ]
💖
[ ቅድስና ምንድነው ? ]
ቅድስና ማለት ቀደስ ባረከ ፤ ለየ ፤ አከበረ ፤ አመሰገነ ፤ አነጻ ፤ ሰውነቱን ከርኩሰት ልቡን ከትዕቢት አራቀ ከሚለው ከግዕዝ ሥርወ ግሥ የተገኘ ኀይለ ቃል ሲሆን ቅድስና ማለት መለየት ፤ መክበር ፤ መመስገን ፣ መንጻትና መጽናት ማለት ነው፡፡
ሰውም ሆነ ሌላውም ነገር ቅዱስ የሚሆነው የእግዚአብሔር ስለሚሆን ብቻ ነው ፤ ሰው ሃይማኖት ይዞ በሥነ ምግባር እየተቀደሰ ሊሄድ ይችላል ፤ [ ዮሐ ፲፯ ፥ ፲፯ ] ዳግመኛ የሰው ልጅ ከመንፈስ ቅዱስ ሲወለድ የቅድስና ሥራ ይጀምራል ፤ በሕይወቱ ደግሞ ቅድስናውን እያሳደገ ይሄዳል ፤ በዕለተ ምጽአት ቅድስናው ፍጹም ይሆናል። [ ፩ኛ ቆሮ.፲፭ ፡ ፶፩ ፣ ፩ኛ ተሰ.፬ ፥ ፬ ]
ቅድስና በአማኝ ሕይወት ውስጥ የሚያድገው በእግዚአብሔር ኀይል ነው ፤ ነቢዩ ሕዝቅኤል " መቅደሴ ለዘለዓለም በመካከላቸው በሆነ ጊዜ እኔ እስራኤልን የምቀድሰው እግዚአብሔር እንደሆንኩ አሕዛብ ያውቃሉ::" በማለት ተናግሯል:: [ ሕዝ ፴፯ ፥ ፳፰ ]
የሰው ልጅ ለእግዚአብሔር አገልግሎት የተለየ በመሆኑ በፍጹም ኀይሉ በፍጹም ነፍሱ በፍጹም ልቡ እግዚአብሔርን መውደድ አለበት:: ቅድስናውና ፍቅሩ ደግሞ ትእዛዙን በመጠበቅ ይገለጣል። [ማር.፲፪ : ፴፫ ፣ ዮሐ.፲፬፥፳፩ ፣ ፊል.፪፥፲፪ ፣ ፩ኛዮሐ.፭፥፳፫ ፣ ዘሌዋ.፲፱፥፪ ፣ ፩ኛ ጴጥ.፩፥፲፭ ]
🕊 💖 🕊
❤1
🕊
[ † እንኳን ለአባታችን ቅዱስ አጋቢጦስ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ፤ አደረሰን። † ]
† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን ! †
🕊 † ቅዱስ አጋቢጦስ † 🕊
+ ይህንን ዓለም ንቆ ለበርካታ ዘመናት በፍፁም ምናኔ የኖረ::
+ ምድራዊ ሃብትና ሹመት ሞልቶለት ሳለ ከሁሉ የክርስቶስን ፍቅር የመረጠ::
+ ከደግነቱ ብዛት የተነሳ ምግብ ሲያዘጋጅ ሽምብራውን ከክቶ ለሌሎች ከሰጠ በሁዋላ ለራሱ የሚመገበው ገለባውን [ አሠሩን ] ነበር::
ሌሊቱን በጸሎት ለመትጋት ማታ ማታ አመድ ይመገብ ነበር:: በዚህም ቅዱስ ዳዊት "አመድን እንደ እህል በላሁ" ያለው በዚህ ቅዱስ ሕይወት ላይ ተገልጧል:: [መዝ.፻፩፥፱] (101:9)
ቅዱስ አጋቢጦስ በዘመኑ ከሠራቸው ይህኛው እጅግ ይገርመኛል:: እርሱ በበርሃ የነበረበት ዘመኑ የሰማዕታት በመሆኑ ብዙ ክርስቲያኖች በርጉማን መክስምያኖስና ዲዮቅልጢያኖስ ተገድለዋል:: ቅዱሱን ግን በአካባቢው የነበረ ሃገረ ገዢ ከበዓቱ አስወጥቶ ወደ ውትድርና ሥራ አስገብቶታል::
ሰይጣን በዚህ ከተጋድሎና ከቅድስና ሕይወት እንደሚያርቀው ተማምኖ ነበር:: ቅዱስ አጋቢጦስ ግን በወታደሮች መካከል ሆኖም ተጋድሎውን ቀጠለ:: የጦር ሠራዊት አለቃ አድርገው ቢሾሙትም እርሱ ከበጐ ማንነቱ ፈጽሞ አልተለወጠም::
ክርስቲያን ማለት እንዲህ ነውና:: ክርስትና ሲመቸን : ሲመቻችልን : በአጋጣሚ ወይም በምክንያት የምንኖረው ሕይወት አይደለም:: ፍጹም ፍቅር የጊዜ : የቦታ : የሁኔታ ገደብ የለውምና አባቶቻችን በጊዜውም : ያለ ጊዜውም ጸንተው ክርስቶስ መድኃኒታችንን አስደሰቱ::
ከቅዱስ ዻውሎስ ጋርም እንዲህ ሲሉ ዘመሩ:- "መኑ ያኀድገነ ፍቅሮ ለክርስቶስ" [ ከክርስቶስ ፍቅር ማን ይለየናል ! ]
ወደ ቀደመው ነገራችን እንመለስና ቅዱስ አጋቢጦስ ለዘመናት ሰው ሳይገድል : ፈጣሪውን ሳይበድል : ከጾም ከጸሎት : ከምጽዋትና ትሕርምት ሳይጐድል ኖረ:: በዚህም ሰይጣንን አሳፈረ:: ዘመነ ሰማዕታትም አለፈ::
በዚህ ጊዜም ወደ በዓቱ ለመመለስ መንገድን ይፈልግ : ይጸልይም ገባ:: እግዚአብሔርም ወደ በርሃ የሚመለስበትን መንገድ በቸርነቱ አቀናለት::
ነገሩ እንዲህ ነው:: ዘመነ ሰማዕታት አልፎ ራትዕ [የቀና] ንጉሥ ቆስጠንጢኖስ ነገሠ:: ስደት ቆመ:: የታሠሩ ተፈቱ:: አብያተ ክርስቲያናት ታነጹ:: ለክርስቲያን ቀደምቶቻችንም ታላቅ ተድላ ሆነ::
ጊዜው ለሁሉ ክርስቲያን የተድላ ቢሆንም አንድ ወጣት በደዌ ሰይጣን ያሰቃየው ነበር:: ወጣቱ የንጉሡ የቅዱስ ቆስጠንጢኖስ ባለሟል : ባለብዙ ሃብት : መልኩ ያማረ ነውና ሁሉ ያዝንለታል:: ይልቁኑ ቅዱሱ ንጉሥ ተጨነቀለት::
አንድ ቀን ግን ከወታደሮቹ አንዱ ያን ወጣት "አንተንኮ አጋቢጦስ ይፈውስህ ነበር" ይለዋል:: ወጣቱ ግን አላወቀምና "ከመቼ ወዲህ የጦር አለቃ እንዲህ አድርጐ ያውቃል?" ሲል በጥያቄ ይመልስለታል:: ወታደሩ ግን ቀስ አድርጐ ምሥጢሩን ይነግረዋል::
ይህ ነገር ሲያያዝ ከንጉሡ ደርሶ ቅዱስ አጋቢጦስን አስጠርቶ "እባክህ ፈውስልኝ?" ይለዋል:: "ካዳንክልኝም የፈለግኸውን አደርግልሃለሁ" ሲል ያክልለታል:: ቅዱስ አጋቢጦስም ወደ ፈጣሪው ለምኖ ሰይጣንን ይገስጸዋል:: በቅጽበትም በክርስቶስ ኃይል ወጣቱ ይድናል::
ቅዱስ ቆስጠንጢኖስም ከደስታው ብዛት "ምን ላድርግልህ?" ቢለው ቅዱሱ "ከሹመቴ ሻረኝ : ወደ በርሃ አሰናብተኝ" ብሎ መሻቱን ገለጸለት:: ቅዱሱ ንጉሥም በመገረም ቡራኬውን ተቀብሎ ወደ በርሃ ሸኝቶታል::
ወገኖቼ ! . . . በዓለማዊም ሆነ በመንፈሳዊው እርከን ስልጣንን የሚንቁ ሰዎችን ካላገኘን መፍትሔው ሩቅ ነው:: እኛም ከሥልጣን መሻት እንራቅ:: ማር ይስሐቅ እንደ ነገረን ሰይጣን ያደረበት ሰው ሹመትን [ሥልጣንን] በመሻቱ ይታወቃልና::
ቅዱሱ በፍፃሜ ዘመኑ እረኝነት [ዽዽስና] ተሹሞ ብዙ ኢ-አማንያንን ወደ ክርስትና መልሶ: ድውያንን ፈውሶ: እውራንን አብርቶ: በርካታ ተአምራትንም አድርጎ በዚህች ቀን አርፏል::
††† ልመናው በረከቱ ይደርብን::
🕊
[ † የካቲት ፳፬ [ 24 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]
፩. ቅዱስ አጋቢጦስ [ ጻድቅ ኤዺስቆዾስ ]
፪. ቅዱስ ጢሞቴዎስ ሰማዕት [ዘጋዛ]
፫. ቅዱስ ሚናስ ዘቆዽሮስ
[ † ወርኀዊ በዓላት ]
፩. ቅዱስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት [ መምሕረ ትሩፋት ]
፪. ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ
፫. ቅዱስ ሙሴ ፀሊም
፬. ቅዱስ ቶማስ ዘመርዐስ
፭. ቅዱስ አብላርዮስ ታላቁ
፮. ፳፬ቱ "24ቱ" ካኅናተ ሰማይ [ ሱራፌል ]
† " የሚያሳድዷችሁን መርቁ . . . ደስ ከሚላቸው ጋር ደስ ይበላችሁ:: ከሚያለቅሱም ጋር አልቅሱ:: እርስ በርሳችሁ በአንድ አሳብ ተስማሙ:: የትዕቢትን ነገር አታስቡ:: ነገር ግን የትሕትናን ነገር ለመሥራት ትጉ ::" † [ሮሜ.፲፪፥፲፬] (12:14-16)
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† † †
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
💖 🕊 💖
[ † እንኳን ለአባታችን ቅዱስ አጋቢጦስ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ፤ አደረሰን። † ]
† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን ! †
🕊 † ቅዱስ አጋቢጦስ † 🕊
+ ይህንን ዓለም ንቆ ለበርካታ ዘመናት በፍፁም ምናኔ የኖረ::
+ ምድራዊ ሃብትና ሹመት ሞልቶለት ሳለ ከሁሉ የክርስቶስን ፍቅር የመረጠ::
+ ከደግነቱ ብዛት የተነሳ ምግብ ሲያዘጋጅ ሽምብራውን ከክቶ ለሌሎች ከሰጠ በሁዋላ ለራሱ የሚመገበው ገለባውን [ አሠሩን ] ነበር::
ሌሊቱን በጸሎት ለመትጋት ማታ ማታ አመድ ይመገብ ነበር:: በዚህም ቅዱስ ዳዊት "አመድን እንደ እህል በላሁ" ያለው በዚህ ቅዱስ ሕይወት ላይ ተገልጧል:: [መዝ.፻፩፥፱] (101:9)
ቅዱስ አጋቢጦስ በዘመኑ ከሠራቸው ይህኛው እጅግ ይገርመኛል:: እርሱ በበርሃ የነበረበት ዘመኑ የሰማዕታት በመሆኑ ብዙ ክርስቲያኖች በርጉማን መክስምያኖስና ዲዮቅልጢያኖስ ተገድለዋል:: ቅዱሱን ግን በአካባቢው የነበረ ሃገረ ገዢ ከበዓቱ አስወጥቶ ወደ ውትድርና ሥራ አስገብቶታል::
ሰይጣን በዚህ ከተጋድሎና ከቅድስና ሕይወት እንደሚያርቀው ተማምኖ ነበር:: ቅዱስ አጋቢጦስ ግን በወታደሮች መካከል ሆኖም ተጋድሎውን ቀጠለ:: የጦር ሠራዊት አለቃ አድርገው ቢሾሙትም እርሱ ከበጐ ማንነቱ ፈጽሞ አልተለወጠም::
ክርስቲያን ማለት እንዲህ ነውና:: ክርስትና ሲመቸን : ሲመቻችልን : በአጋጣሚ ወይም በምክንያት የምንኖረው ሕይወት አይደለም:: ፍጹም ፍቅር የጊዜ : የቦታ : የሁኔታ ገደብ የለውምና አባቶቻችን በጊዜውም : ያለ ጊዜውም ጸንተው ክርስቶስ መድኃኒታችንን አስደሰቱ::
ከቅዱስ ዻውሎስ ጋርም እንዲህ ሲሉ ዘመሩ:- "መኑ ያኀድገነ ፍቅሮ ለክርስቶስ" [ ከክርስቶስ ፍቅር ማን ይለየናል ! ]
ወደ ቀደመው ነገራችን እንመለስና ቅዱስ አጋቢጦስ ለዘመናት ሰው ሳይገድል : ፈጣሪውን ሳይበድል : ከጾም ከጸሎት : ከምጽዋትና ትሕርምት ሳይጐድል ኖረ:: በዚህም ሰይጣንን አሳፈረ:: ዘመነ ሰማዕታትም አለፈ::
በዚህ ጊዜም ወደ በዓቱ ለመመለስ መንገድን ይፈልግ : ይጸልይም ገባ:: እግዚአብሔርም ወደ በርሃ የሚመለስበትን መንገድ በቸርነቱ አቀናለት::
ነገሩ እንዲህ ነው:: ዘመነ ሰማዕታት አልፎ ራትዕ [የቀና] ንጉሥ ቆስጠንጢኖስ ነገሠ:: ስደት ቆመ:: የታሠሩ ተፈቱ:: አብያተ ክርስቲያናት ታነጹ:: ለክርስቲያን ቀደምቶቻችንም ታላቅ ተድላ ሆነ::
ጊዜው ለሁሉ ክርስቲያን የተድላ ቢሆንም አንድ ወጣት በደዌ ሰይጣን ያሰቃየው ነበር:: ወጣቱ የንጉሡ የቅዱስ ቆስጠንጢኖስ ባለሟል : ባለብዙ ሃብት : መልኩ ያማረ ነውና ሁሉ ያዝንለታል:: ይልቁኑ ቅዱሱ ንጉሥ ተጨነቀለት::
አንድ ቀን ግን ከወታደሮቹ አንዱ ያን ወጣት "አንተንኮ አጋቢጦስ ይፈውስህ ነበር" ይለዋል:: ወጣቱ ግን አላወቀምና "ከመቼ ወዲህ የጦር አለቃ እንዲህ አድርጐ ያውቃል?" ሲል በጥያቄ ይመልስለታል:: ወታደሩ ግን ቀስ አድርጐ ምሥጢሩን ይነግረዋል::
ይህ ነገር ሲያያዝ ከንጉሡ ደርሶ ቅዱስ አጋቢጦስን አስጠርቶ "እባክህ ፈውስልኝ?" ይለዋል:: "ካዳንክልኝም የፈለግኸውን አደርግልሃለሁ" ሲል ያክልለታል:: ቅዱስ አጋቢጦስም ወደ ፈጣሪው ለምኖ ሰይጣንን ይገስጸዋል:: በቅጽበትም በክርስቶስ ኃይል ወጣቱ ይድናል::
ቅዱስ ቆስጠንጢኖስም ከደስታው ብዛት "ምን ላድርግልህ?" ቢለው ቅዱሱ "ከሹመቴ ሻረኝ : ወደ በርሃ አሰናብተኝ" ብሎ መሻቱን ገለጸለት:: ቅዱሱ ንጉሥም በመገረም ቡራኬውን ተቀብሎ ወደ በርሃ ሸኝቶታል::
ወገኖቼ ! . . . በዓለማዊም ሆነ በመንፈሳዊው እርከን ስልጣንን የሚንቁ ሰዎችን ካላገኘን መፍትሔው ሩቅ ነው:: እኛም ከሥልጣን መሻት እንራቅ:: ማር ይስሐቅ እንደ ነገረን ሰይጣን ያደረበት ሰው ሹመትን [ሥልጣንን] በመሻቱ ይታወቃልና::
ቅዱሱ በፍፃሜ ዘመኑ እረኝነት [ዽዽስና] ተሹሞ ብዙ ኢ-አማንያንን ወደ ክርስትና መልሶ: ድውያንን ፈውሶ: እውራንን አብርቶ: በርካታ ተአምራትንም አድርጎ በዚህች ቀን አርፏል::
††† ልመናው በረከቱ ይደርብን::
🕊
[ † የካቲት ፳፬ [ 24 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]
፩. ቅዱስ አጋቢጦስ [ ጻድቅ ኤዺስቆዾስ ]
፪. ቅዱስ ጢሞቴዎስ ሰማዕት [ዘጋዛ]
፫. ቅዱስ ሚናስ ዘቆዽሮስ
[ † ወርኀዊ በዓላት ]
፩. ቅዱስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት [ መምሕረ ትሩፋት ]
፪. ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ
፫. ቅዱስ ሙሴ ፀሊም
፬. ቅዱስ ቶማስ ዘመርዐስ
፭. ቅዱስ አብላርዮስ ታላቁ
፮. ፳፬ቱ "24ቱ" ካኅናተ ሰማይ [ ሱራፌል ]
† " የሚያሳድዷችሁን መርቁ . . . ደስ ከሚላቸው ጋር ደስ ይበላችሁ:: ከሚያለቅሱም ጋር አልቅሱ:: እርስ በርሳችሁ በአንድ አሳብ ተስማሙ:: የትዕቢትን ነገር አታስቡ:: ነገር ግን የትሕትናን ነገር ለመሥራት ትጉ ::" † [ሮሜ.፲፪፥፲፬] (12:14-16)
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† † †
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
💖 🕊 💖
#ቅድስት፤ #ሁለተኛው_የዐቢይ_ጾም_ሳምንት
‹‹ ሰንበትየ ቅድስት›› የሚልና ይህን የመሰለ የሰንበትን ቅድስና የሚያዘክር ምስጋና የሚቀርብበት ሳምንት ነው፡፡
የዚህቸ የሰንበት ክብር እጅግ ልዩ ነው ከዳግም ምጽዓት በኃላ ጸንታ የሚትቆየው ብቻኛዋ ዕለት ይህች ሰንበት ነች
‹‹ እምኵሉ ዕለት ሰንበት አክበረ
ወእምኵሉን አንስት ማርያምሃ አፍቀረ ››
ከዕለታት ሁሉ ሰንበትን አከበረ ከሴቶች ሁሉ ደግሞ #ማርያምን_አፈቀረ መረጠ ‹‹ቅዱስ ያሬድ ››
#መልካም_ቀን🙏
አጫጭር ኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶች
•➢ 👇 ለማግኘት // 👇
@Enatachn_mareyam
@Enatachn_mareyam
‹‹ ሰንበትየ ቅድስት›› የሚልና ይህን የመሰለ የሰንበትን ቅድስና የሚያዘክር ምስጋና የሚቀርብበት ሳምንት ነው፡፡
የዚህቸ የሰንበት ክብር እጅግ ልዩ ነው ከዳግም ምጽዓት በኃላ ጸንታ የሚትቆየው ብቻኛዋ ዕለት ይህች ሰንበት ነች
‹‹ እምኵሉ ዕለት ሰንበት አክበረ
ወእምኵሉን አንስት ማርያምሃ አፍቀረ ››
ከዕለታት ሁሉ ሰንበትን አከበረ ከሴቶች ሁሉ ደግሞ #ማርያምን_አፈቀረ መረጠ ‹‹ቅዱስ ያሬድ ››
#መልካም_ቀን🙏
አጫጭር ኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶች
•➢ 👇 ለማግኘት // 👇
@Enatachn_mareyam
@Enatachn_mareyam
❤10😢1
†
† 🕊 መንፈሳዊው መሰላል 🕊 †
💖
[ ዓ ለ ም ን ስ ለ መ ተ ው ! ]
[ ክፍል አምስት ]
▬▬▬▬▬▬ ♱ ▬▬▬▬▬▬
አሳባችንን ወደ የውሃት .... !
❝ የሆነ አሳባችንን ወደ የውሃት ፣ ወደ ጥልቅ ቍጣ አልባነት፣ ወደ ንቍነትም በማምጣት ፣ የንጽሕናና የንቍነት ወዳጅ እስካላደረግነው ድረስ በተለይ በቸልታ ሕይወት በሚኖሩ ዘንድ ፣ በርካታ የሚሆኑ የማይታዩ መከራትን የሚያመጣ ነውና ይህ በእውነት ታላቅ ፣ በእውነት እጅግ ታላቅ መከራ ነው፡፡
ሆኖም ግን ደካማና በፈቃደ ሥጋ የምንመላለስ እኛ ጽናት የለሽነታችንንና ደካማ ጠባያችንን ጥርጥር በሌለበት እምነት ወደ ክርስቶስ እናቀርብ ፣ ይህንም ለእርሱ እንናዘዝ ዘንድ እንበርታ ፤ ሳናቋርጥ ጥልቅ ወደ ሆነ ትሕትና ራሳችንን የምንጥል ከሆነ ብቻ ፣ ለእኛ ከሚገባው በላይ የሆነውን የእርሱን ርዳታ እንኳ እንደምናገኝ ርግጠኛ እንሆናለን፡፡
ወደ እዚህ አስደናቂ ፣ ጽኑና አስቸጋሪ ቢሆንም ቅሉ ፣ ነገር ግን ደግሞ ቀላል ወደ ሆነው መልካም ተጋድሎ የገቡ ሁሉ ፣ በእውነት ሰማያዊ የሆነው እሳት በውስጣቸው ያድር ዘንድ የሚጠብቁ ከሆነ ወደ እሳቱ ዘለው መግባት እንዳለባቸው ሊገነዘቡ ይገባል፡፡ ነገር ግን እያንዳንዱ ሰው አገልግሎቱ ወደ ገዛ ፍርዱ ወደ ገዛ ፍርዱ እንዳይመራው ፣ ራሱን ይመርምር እንጀራውንም ከመራራ ቅጠል ጋር ይብላ ፣ ጽዋውንም ከእንባ ጋር ይጠጣ፡፡ ተጠምቆ የነበረ ሰው ሁሉ ድኅነት ያላገኘ ከነበረ ተከትሎ ስለሚሆነው ነገር ዝም እላለሁ፡፡
ወደዚህ ተጋድሎ የገቡ ጽኑ መሠረትን ማኖር ይችሉ ዘንድ ሁሉንም ነገር መተው ፣ ሁሉንም ነገሮች መናቅ ፣ በሁሉም ነገሮች ላይ መዘበትና ሁሉንም ነገሮች አራግፈው መጣል አለባቸው፡፡ ለሦስቱ ንጣፎችና ለሦስቱ ምሰሶዎች ግሩም መሠረት የውሃነት ፣ ጾም ፣ ራስንም መግዛት ነው፡፡ በተፈጥሮ ሕፃናት የሆኑትን አርአያነት በመንሣት ፣ በክርስቶስ ሕፃናት የሆኑ ሁሉ በእሊህ ምግባራት ይጀምሩ፡፡ በእነርሱ [በሕፃናት] ዘንድ ከቶም አንዳች ተንኮል ወይም ማታለል አታገኝምና፡፡ እነሱ የማይረካ ፍላጎት ፣ የማይጠግብ ሆድ ፣ የሚቃጠል ወይም እንደ አውሬ ቍጡ የሆነ ሰውነት የላቸውም ፤ ምናልባት ግን አድገው የበዛ ምግብ የሚመገቡ እንደ መሆናቸው መጠን ፣ ተፈጥሮአዊ ፈቃዶቻቸው [ምኞታቸው] ደግሞ ይጨምራሉ፡፡ ❞
[ ዮሐንስ ክሊማኮስ [ ቅዱስ ዮሐንስ ዘሰዋስው ]
🕊 💖 🕊
† 🕊 መንፈሳዊው መሰላል 🕊 †
💖
[ ዓ ለ ም ን ስ ለ መ ተ ው ! ]
[ ክፍል አምስት ]
▬▬▬▬▬▬ ♱ ▬▬▬▬▬▬
አሳባችንን ወደ የውሃት .... !
❝ የሆነ አሳባችንን ወደ የውሃት ፣ ወደ ጥልቅ ቍጣ አልባነት፣ ወደ ንቍነትም በማምጣት ፣ የንጽሕናና የንቍነት ወዳጅ እስካላደረግነው ድረስ በተለይ በቸልታ ሕይወት በሚኖሩ ዘንድ ፣ በርካታ የሚሆኑ የማይታዩ መከራትን የሚያመጣ ነውና ይህ በእውነት ታላቅ ፣ በእውነት እጅግ ታላቅ መከራ ነው፡፡
ሆኖም ግን ደካማና በፈቃደ ሥጋ የምንመላለስ እኛ ጽናት የለሽነታችንንና ደካማ ጠባያችንን ጥርጥር በሌለበት እምነት ወደ ክርስቶስ እናቀርብ ፣ ይህንም ለእርሱ እንናዘዝ ዘንድ እንበርታ ፤ ሳናቋርጥ ጥልቅ ወደ ሆነ ትሕትና ራሳችንን የምንጥል ከሆነ ብቻ ፣ ለእኛ ከሚገባው በላይ የሆነውን የእርሱን ርዳታ እንኳ እንደምናገኝ ርግጠኛ እንሆናለን፡፡
ወደ እዚህ አስደናቂ ፣ ጽኑና አስቸጋሪ ቢሆንም ቅሉ ፣ ነገር ግን ደግሞ ቀላል ወደ ሆነው መልካም ተጋድሎ የገቡ ሁሉ ፣ በእውነት ሰማያዊ የሆነው እሳት በውስጣቸው ያድር ዘንድ የሚጠብቁ ከሆነ ወደ እሳቱ ዘለው መግባት እንዳለባቸው ሊገነዘቡ ይገባል፡፡ ነገር ግን እያንዳንዱ ሰው አገልግሎቱ ወደ ገዛ ፍርዱ ወደ ገዛ ፍርዱ እንዳይመራው ፣ ራሱን ይመርምር እንጀራውንም ከመራራ ቅጠል ጋር ይብላ ፣ ጽዋውንም ከእንባ ጋር ይጠጣ፡፡ ተጠምቆ የነበረ ሰው ሁሉ ድኅነት ያላገኘ ከነበረ ተከትሎ ስለሚሆነው ነገር ዝም እላለሁ፡፡
ወደዚህ ተጋድሎ የገቡ ጽኑ መሠረትን ማኖር ይችሉ ዘንድ ሁሉንም ነገር መተው ፣ ሁሉንም ነገሮች መናቅ ፣ በሁሉም ነገሮች ላይ መዘበትና ሁሉንም ነገሮች አራግፈው መጣል አለባቸው፡፡ ለሦስቱ ንጣፎችና ለሦስቱ ምሰሶዎች ግሩም መሠረት የውሃነት ፣ ጾም ፣ ራስንም መግዛት ነው፡፡ በተፈጥሮ ሕፃናት የሆኑትን አርአያነት በመንሣት ፣ በክርስቶስ ሕፃናት የሆኑ ሁሉ በእሊህ ምግባራት ይጀምሩ፡፡ በእነርሱ [በሕፃናት] ዘንድ ከቶም አንዳች ተንኮል ወይም ማታለል አታገኝምና፡፡ እነሱ የማይረካ ፍላጎት ፣ የማይጠግብ ሆድ ፣ የሚቃጠል ወይም እንደ አውሬ ቍጡ የሆነ ሰውነት የላቸውም ፤ ምናልባት ግን አድገው የበዛ ምግብ የሚመገቡ እንደ መሆናቸው መጠን ፣ ተፈጥሮአዊ ፈቃዶቻቸው [ምኞታቸው] ደግሞ ይጨምራሉ፡፡ ❞
[ ዮሐንስ ክሊማኮስ [ ቅዱስ ዮሐንስ ዘሰዋስው ]
🕊 💖 🕊
❤3
💛
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
🕊 ዐቢይ ጾም [ ጾመ እግዚእ ] 🕊
▷ " ስ ለ ፈ ቃ ድ "
[ " በአቡነ አትናቴዎስ ዘእስክንድር ... ! " ]
[ 🕊 ]
----------------------------------------------------
" በውስጡ ሰውነቴ በእግዚአብሔር ሕግ ደስ ይለኛልና ፥ ነገር ግን በብልቶቼ ከአእምሮዬ ሕግ ጋር የሚዋጋውንና በብልቶቼ ባለ በኃጢአት ሕግ የሚማርከኝን ሌላ ሕግ አያለሁ።
እኔ ምንኛ ጎስቋላ ሰው ነኝ ! ለዚህ ሞት ከተሰጠ ሰውነት ማን ያድነኛል ? " [ ሮሜ.፯፥፳፪ ]
🕊 💖 🕊
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
🕊 ዐቢይ ጾም [ ጾመ እግዚእ ] 🕊
▷ " ስ ለ ፈ ቃ ድ "
[ " በአቡነ አትናቴዎስ ዘእስክንድር ... ! " ]
[ 🕊 ]
----------------------------------------------------
" በውስጡ ሰውነቴ በእግዚአብሔር ሕግ ደስ ይለኛልና ፥ ነገር ግን በብልቶቼ ከአእምሮዬ ሕግ ጋር የሚዋጋውንና በብልቶቼ ባለ በኃጢአት ሕግ የሚማርከኝን ሌላ ሕግ አያለሁ።
እኔ ምንኛ ጎስቋላ ሰው ነኝ ! ለዚህ ሞት ከተሰጠ ሰውነት ማን ያድነኛል ? " [ ሮሜ.፯፥፳፪ ]
🕊 💖 🕊
🙏1
🕊
[ † እንኳን ለጻድቁ አባታችን ቅዱስ አቡፋና እና ቅዱስ እንጦኒ ሐዲስ ሰማዕት ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ፤ አደረሰን። † ]
† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †
🕊 † አባ አቡፋና † 🕊
† ታላቁ አባ አቡፋና ፦
በምድረ ግብጽ ተጋድሏቸውን የፈፀሙ፣
በመዐልት አምስት መቶ ጊዜ በሌሊትም አምስት ጊዜ አቡነ ዘበሰማያትን ይጸልዩ የነበሩ፣
በአርባ ቀን አንድ ጊዜ ብቻ እህል ይቀምሱ የነበሩና ሙሉ ዘመናቸውን በበርሃ በታላቅ ጽሙና የፈፀሙ አባት ናቸው።
ጻድቁ በጣም የሚታወቁት ከማበጡ የተነሳ እጅግ ግዙፍ በነበረ እግራቸው ነው። ለዚህ ምክንያቱ ደግሞ ስለ መድኃኔ ዓለም ፍቅር አልቀመጥም፤ አልተኛም ብለው ለአሥራ ስምንት ዓመታት በመቆማቸው ነው።
አሥራ ስምንት ዓመት የመቆማቸው ዜናስ እንደምን ነው ቢሉ ፦
አንድ ቀን "እኔ ግን ከዚህ ዓለም የምለየው መቼ ይሆን?" ሲሉ አሰቡ። በእርግጥ ይህንን ሐሳብ ብዙ ሰዎች ሊያስቡት ይችላል። ሐሳቡ ጠቃሚም ያልተፈቀደም ነው።
፩. "ጠቃሚ ነው።" ያልኩት አንድ ሰው ሞት እንዳለ ካወቀ ወይም 'መቼ ነው የምሞተው' ብሎ ካሰበ ንስሐ ይገባል ፤ ክፋትን ይተዋል ተብሎ ስለሚታመን ነው። ወገኔ ሁሉ እንደ አውሬ ሲባላ ፣ ደም ሲያፈስ ፣ ክፋትን ሲጐነጉን የሚውል "እሞት ባይ" ሳይሆን "እኖር ባይ" ሆኖ ነውና።
ግን ሞት በቅርቡ እንዳለ በኃያሉ አምላክ ፊት ራቁቱን ለፍርድ እንደሚቀርብ ለወገኔ ማን በነገረው !
፪. "ያልተፈቀደ ነው።" ያልኩት ደግሞ በሁለት ምክንያት ነው።
"ኢትበሉ ለጌሰም [ ለነገ አትበሉ። ]" የሚል አምላካዊ ቃል ስላለ። [ማቴ. ፮፥፴፬]
ሰው [በተለይ ዓለማዊው] የሚሞትበትን ቀን ቢያውቅ አጭር ጊዜ ከሆነ ሽብር ጭንቀት ይበላዋል። ወዲህ ደግሞ ጊዜው ረዥም ቢሆን እንደ ሰብአ ትካት [ማለትም በኖኅ ዘመን እንደ ነበሩ ሰዎች] 'ብዙውን ልዝናናበት [ኃጢአት ልሥራበት']ና ንስሐ እገባለሁ።' ይላልና ነው።
በዚያውም ላይ በቤተ ክርስቲያን ትውፊት መሠረት ቅዱስ ሰውና የነቢያት አለቃ ቅዱስ ሙሴ የሞቱን ጊዜ ጠይቆ እጅግ መቸገሩን መጥቀሱ በራሱ በቂ ነው። ጌታ "ዓርብ ቀን ትሞታለህ።" ብሎት ለሁለት ዓመታት ዓርብ ዓርብ ሲገነዝ ሲፈታ ኑሯል።
በመጨረሻም ዓርብ ቀን ድንገት መልአከ ሞት መጥቶበታል። ስለዚህ "ወድልዋኒክሙ ንበሩ - ተዘጋጅታችሁ ኑሩ። መባላችንን አስበን ልንኖር ግድ ይለናል። [ማቴ. ፳፬፥፵፬]
ወደ ቀደመ ነገራችን እንመለስና ቅዱስ አቡፋና ይህንን የዕረፍታቸውን ነገር ሲያስቡ ቅዱስ መልአክ ተገልጦ "ተርፈከ አሠርቱ ወሰመንቱ - አሥራ ስምንት ቀርቶሃል።" አላቸው። እርሳቸውም "ጌታዬ አሥራ ስምንት ምን?" ሲሉ ቢጠይቁትም ሳይመልስላቸው ተሠወረ።
ከደቂቃ እስከ ኢዮቤልዩ ብዙ አሥራ ስምንቶች አሉ። እርሳቸው ግን "አሥራ ስምንት ቀን ነው!" ብለው ለጌታ ተሳሉ። ስዕለታቸውም "ከዚህ በኋላ አልቀመጥም።" የሚል ነው። እየጾሙ እየጸለዩ ለአሥራ ስምንት ቀናት ቆሙ። ሞት አልመጣም።
"አሥራ ስምንት ሱባኤ ይሆን!" ብለው አሥራ ስምንት ሱባኤ [መቶ ሃያ ስድስት ቀናት] ቆመው ጸለዩ። አሁንም ሞት አልመጣም። "አይ! አሥራ ስምንት ወር ሊሆን ይችላል።" ብለው ለአሥራ ስምንት ወራት (ለአንድ ዓመት ከስድስት ወር) ቆመው ተጉ። አሁንም ግን ሞት የውኃ ሽታ ሆኖ ቀረ።
ይህን ጊዜ ግን ወደ ፈጣሪ ለመኑ። "ጌታዬ! ያልከኝ ምን አሥራ ስምንት ነው?"
ቅዱስ መልአኩም መጥቶ "አቡፋና ሆይ! የቀረህ አሥራ ስምንት ዓመት ነውና ጽና።" ብሏቸው ተሰወረ። ልብ በሉልኝ "እስክሞት አልቀመጥም።" ብለው ተስለዋል።
ቅዱሱ ገዳማዊ በቃላቸው የሚገኙ እውነተኛ ክርስቲያን ነበሩና ለአሥራ ስምንት ዓመታት እንደተተከለ ምሰሶ ቆመው ጸለዩ፣ ጾሙ። እንዲህ ያሉትን ቅዱሳን ሊቃውንት፦
"ሰላም ለከ ጽኑዕ ከመ ዓምድ
ዘኢያንቀለቅሎ ሞገድ።"
[ማዕበለ ዓለም የማያናውጸው ብርቱ ምሰሶ ሆይ! ምስጋና ይገባሃል።] የሚሏቸው።
ስለ ቅዱሱ የተጻፈ አርኬም ፦
"ሰላም ለቁመተ አቡፋና ዘአልቦ ኑታጌ
እስከ ተመሰለ እግሩ ከመ እግረ ነጌ።" ይላል። ከመቆም ብዛት አካላቸው ደቆ እግራቸው የዝሆን እግር እስኪመስል ወፍሮ ነበርና።
† አባ አቡፋና በዘመናቸው ብዙ ተአምራትን ሠርተው በዚህች ቀን አርፈዋል።
🕊 † ቅዱስ እንጦኒ ሐዲስ ሰማዕት † 🕊
† ቅዱስ እንጦኒ [Anthony] በትውልዱ ከሶርያ ዐረቦች ሲሆን በቀደመ ሕይወቱ ክርስቲያኖችን ያሳድድ ፣ ካህናትን ይደበድብ ፣ አብያተ ክርስቲያናትንም ያቃጥል ነበር። እግዚአብሔር በንስሐ ሲጠራው ግን ደግ ፣ ጻድቅና ምርጥ ዕቃ ሆኖ ተገኘ። በመጨረሻም ከብዙ መከራ በኋላ ለሰማዕትነት በቅቷል።
† አምላከ ቅዱሳን የወዳጆቹን ትጋት፣ ጽናት፣ ፍቅርና በረከት ያድለን። ከማስተዋልም አያጉድለን።
🕊
[ † የካቲት ፳፭ [ 25 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]
፩. ቅዱስ አባ አቡፋና ጻድቅ
፪. ቅዱስ እንጦኒ ሐዲስ ሰማዕት
፫. ቅዱሳን ሰማዕታት አውሳንዮስ፣ ፊልሞናና ሉቅያ ድንግል [የቅዱስ ጳውሎስ ሐዋርያ ደቀ መዛሙርት]
፬. ቅዱስ ቶና ዲያቆንና ሰማዕት
፭. ቅዱስ ሚናስ ዘሃገረ ቁስ
[ † ወርኀዊ በዓላት ]
፩. ቅዱስ መርቆሬዎስ ሰማዕት
፪. ቅድስት ቴክላ ሐዋርያዊት
፫. ቅዱስ አበከረዙን ሰማዕት
፬. ቅዱስ ዱማድዮስ ሶርያዊ
፭. አቡነ አቢብ [ አባ ቡላ ]
† " ኃይል የሰጠኝን ክርስቶስ ኢየሱስን ጌታችንን አመሰግናለሁ። አስቀድሞ ተሳዳቢና አሳዳጅ አንገላችም ምንም ብሆን ይህን አደረገልኝ። ነገር ግን ሳላውቅ ባለማመን ስላደረግሁት ምሕረትን አገኘሁ።" † [፩ጢሞ ፩፥፲፪-፲፫]
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† † †
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
💖 🕊 💖
[ † እንኳን ለጻድቁ አባታችን ቅዱስ አቡፋና እና ቅዱስ እንጦኒ ሐዲስ ሰማዕት ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ፤ አደረሰን። † ]
† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †
🕊 † አባ አቡፋና † 🕊
† ታላቁ አባ አቡፋና ፦
በምድረ ግብጽ ተጋድሏቸውን የፈፀሙ፣
በመዐልት አምስት መቶ ጊዜ በሌሊትም አምስት ጊዜ አቡነ ዘበሰማያትን ይጸልዩ የነበሩ፣
በአርባ ቀን አንድ ጊዜ ብቻ እህል ይቀምሱ የነበሩና ሙሉ ዘመናቸውን በበርሃ በታላቅ ጽሙና የፈፀሙ አባት ናቸው።
ጻድቁ በጣም የሚታወቁት ከማበጡ የተነሳ እጅግ ግዙፍ በነበረ እግራቸው ነው። ለዚህ ምክንያቱ ደግሞ ስለ መድኃኔ ዓለም ፍቅር አልቀመጥም፤ አልተኛም ብለው ለአሥራ ስምንት ዓመታት በመቆማቸው ነው።
አሥራ ስምንት ዓመት የመቆማቸው ዜናስ እንደምን ነው ቢሉ ፦
አንድ ቀን "እኔ ግን ከዚህ ዓለም የምለየው መቼ ይሆን?" ሲሉ አሰቡ። በእርግጥ ይህንን ሐሳብ ብዙ ሰዎች ሊያስቡት ይችላል። ሐሳቡ ጠቃሚም ያልተፈቀደም ነው።
፩. "ጠቃሚ ነው።" ያልኩት አንድ ሰው ሞት እንዳለ ካወቀ ወይም 'መቼ ነው የምሞተው' ብሎ ካሰበ ንስሐ ይገባል ፤ ክፋትን ይተዋል ተብሎ ስለሚታመን ነው። ወገኔ ሁሉ እንደ አውሬ ሲባላ ፣ ደም ሲያፈስ ፣ ክፋትን ሲጐነጉን የሚውል "እሞት ባይ" ሳይሆን "እኖር ባይ" ሆኖ ነውና።
ግን ሞት በቅርቡ እንዳለ በኃያሉ አምላክ ፊት ራቁቱን ለፍርድ እንደሚቀርብ ለወገኔ ማን በነገረው !
፪. "ያልተፈቀደ ነው።" ያልኩት ደግሞ በሁለት ምክንያት ነው።
"ኢትበሉ ለጌሰም [ ለነገ አትበሉ። ]" የሚል አምላካዊ ቃል ስላለ። [ማቴ. ፮፥፴፬]
ሰው [በተለይ ዓለማዊው] የሚሞትበትን ቀን ቢያውቅ አጭር ጊዜ ከሆነ ሽብር ጭንቀት ይበላዋል። ወዲህ ደግሞ ጊዜው ረዥም ቢሆን እንደ ሰብአ ትካት [ማለትም በኖኅ ዘመን እንደ ነበሩ ሰዎች] 'ብዙውን ልዝናናበት [ኃጢአት ልሥራበት']ና ንስሐ እገባለሁ።' ይላልና ነው።
በዚያውም ላይ በቤተ ክርስቲያን ትውፊት መሠረት ቅዱስ ሰውና የነቢያት አለቃ ቅዱስ ሙሴ የሞቱን ጊዜ ጠይቆ እጅግ መቸገሩን መጥቀሱ በራሱ በቂ ነው። ጌታ "ዓርብ ቀን ትሞታለህ።" ብሎት ለሁለት ዓመታት ዓርብ ዓርብ ሲገነዝ ሲፈታ ኑሯል።
በመጨረሻም ዓርብ ቀን ድንገት መልአከ ሞት መጥቶበታል። ስለዚህ "ወድልዋኒክሙ ንበሩ - ተዘጋጅታችሁ ኑሩ። መባላችንን አስበን ልንኖር ግድ ይለናል። [ማቴ. ፳፬፥፵፬]
ወደ ቀደመ ነገራችን እንመለስና ቅዱስ አቡፋና ይህንን የዕረፍታቸውን ነገር ሲያስቡ ቅዱስ መልአክ ተገልጦ "ተርፈከ አሠርቱ ወሰመንቱ - አሥራ ስምንት ቀርቶሃል።" አላቸው። እርሳቸውም "ጌታዬ አሥራ ስምንት ምን?" ሲሉ ቢጠይቁትም ሳይመልስላቸው ተሠወረ።
ከደቂቃ እስከ ኢዮቤልዩ ብዙ አሥራ ስምንቶች አሉ። እርሳቸው ግን "አሥራ ስምንት ቀን ነው!" ብለው ለጌታ ተሳሉ። ስዕለታቸውም "ከዚህ በኋላ አልቀመጥም።" የሚል ነው። እየጾሙ እየጸለዩ ለአሥራ ስምንት ቀናት ቆሙ። ሞት አልመጣም።
"አሥራ ስምንት ሱባኤ ይሆን!" ብለው አሥራ ስምንት ሱባኤ [መቶ ሃያ ስድስት ቀናት] ቆመው ጸለዩ። አሁንም ሞት አልመጣም። "አይ! አሥራ ስምንት ወር ሊሆን ይችላል።" ብለው ለአሥራ ስምንት ወራት (ለአንድ ዓመት ከስድስት ወር) ቆመው ተጉ። አሁንም ግን ሞት የውኃ ሽታ ሆኖ ቀረ።
ይህን ጊዜ ግን ወደ ፈጣሪ ለመኑ። "ጌታዬ! ያልከኝ ምን አሥራ ስምንት ነው?"
ቅዱስ መልአኩም መጥቶ "አቡፋና ሆይ! የቀረህ አሥራ ስምንት ዓመት ነውና ጽና።" ብሏቸው ተሰወረ። ልብ በሉልኝ "እስክሞት አልቀመጥም።" ብለው ተስለዋል።
ቅዱሱ ገዳማዊ በቃላቸው የሚገኙ እውነተኛ ክርስቲያን ነበሩና ለአሥራ ስምንት ዓመታት እንደተተከለ ምሰሶ ቆመው ጸለዩ፣ ጾሙ። እንዲህ ያሉትን ቅዱሳን ሊቃውንት፦
"ሰላም ለከ ጽኑዕ ከመ ዓምድ
ዘኢያንቀለቅሎ ሞገድ።"
[ማዕበለ ዓለም የማያናውጸው ብርቱ ምሰሶ ሆይ! ምስጋና ይገባሃል።] የሚሏቸው።
ስለ ቅዱሱ የተጻፈ አርኬም ፦
"ሰላም ለቁመተ አቡፋና ዘአልቦ ኑታጌ
እስከ ተመሰለ እግሩ ከመ እግረ ነጌ።" ይላል። ከመቆም ብዛት አካላቸው ደቆ እግራቸው የዝሆን እግር እስኪመስል ወፍሮ ነበርና።
† አባ አቡፋና በዘመናቸው ብዙ ተአምራትን ሠርተው በዚህች ቀን አርፈዋል።
🕊 † ቅዱስ እንጦኒ ሐዲስ ሰማዕት † 🕊
† ቅዱስ እንጦኒ [Anthony] በትውልዱ ከሶርያ ዐረቦች ሲሆን በቀደመ ሕይወቱ ክርስቲያኖችን ያሳድድ ፣ ካህናትን ይደበድብ ፣ አብያተ ክርስቲያናትንም ያቃጥል ነበር። እግዚአብሔር በንስሐ ሲጠራው ግን ደግ ፣ ጻድቅና ምርጥ ዕቃ ሆኖ ተገኘ። በመጨረሻም ከብዙ መከራ በኋላ ለሰማዕትነት በቅቷል።
† አምላከ ቅዱሳን የወዳጆቹን ትጋት፣ ጽናት፣ ፍቅርና በረከት ያድለን። ከማስተዋልም አያጉድለን።
🕊
[ † የካቲት ፳፭ [ 25 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]
፩. ቅዱስ አባ አቡፋና ጻድቅ
፪. ቅዱስ እንጦኒ ሐዲስ ሰማዕት
፫. ቅዱሳን ሰማዕታት አውሳንዮስ፣ ፊልሞናና ሉቅያ ድንግል [የቅዱስ ጳውሎስ ሐዋርያ ደቀ መዛሙርት]
፬. ቅዱስ ቶና ዲያቆንና ሰማዕት
፭. ቅዱስ ሚናስ ዘሃገረ ቁስ
[ † ወርኀዊ በዓላት ]
፩. ቅዱስ መርቆሬዎስ ሰማዕት
፪. ቅድስት ቴክላ ሐዋርያዊት
፫. ቅዱስ አበከረዙን ሰማዕት
፬. ቅዱስ ዱማድዮስ ሶርያዊ
፭. አቡነ አቢብ [ አባ ቡላ ]
† " ኃይል የሰጠኝን ክርስቶስ ኢየሱስን ጌታችንን አመሰግናለሁ። አስቀድሞ ተሳዳቢና አሳዳጅ አንገላችም ምንም ብሆን ይህን አደረገልኝ። ነገር ግን ሳላውቅ ባለማመን ስላደረግሁት ምሕረትን አገኘሁ።" † [፩ጢሞ ፩፥፲፪-፲፫]
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† † †
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
💖 🕊 💖
👍4