🕊
[ † እንኳን ለቅዱሳን ጻድቃነ ዴጌ ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ ፤ አደረሰን። † ]
† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን ! †
🕊 † ጻድቃነ ዴጌ † 🕊
† እነዚህ ጻድቃን ኢትዮዽያውያን ባይሆኑም ያበሩት በሃገራችን ነው:: ቅዱሳኑ በቁጥር ፫ ሺህ [3,000] : በዜግነት ሮማውያን ናቸው:: ከሺህ አዝማናት በፊት ከሮም ግዛት ተሰባስበው እንደ ተስዓቱ ቅዱሳን ወደ ኢትዮዽያ [አክሱም] መጥተዋል::
ቀጥለውም እዛው አካባቢ ወደሚገኝ ገዳም ገብተዋል:: ይህ ቦታ ለአክሱም ቅርብ ሲሆን በዘመነ ሐዋርያት የቅዱስ ማቴዎስ ወንጌላዊ በዓት ነበር:: የሐዋርያው በትረ መስቀልም እስካሁን አለች::
ጻድቃነ ዴጌ ሕጋቸው አንዲት : እርሷም ፍቅር ናት:: ለዘመናት በፍቅረ ክርስቶስ ታሥረው : ፍቅርን ለብሰው : በፍቅር ኑረዋል:: ሁሌም በ፳፱ [29] የጌታችንን ስም እየጠሩ ጽዋ ጠጥተዋል:: ስለ ፍቅራቸውም ጌታችን ፫ ሺህ ፩ኛ [3,001] ኛ ሆኖ : ነዳይ መስሎ አብሯቸው ጠጥቷል::
በመጨረሻም ፫ ሺው በአንድነት ተሠውረዋል::
† ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን:: እኛንም በወዳጆቹ ጸሎት ይማረን:: . . .አሜን !
🕊
[ † ጥር ፳፱ [ 29 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]
፩. ጻድቃን ቅዱሳን ማሕበረ ዶጌ [ዴጌ ጻድቃን]
[አክሱም አካባቢ በቁጥር ወደ ፫ ሺህ [3,000] ሲሆኑ ከመድኃኔ ዓለም ጋር ማሕበር ይጠጡ የነበሩና በአንድ ላይ የተሠወሩ ቅዱሳን ናቸው]
፪. አባ ገብረ ናዝራዊ ዘቃውንት [ኢትዮዽያዊ]
፫. ቅድስት አክሳኒ ፈላሲት
፬. ቅዱስ ሰርያኮስ ሰማዕት
፭. አባ እስጢፋኖስ ገዳማዊ
፮. ከድሮዋ ሮም የተነሱ ቅዱሳት አንስት
[ † ወርሐዊ በዓላት ]
፩. ቅድስት አርሴማ ሰማዕት
፪. ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ እናታችን
፫. ቅዱስ ዼጥሮስ ተፍፃሜተ ሰማዕት
፬. ቅዱስ ማርቆስ ዘቶርማቅ
፭. ቅዱስ ዘርዐ ክርስቶስ
† " ጻድቃን ምድርን ይወርሳሉ:: በእርስዋም ለዘለዓለም ይኖራሉ:: የጻድቅ አፍ ጥበብን ያስተምራል:: አንደበቱም ፍርድን ይናገራል:: የአምላኩ ሕግ በልቡ ውስጥ ነው:: በእርምጃውም አይሰናከልም:: " † [መዝ.፴፮፥፳፱]
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† † †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖 🕊 💖
[ † እንኳን ለቅዱሳን ጻድቃነ ዴጌ ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ ፤ አደረሰን። † ]
† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን ! †
🕊 † ጻድቃነ ዴጌ † 🕊
† እነዚህ ጻድቃን ኢትዮዽያውያን ባይሆኑም ያበሩት በሃገራችን ነው:: ቅዱሳኑ በቁጥር ፫ ሺህ [3,000] : በዜግነት ሮማውያን ናቸው:: ከሺህ አዝማናት በፊት ከሮም ግዛት ተሰባስበው እንደ ተስዓቱ ቅዱሳን ወደ ኢትዮዽያ [አክሱም] መጥተዋል::
ቀጥለውም እዛው አካባቢ ወደሚገኝ ገዳም ገብተዋል:: ይህ ቦታ ለአክሱም ቅርብ ሲሆን በዘመነ ሐዋርያት የቅዱስ ማቴዎስ ወንጌላዊ በዓት ነበር:: የሐዋርያው በትረ መስቀልም እስካሁን አለች::
ጻድቃነ ዴጌ ሕጋቸው አንዲት : እርሷም ፍቅር ናት:: ለዘመናት በፍቅረ ክርስቶስ ታሥረው : ፍቅርን ለብሰው : በፍቅር ኑረዋል:: ሁሌም በ፳፱ [29] የጌታችንን ስም እየጠሩ ጽዋ ጠጥተዋል:: ስለ ፍቅራቸውም ጌታችን ፫ ሺህ ፩ኛ [3,001] ኛ ሆኖ : ነዳይ መስሎ አብሯቸው ጠጥቷል::
በመጨረሻም ፫ ሺው በአንድነት ተሠውረዋል::
† ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን:: እኛንም በወዳጆቹ ጸሎት ይማረን:: . . .አሜን !
🕊
[ † ጥር ፳፱ [ 29 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]
፩. ጻድቃን ቅዱሳን ማሕበረ ዶጌ [ዴጌ ጻድቃን]
[አክሱም አካባቢ በቁጥር ወደ ፫ ሺህ [3,000] ሲሆኑ ከመድኃኔ ዓለም ጋር ማሕበር ይጠጡ የነበሩና በአንድ ላይ የተሠወሩ ቅዱሳን ናቸው]
፪. አባ ገብረ ናዝራዊ ዘቃውንት [ኢትዮዽያዊ]
፫. ቅድስት አክሳኒ ፈላሲት
፬. ቅዱስ ሰርያኮስ ሰማዕት
፭. አባ እስጢፋኖስ ገዳማዊ
፮. ከድሮዋ ሮም የተነሱ ቅዱሳት አንስት
[ † ወርሐዊ በዓላት ]
፩. ቅድስት አርሴማ ሰማዕት
፪. ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ እናታችን
፫. ቅዱስ ዼጥሮስ ተፍፃሜተ ሰማዕት
፬. ቅዱስ ማርቆስ ዘቶርማቅ
፭. ቅዱስ ዘርዐ ክርስቶስ
† " ጻድቃን ምድርን ይወርሳሉ:: በእርስዋም ለዘለዓለም ይኖራሉ:: የጻድቅ አፍ ጥበብን ያስተምራል:: አንደበቱም ፍርድን ይናገራል:: የአምላኩ ሕግ በልቡ ውስጥ ነው:: በእርምጃውም አይሰናከልም:: " † [መዝ.፴፮፥፳፱]
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† † †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖 🕊 💖
🙏1
#_______ፀሎት
#ፀሎት ልማድህ ሲሆን ተአምራቶች የህይወትህ ዘይቤ ይሆናሉ።
#ፀሎት የሰው ልጅ ካለምንም የአለማዊ ኔትዎርክ ዝርጋታ በቀጥታ #ከእግዚአብሔር ጋር የምንነጋገርበት የመገናኛ መስመር ነው።
#ፀሎት ዘር ነውና መኸር አለው፣
#ፀሎት እንባ ነውና ሳቅ አለው፣
#ፀሎት ትግል ነውና ድል አለው፣
#ፀሎት ጩኸት ነውና መልስ አለው፣
#ፀሎት መንበርከክ ነውና ማሸነፍ አለው
በእግዚአብሔር ፊት #የሚንብረከክ ሰው በማንኛውም ሁኔታ ውስጥ መቆም ይችላል።
#በፀሎት የማይቻለው ይቻላል🙏🙏🙏
#መልካም__ቀን🙏
አጫጭር ኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶች
•➢ 👇 ለማግኘት // 👇
@Enatachn_mareyam
@Enatachn_mareyam
#ፀሎት ልማድህ ሲሆን ተአምራቶች የህይወትህ ዘይቤ ይሆናሉ።
#ፀሎት የሰው ልጅ ካለምንም የአለማዊ ኔትዎርክ ዝርጋታ በቀጥታ #ከእግዚአብሔር ጋር የምንነጋገርበት የመገናኛ መስመር ነው።
#ፀሎት ዘር ነውና መኸር አለው፣
#ፀሎት እንባ ነውና ሳቅ አለው፣
#ፀሎት ትግል ነውና ድል አለው፣
#ፀሎት ጩኸት ነውና መልስ አለው፣
#ፀሎት መንበርከክ ነውና ማሸነፍ አለው
በእግዚአብሔር ፊት #የሚንብረከክ ሰው በማንኛውም ሁኔታ ውስጥ መቆም ይችላል።
#በፀሎት የማይቻለው ይቻላል🙏🙏🙏
#መልካም__ቀን🙏
አጫጭር ኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶች
•➢ 👇 ለማግኘት // 👇
@Enatachn_mareyam
@Enatachn_mareyam
❤11🙏4
💛
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
[ የመርሐ-ግብር ማሳወቂያ ! ]
🕊
[ 💖 መንፈሳዊው መሰላል 💖 ]
እንደ እግዚአብሔር መልካም ፈቃድ ከፊታችን ሰኞ ጀምሮ በቀኑ መርሐ-ግብር የቅዱስ ዮሐንስ ክሊማኮስ [ ቅዱስ ዮሐንስ ዘሰዋስው ] ድርሳን ላይ "መንፈሳዊው መሰላል" በሚል ርዕስ የቀረበው ትምህርትና ድንቅ ምክር ለንባብ እንዲመች እየተመጠነ የሚቀርብ ይሆናል።
በመርሐ-ግብሩ ወደ እግዚአብሔር ለመድረስ ልንወጣ ስለሚገባን የቅድስና መሰላልና የንጽሕና ሕይወት ጉዞ አስደናቂ ትምህርቶችን የምናገኝበት ነው፡፡
[ 🕊 መንፈሳዊው መሰላል 🕊 ]
- ተከታታይ መርሐ-ግብር
- ከፊታችን ሰኞ ጀምሮ
- ከቀኑ ፱ ሰዓት [ 09:00 ] ላይ
🕊 💖 🕊
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
[ የመርሐ-ግብር ማሳወቂያ ! ]
🕊
[ 💖 መንፈሳዊው መሰላል 💖 ]
እንደ እግዚአብሔር መልካም ፈቃድ ከፊታችን ሰኞ ጀምሮ በቀኑ መርሐ-ግብር የቅዱስ ዮሐንስ ክሊማኮስ [ ቅዱስ ዮሐንስ ዘሰዋስው ] ድርሳን ላይ "መንፈሳዊው መሰላል" በሚል ርዕስ የቀረበው ትምህርትና ድንቅ ምክር ለንባብ እንዲመች እየተመጠነ የሚቀርብ ይሆናል።
በመርሐ-ግብሩ ወደ እግዚአብሔር ለመድረስ ልንወጣ ስለሚገባን የቅድስና መሰላልና የንጽሕና ሕይወት ጉዞ አስደናቂ ትምህርቶችን የምናገኝበት ነው፡፡
[ 🕊 መንፈሳዊው መሰላል 🕊 ]
- ተከታታይ መርሐ-ግብር
- ከፊታችን ሰኞ ጀምሮ
- ከቀኑ ፱ ሰዓት [ 09:00 ] ላይ
🕊 💖 🕊
❤6👍1
†
[ 🕊 ፍኖተ ቅዱሳን 🕊 ]
[ የቅዱሳን አባቶቻችን የቅድስናና የተጋድሎ ሕይወት ]
▬▬▬▬▬▬ † ▬▬▬▬▬▬
[ ትሕትና ! ]
------------------------------------------
❝ አባ ኤስድሮስ እንዲህ አለ ፦ ሁል ጊዜ የምትጾም ከሆነ በትዕቢት ራስህን ወደ ላይ አታውጣ ፤ ከዚህ የተነሣ ራስህን ከፍ አድርገህ የምትመለከት ከሆነ ግን ሥጋ ብትበላ ይሻልሃል፡፡ ለአንድ ሰው ራሱን በትዕቢት ከመንፋትና ራሱን ከማክበር ሥጋ ቢበላ ይሻለዋልና፡፡ ❞
-------------------------------------------
❝ ቅድስት ሰንቀሌጢቃ እንዲህ አለች ፦ "መርከብ ያለ ምስማር ሊሠራ እንደማይችል ሁሉ ድኅነትም [ መዳንም ] ያለ ትሕትና ሊገኝ አይችልም፡፡ " ❞
--------------------------------------------
ለአባ ዮሐንስ ፦ " ሰውች መላእክትን አየናቸው ይላሉ። " አሉት። እርሱም ፦ " ብፁዕስ ሁል ጊዜ ኃጢአቱን የሚያይ ሰው ነው።" አላቸው
-------------------------------------------
🕊
የደጋግ አባቶቻችን ጸሎትና በረከት ይደርብን፡፡
† † †
💖 🕊 💖
[ 🕊 ፍኖተ ቅዱሳን 🕊 ]
[ የቅዱሳን አባቶቻችን የቅድስናና የተጋድሎ ሕይወት ]
▬▬▬▬▬▬ † ▬▬▬▬▬▬
[ ትሕትና ! ]
------------------------------------------
❝ አባ ኤስድሮስ እንዲህ አለ ፦ ሁል ጊዜ የምትጾም ከሆነ በትዕቢት ራስህን ወደ ላይ አታውጣ ፤ ከዚህ የተነሣ ራስህን ከፍ አድርገህ የምትመለከት ከሆነ ግን ሥጋ ብትበላ ይሻልሃል፡፡ ለአንድ ሰው ራሱን በትዕቢት ከመንፋትና ራሱን ከማክበር ሥጋ ቢበላ ይሻለዋልና፡፡ ❞
-------------------------------------------
❝ ቅድስት ሰንቀሌጢቃ እንዲህ አለች ፦ "መርከብ ያለ ምስማር ሊሠራ እንደማይችል ሁሉ ድኅነትም [ መዳንም ] ያለ ትሕትና ሊገኝ አይችልም፡፡ " ❞
--------------------------------------------
ለአባ ዮሐንስ ፦ " ሰውች መላእክትን አየናቸው ይላሉ። " አሉት። እርሱም ፦ " ብፁዕስ ሁል ጊዜ ኃጢአቱን የሚያይ ሰው ነው።" አላቸው
-------------------------------------------
🕊
የደጋግ አባቶቻችን ጸሎትና በረከት ይደርብን፡፡
† † †
💖 🕊 💖
❤1🥰1
🕊
[ † እንኳን ለቅዱሳት አንስት ሶፍያ ወአዋልዲሃ: ኦርኒ ወማኅበራኒሃ እና ለሊቁ ቅዱስ ጐርጐርዮስ ነባቤ መለኮት ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን። † ]
† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †
🕊 † ቅድስት ሶፍያና ልጆቿ † 🕊
† በቤተ ክርስቲያን ታሪክ ታዋቂ ከሆኑ የእናቶቻችን ስሞች "ሶፍያ" ቀዳሚው ነው:: ቃሉ በጥሬው ሲተረጐም "ጥበብ [ጥበበ ክርስቶስ] Wisdom of God" ማለት ነው:: ከጻድቃንና ከሰማዕታት ወገን በዚህ ስም የተጠሩ እናቶች አሉ::
ከእነዚህ መካከል አንዷ የሆነችው በዕለቱ የምናስባት እናት ቁጥሯ ከሰማዕታት ነው:: ዋናው ዘመነ ሰማዕታት ከመጀመሩ በፊት የነበረችው ቅድስት ሶፍያ ከሕግ ትዳር ፫ ሴቶች ልጆችን አፍርታለች::
ስማቸውንም:- ጲስጢስ [ሃይማኖት] : አላጲስ [ተስፋ] : አጋጲስ [ፍቅር] ስትል ሰይማቸዋለች:: እንደሚገባም በሥርዓቱ አሳድጋ እድሜአቸው 9 : ፲ እና ፲፪ ሲደርስ ለሰማያዊ ሙሽርነት አጭታቸዋለች::
በዘመኑ "ክርስቶስን ካዱ" የሚል መሪ ተነስቶ ነበርና ቅዱሳቱ በመድኃኒታችን አምነው : ጣዖትን ዘልፈው አንገታቸውን ሰጥተዋል:: ክብረ ሰማዕትን : ሃገረ ክርስቶስንም ወርሰዋል::
🕊 † ቅድስት ኦርኒ ሰማዕት † 🕊
† "ኦርኒ" ማለት በምሥራቃውያን ልሳን "ሰላም" ማለት ነው:: ቅድስቲቱ አርበኛ የዘመነ ሐዋርያት የቤተ ክርስቲያን ፍሬ ስትሆን ተወልዳ ያደገችውም በቀድሞው የሮም ግዛት ውስጥ ነው::
ምንም ዛሬ ያለ ትውልድ ቢዘነጋት ቅድስት ኦርኒ ተወዳዳሪ የሌላት ሰማዕት : ሐዋርያዊት : ድንግል ናት:: እርሷ ውበቷን : ንግሥናዋን : ክብሯን : ሃብቷን : ወጣትነቷንና ያላትን ሁሉ ስለ ፍቅረ ክርስቶስ ሰውታለችና ክብርት ናት::
በ1ኛው መቶ ክ/ዘመን መጨረሻ አካባቢ ከሮም ቤተ መንግስት የተወለደችው ቅድስት ኦርኒ እስከ ወጣትነቷ ድረስ ክርስቶስን ልታውቀው አልተቻላትም ነበር:: ምክንያቱ ደግሞ ንጉሡ አባቷ ጣዖትን ማምለኩ ነበር::
ንግሥት እናቷ ምንም ክርስቲያን ብትሆንም ስለ ክርስትና ልትነግራት አልደፈረችም:: ይህን ብታደርግ የሚደርስባትን መከራ ታውቃለችና:: ግን ደግሞ ውስጥ ውስጡን ትጸልይላት ነበርና ፈጣሪ መንገዱን ሊከፍት ጀመረ::
መምለኬ ጣዖት አባቷ ሰው እንዳያያት ቤተ መንግስት ሠርቶ : ፲፪ ሞግዚቶችን መድቦ ጣዖት ከፊቷ አቁሞ ለዘመናት ዘጋት:: የሚገርመው ግን መልኳን እንዳያይ በበር ሆኖ የሚያስተምራት ፈላስፋ ተቀጥሮ ነበርና የዚህ ሰው ማንነቱ ነው::
መምለኬ ክርስቶስ ደግ ሰው ነበርና ፈሊጥን ይሻላት ገባ:: በዚህ መካከል ቅድስት ኦርኒ ራዕይን ታያለች:: የቤቷ መስኮቶች ተከፍተው ሳሉ በስተምሥራቅ ነጭ ርግብ : የዘይት [የወይራ] ዝንጣፊ ይዛ ገብታ : ከማዕዷ ላይ ጥላው ወጣች::
እርሷን ተከትሎ ቁራ በምዕራብ ገባ:: እባቡን ማዕዷ ላይ ጣለው:: በ3ኛው ደግሞ ንስር ገብቶ አክሊል ትቶላት ወጣ:: ቅድስቲቱም እየገረማት አረጋዊ መምህሯን "ተርጉምልኝ" አለችው::
† እርሱም :-
• ርግብ = ጥበብ [ መንፈስ ቅዱስ ]
• ዘይት = ጥምቀት
• ቁራ = ክፉ ንጉሥ
• እባብ = መከራ
• ንስር = ድል ነሺነት [ ልዑላዊነት ]
• አክሊልም = ክብረ ሰማዕታት ነው" ብሎ ተርጉሞ : ክርስቲያን ሆና ይህ ሁሉ እንደሚደረግ ነግሮ ተሰናበታት::
እርሷም ስትጸልይ ቅዱስ መልአክ ተገልጦ አጽናናት:: ያጠምቃትና ያስተምራት ዘንድም ሐዋርያው ቅዱስ ጢሞቴዎስን ልኮላታል:: ሐዋርያውም የቤተ መንግስቱን ግድግዳ ሰንጥቆ ገብቶ : ለሰማያዊ ሙሽርነት የሚያበቃ ትምህርትና ጥምቀትን ሰጥቷት ሔዷል::
ቅድስት ኦርኒም የአባቷን ጣዖታት ቀጥቅጣ ሰብራ ከአባቷ ጋር ተጣላች:: እርሱም "እገድላታለሁ" ብሎ በእንስሳት ጅራት ላይ ጸጉሯን ሲያስር እንስሶቹ ደንብረው : እጁን ገንጥለው መሬት ላይ ጥለው ገደሉት:: ቅድስት ኦርኒ ግን ጸሎት አድርሳ አባቷን ከሞት አስነሳችው:: እጁንም ቀጠለችለት::
በዚህ ምክንያት በዚያች ዕለት ብቻ አባቷና ፴ ሺህ [ 30,000 ] የከተማው አሕዛብ አምነው ተጠምቀዋል:: ቅድስት ኦርኒ ግን ኃይለ መንፈስ ቅዱስ ታጥቃ ክርስትናን ሰበከች:: ብዙም ተሰቃየች:: ንጉሡ ዳኬዎስ : ልጁና ሌሎች ፪ ያህል ነገሥታት በእሳት : በአራዊት : በግርፋትና በጦር ፈትነዋታል::
እርሷ ግን ሁሉን በኃይለ ክርስቶስ ድል ነስታለች:: ሙታም የተነሳችበት ጊዜ አለ:: በመጨረሻም በዚህች ቀን ወደ ሰማያዊ ርስት [ ገነት ] ተመስጣለች:: በዘመነ ስብከቷ ካሳመነቻቸው ባሻገር ፻፴ ሺህ [ 130,000 ] የሚያህሉ ሰዎች ለሰማዕትነት እንዲበቁም ምክንያት ሆናለች::
🕊 † ቅዱስ ጐርጐርዮስ ታኦሎጐስ † 🕊
† ቅዱሱ :-
• የዘመነ ሊቃውንት ፍሬ:
• የእንዚናዙ ኤጲስ ቆጶስ:
• የቁስጥንጥንያ ፓትርያርክ:
• የጉባዔ ቁስጥንጥንያ [ በ381 ዓ/ም] ፫ኛ ሊቀ መንበር:
• ባለ ብዙ ድርሳን:
• የቂሣርያ [ ቀጰዶቅያ ] ኮከብ:
• ብሩህ ገዳማዊ:
• መልካም እረኛ የነበረ አባት ነው::
መጽሐፈ ቅዳሴውን ጨምሮ በጻፋቸው ብዙ መጻሕፍትና በስብከቱ ከሊቃውንት ወገን "ታኦ(ዎ)ሎጐስ" ተብሎ የተጠራ እርሱ ብቻ ነው:: ትርጉሙም በግዕዙ "ነባቤ መለኮት" ማለት ነው:: በአማርኛም "አንድነትን : ሦስትነትን የተናገረ [ያመሠጠረ] እንደ ማለት ነው:: ቅዱሱ ዛሬ ዕረፍቱ ነው::
† አምላከ ቅዱሳን ከበረከታቸው ይክፈለን፡፡
በመጽናታቸውም ያጽናን፡፡
† እንዲህ ኃጢአታችን ጽዋዑን ሞልቶ በተረፈበት በዚህ ዘመን አንዲት ሰዓትም ውድ የሆነች የንስሃ ዕድሜ ናት:: እግዚአብሔር ግን ደግ ነውና ይሔው ጥርን አስፈጸመን:: ባይገባን ነው እንጂ በዚሕች ወር ውስጥ ሚሊየኖች በደዌ የአልጋ ቁራኛ ሁነዋል::
ሚሊየኖችም ለንስሃ ሳይበቁ እንዲሁ አንቀላፍተዋል [ሙተዋል]:: እስኪ እርሱ አምላካችን ቀሪውን ዘመን ደግሞ ለንስሃና ለመልካም ሥራ ባርኮ ይስጠን::
† ወርኀ ጥርን በቸር ያስፈፀመ አምላከ ቅዱሳን ወርኀ የካቲትን እንዲባርክልን እንለምነው::
🕊
[ † ጥር ፴ [ 30 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]
፩. ቅድስት ሶፍያና ሦስቱ ሰማዕታት ልጆቿ [ጲስጢስ አላጲስና አጋጲስ]
፪. ቅድስት ኦርኒ ሰማዕት [በ፭ ነገሥታት እጅ የተሰቃየች : የሐዋርያው ጢሞቴዎስ ተከታይና ወደ ብሔረ ሕያዋን የተነጠቀች እናት]
፫. ቅዱስ ጐርጐርዮስ ነባቤ መለኮት
፬. አባ አክርስጥሮስ
፭. አምስቱ ደናግል ሰማዕታት [ጤቅላ: ማርያ: ማርታ: አበያ: ዓመታ]
፮. ጻድቃነ ዴጌ [የተሠወሩበት]
፯. አባ ሚናስ ሊቀ ጳጳሳት
፰. ፻፴ ሺህ "130,000" ሰማዕታት [የቅድስት ኦርኒ ማኅበር]
[ † ወርኀዊ በዓላት ]
፩. ቅዱስ ማርቆስ ዘአንበሳ
፪. ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቀ መለኮት
፫. አባ ሣሉሲ ክቡር
† " ለእናንተም ጠጉርን በመሸረብና ወርቅን በማንጠልጠል ወይም ልብስን በመጐናጸፍ በውጭ የሆነ ሽልማት አይሁንላችሁ:: ነገር ግን በእግዚአብሔር ፊት ዋጋው እጅግ የከበረ የዋህና ዝግተኛ መንፈስ ያለውን የማይጠፋውን ልብስ ለብሶ የተሰወረ የልብ ሰው ይሁንላችሁ:: " † [ ፩ጴጥ. ፫፥፫ ]
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† † †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖 🕊 💖
[ † እንኳን ለቅዱሳት አንስት ሶፍያ ወአዋልዲሃ: ኦርኒ ወማኅበራኒሃ እና ለሊቁ ቅዱስ ጐርጐርዮስ ነባቤ መለኮት ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን። † ]
† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †
🕊 † ቅድስት ሶፍያና ልጆቿ † 🕊
† በቤተ ክርስቲያን ታሪክ ታዋቂ ከሆኑ የእናቶቻችን ስሞች "ሶፍያ" ቀዳሚው ነው:: ቃሉ በጥሬው ሲተረጐም "ጥበብ [ጥበበ ክርስቶስ] Wisdom of God" ማለት ነው:: ከጻድቃንና ከሰማዕታት ወገን በዚህ ስም የተጠሩ እናቶች አሉ::
ከእነዚህ መካከል አንዷ የሆነችው በዕለቱ የምናስባት እናት ቁጥሯ ከሰማዕታት ነው:: ዋናው ዘመነ ሰማዕታት ከመጀመሩ በፊት የነበረችው ቅድስት ሶፍያ ከሕግ ትዳር ፫ ሴቶች ልጆችን አፍርታለች::
ስማቸውንም:- ጲስጢስ [ሃይማኖት] : አላጲስ [ተስፋ] : አጋጲስ [ፍቅር] ስትል ሰይማቸዋለች:: እንደሚገባም በሥርዓቱ አሳድጋ እድሜአቸው 9 : ፲ እና ፲፪ ሲደርስ ለሰማያዊ ሙሽርነት አጭታቸዋለች::
በዘመኑ "ክርስቶስን ካዱ" የሚል መሪ ተነስቶ ነበርና ቅዱሳቱ በመድኃኒታችን አምነው : ጣዖትን ዘልፈው አንገታቸውን ሰጥተዋል:: ክብረ ሰማዕትን : ሃገረ ክርስቶስንም ወርሰዋል::
🕊 † ቅድስት ኦርኒ ሰማዕት † 🕊
† "ኦርኒ" ማለት በምሥራቃውያን ልሳን "ሰላም" ማለት ነው:: ቅድስቲቱ አርበኛ የዘመነ ሐዋርያት የቤተ ክርስቲያን ፍሬ ስትሆን ተወልዳ ያደገችውም በቀድሞው የሮም ግዛት ውስጥ ነው::
ምንም ዛሬ ያለ ትውልድ ቢዘነጋት ቅድስት ኦርኒ ተወዳዳሪ የሌላት ሰማዕት : ሐዋርያዊት : ድንግል ናት:: እርሷ ውበቷን : ንግሥናዋን : ክብሯን : ሃብቷን : ወጣትነቷንና ያላትን ሁሉ ስለ ፍቅረ ክርስቶስ ሰውታለችና ክብርት ናት::
በ1ኛው መቶ ክ/ዘመን መጨረሻ አካባቢ ከሮም ቤተ መንግስት የተወለደችው ቅድስት ኦርኒ እስከ ወጣትነቷ ድረስ ክርስቶስን ልታውቀው አልተቻላትም ነበር:: ምክንያቱ ደግሞ ንጉሡ አባቷ ጣዖትን ማምለኩ ነበር::
ንግሥት እናቷ ምንም ክርስቲያን ብትሆንም ስለ ክርስትና ልትነግራት አልደፈረችም:: ይህን ብታደርግ የሚደርስባትን መከራ ታውቃለችና:: ግን ደግሞ ውስጥ ውስጡን ትጸልይላት ነበርና ፈጣሪ መንገዱን ሊከፍት ጀመረ::
መምለኬ ጣዖት አባቷ ሰው እንዳያያት ቤተ መንግስት ሠርቶ : ፲፪ ሞግዚቶችን መድቦ ጣዖት ከፊቷ አቁሞ ለዘመናት ዘጋት:: የሚገርመው ግን መልኳን እንዳያይ በበር ሆኖ የሚያስተምራት ፈላስፋ ተቀጥሮ ነበርና የዚህ ሰው ማንነቱ ነው::
መምለኬ ክርስቶስ ደግ ሰው ነበርና ፈሊጥን ይሻላት ገባ:: በዚህ መካከል ቅድስት ኦርኒ ራዕይን ታያለች:: የቤቷ መስኮቶች ተከፍተው ሳሉ በስተምሥራቅ ነጭ ርግብ : የዘይት [የወይራ] ዝንጣፊ ይዛ ገብታ : ከማዕዷ ላይ ጥላው ወጣች::
እርሷን ተከትሎ ቁራ በምዕራብ ገባ:: እባቡን ማዕዷ ላይ ጣለው:: በ3ኛው ደግሞ ንስር ገብቶ አክሊል ትቶላት ወጣ:: ቅድስቲቱም እየገረማት አረጋዊ መምህሯን "ተርጉምልኝ" አለችው::
† እርሱም :-
• ርግብ = ጥበብ [ መንፈስ ቅዱስ ]
• ዘይት = ጥምቀት
• ቁራ = ክፉ ንጉሥ
• እባብ = መከራ
• ንስር = ድል ነሺነት [ ልዑላዊነት ]
• አክሊልም = ክብረ ሰማዕታት ነው" ብሎ ተርጉሞ : ክርስቲያን ሆና ይህ ሁሉ እንደሚደረግ ነግሮ ተሰናበታት::
እርሷም ስትጸልይ ቅዱስ መልአክ ተገልጦ አጽናናት:: ያጠምቃትና ያስተምራት ዘንድም ሐዋርያው ቅዱስ ጢሞቴዎስን ልኮላታል:: ሐዋርያውም የቤተ መንግስቱን ግድግዳ ሰንጥቆ ገብቶ : ለሰማያዊ ሙሽርነት የሚያበቃ ትምህርትና ጥምቀትን ሰጥቷት ሔዷል::
ቅድስት ኦርኒም የአባቷን ጣዖታት ቀጥቅጣ ሰብራ ከአባቷ ጋር ተጣላች:: እርሱም "እገድላታለሁ" ብሎ በእንስሳት ጅራት ላይ ጸጉሯን ሲያስር እንስሶቹ ደንብረው : እጁን ገንጥለው መሬት ላይ ጥለው ገደሉት:: ቅድስት ኦርኒ ግን ጸሎት አድርሳ አባቷን ከሞት አስነሳችው:: እጁንም ቀጠለችለት::
በዚህ ምክንያት በዚያች ዕለት ብቻ አባቷና ፴ ሺህ [ 30,000 ] የከተማው አሕዛብ አምነው ተጠምቀዋል:: ቅድስት ኦርኒ ግን ኃይለ መንፈስ ቅዱስ ታጥቃ ክርስትናን ሰበከች:: ብዙም ተሰቃየች:: ንጉሡ ዳኬዎስ : ልጁና ሌሎች ፪ ያህል ነገሥታት በእሳት : በአራዊት : በግርፋትና በጦር ፈትነዋታል::
እርሷ ግን ሁሉን በኃይለ ክርስቶስ ድል ነስታለች:: ሙታም የተነሳችበት ጊዜ አለ:: በመጨረሻም በዚህች ቀን ወደ ሰማያዊ ርስት [ ገነት ] ተመስጣለች:: በዘመነ ስብከቷ ካሳመነቻቸው ባሻገር ፻፴ ሺህ [ 130,000 ] የሚያህሉ ሰዎች ለሰማዕትነት እንዲበቁም ምክንያት ሆናለች::
🕊 † ቅዱስ ጐርጐርዮስ ታኦሎጐስ † 🕊
† ቅዱሱ :-
• የዘመነ ሊቃውንት ፍሬ:
• የእንዚናዙ ኤጲስ ቆጶስ:
• የቁስጥንጥንያ ፓትርያርክ:
• የጉባዔ ቁስጥንጥንያ [ በ381 ዓ/ም] ፫ኛ ሊቀ መንበር:
• ባለ ብዙ ድርሳን:
• የቂሣርያ [ ቀጰዶቅያ ] ኮከብ:
• ብሩህ ገዳማዊ:
• መልካም እረኛ የነበረ አባት ነው::
መጽሐፈ ቅዳሴውን ጨምሮ በጻፋቸው ብዙ መጻሕፍትና በስብከቱ ከሊቃውንት ወገን "ታኦ(ዎ)ሎጐስ" ተብሎ የተጠራ እርሱ ብቻ ነው:: ትርጉሙም በግዕዙ "ነባቤ መለኮት" ማለት ነው:: በአማርኛም "አንድነትን : ሦስትነትን የተናገረ [ያመሠጠረ] እንደ ማለት ነው:: ቅዱሱ ዛሬ ዕረፍቱ ነው::
† አምላከ ቅዱሳን ከበረከታቸው ይክፈለን፡፡
በመጽናታቸውም ያጽናን፡፡
† እንዲህ ኃጢአታችን ጽዋዑን ሞልቶ በተረፈበት በዚህ ዘመን አንዲት ሰዓትም ውድ የሆነች የንስሃ ዕድሜ ናት:: እግዚአብሔር ግን ደግ ነውና ይሔው ጥርን አስፈጸመን:: ባይገባን ነው እንጂ በዚሕች ወር ውስጥ ሚሊየኖች በደዌ የአልጋ ቁራኛ ሁነዋል::
ሚሊየኖችም ለንስሃ ሳይበቁ እንዲሁ አንቀላፍተዋል [ሙተዋል]:: እስኪ እርሱ አምላካችን ቀሪውን ዘመን ደግሞ ለንስሃና ለመልካም ሥራ ባርኮ ይስጠን::
† ወርኀ ጥርን በቸር ያስፈፀመ አምላከ ቅዱሳን ወርኀ የካቲትን እንዲባርክልን እንለምነው::
🕊
[ † ጥር ፴ [ 30 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]
፩. ቅድስት ሶፍያና ሦስቱ ሰማዕታት ልጆቿ [ጲስጢስ አላጲስና አጋጲስ]
፪. ቅድስት ኦርኒ ሰማዕት [በ፭ ነገሥታት እጅ የተሰቃየች : የሐዋርያው ጢሞቴዎስ ተከታይና ወደ ብሔረ ሕያዋን የተነጠቀች እናት]
፫. ቅዱስ ጐርጐርዮስ ነባቤ መለኮት
፬. አባ አክርስጥሮስ
፭. አምስቱ ደናግል ሰማዕታት [ጤቅላ: ማርያ: ማርታ: አበያ: ዓመታ]
፮. ጻድቃነ ዴጌ [የተሠወሩበት]
፯. አባ ሚናስ ሊቀ ጳጳሳት
፰. ፻፴ ሺህ "130,000" ሰማዕታት [የቅድስት ኦርኒ ማኅበር]
[ † ወርኀዊ በዓላት ]
፩. ቅዱስ ማርቆስ ዘአንበሳ
፪. ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቀ መለኮት
፫. አባ ሣሉሲ ክቡር
† " ለእናንተም ጠጉርን በመሸረብና ወርቅን በማንጠልጠል ወይም ልብስን በመጐናጸፍ በውጭ የሆነ ሽልማት አይሁንላችሁ:: ነገር ግን በእግዚአብሔር ፊት ዋጋው እጅግ የከበረ የዋህና ዝግተኛ መንፈስ ያለውን የማይጠፋውን ልብስ ለብሶ የተሰወረ የልብ ሰው ይሁንላችሁ:: " † [ ፩ጴጥ. ፫፥፫ ]
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† † †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖 🕊 💖
❤3👍1