tgoop.com/Esat_tv1/20828
Last Update:
ኤርትራ የፕሪቶርያውን የሰላም ስምምነት የማፍረስ ምንም ፍላጎት የላትም ሲሉ የኤርትራው የመረጃ ሚኒስተር አስታወቁ‼️
“የኤርትራ ጦር በኢትዮጵያ ትግራይ ክልል አለ” የሚለውና ተደጋጋሚ የሆነ በተወሰኑ አካላት የሚነሳ ውንጀላ ፍፁም ሀሰት እና ግጭት ለመቀስቀስ ምክንያት ለመፍጠር ነው፤ የኤርትራ ወታደሮች ሙሉ በሙሉ በሉዓላዊ ግዛታቸው ውስጥ ተሰማርተው ይገኛሉ ሲሉ አቶ የማነ ገብረመስቀል ገልፀዋል።
ሚኒስተሩ አክለው ከዚህ ቀደም በብዙ አጋጣሚዎች በማያሻማ መልኩ እንደተገለጸው፣ ኤርትራ የፕሪቶሪያን የሰላም ስምምነት ለማፍረስ ምንም ፍላጎት የላትም፤ በመሰረቱም ስምምነቱ የኢትዮጵያ የውስጥ ጉዳይ ነው ብለዋል።
በተመሳሳይ ኤርትራ በህወሓት የፖለቲካ አንጃዎች ውስጥ የተፈጠረውን የውስጥ ሽኩቻ የማባባስ ፍላጎት የላትም ይህም በትግራይ ህዝብ ላይ አላስፈላጊ እና ሊወገድ የማይችል ስቃይ ያስከትላል ሲሉ ተደምጠዋል።
በቀይ ባህር ዙሪያ የተለያዩ የኢትዮጵያ የፖለቲካ ሃይሎች ሌት ተቀን የሚያወጡት የማያቋርጥ ግጭት ቀስቃሽ መግለጫዎች ለአላስፈላጊ ውጥረቱ አባባሽ ምክንያት ሆነው ቀጥለዋል ያሉ ሲሆን ይህ ያለምንም ማወላወል በጠንካራ ሁኔታ መወገዝ አለበት ሲሉም የኤርትራው የመረጃ ሚኒስተር አቶ የማነ ገብረመስቀል በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ባጋሩት መልእክት አስታውቀዋል።
@Esat_tv1
@Esat_tv1
BY ESAT (ኢሳት🇪🇹)®

Share with your friend now:
tgoop.com/Esat_tv1/20828