ETHIO_BETECRSTIAN Telegram 5040


የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ድርሳን ስለ ጌታችን ጥምቀት


እነሆ በዚች ዕለት በውኃ በመንፈስ ቅዱስና በእሳት እጠመቃለሁ፡፡ ውኃው የኃጢአትን እድፍ የማጠራበት ነው፡፡ በመንፈስ ቅዱስም መሬታውያኑን ሰማያውያን አደርግበታለሁ፡፡ በእሳቱም የኃጢአት እሾህን አቃጥልበታለሁ።

ዮሐንስም ይህን ነገር በሰማ ጊዜ በታላቅ ፍርሀትና መንቀጥቀጥ በብዙ ትሕትናም በጌታ ኢየሱስ ራስ ላይ እጁን ዘርግቶ አጠመቀው፡፡ ሰነፎች አይሁድ ይህን ባዩ ጊዜ ዮሐንስ ከክርስቶስ ይልቅ እጅግ ይከብራል፡፡ ክርስቶስም ከእርሱ ያንሳል፡፡ እንዲህስ ባይሆን ኑሮ ከእርሱ ባልተጠመቀም ነበር አሉ፡፡

እግዚአብሔር አብም የአይሁድን ሐሳብ ያውቃልና ይህችን ሐሳብ ከልቡናቸው ያርቅ ዘንድና እርሱ በመለኮቱ ክብር ከእርሱ ጋር አንድ የሆነ የሚወደው ልጁ እንደ ሆነ ያስረዳቸው ዘንድ ወደደ፡፡

ስለዚህ ሰማይን ከፍቶ መንፈስ ቅዱስን በርግብ አምሳል ሰደደ፡፡ በራሱ ላይም ተቀመጠ፡፡ በታላቅ ቃልም በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው ብሎ ተናገረ። ዳግመኛም በሥጋ የተወለደው እርሱ በመለኮቱ ክብር ከእኔ ጋር አንድ ነው፡፡ ከቀደመ ግብሩ ሳይለወጥ ሰው ሆኗልና፡፡ እኔ የወለድሁት ማርያም ከወለደችው የተለየ አይደለም፡፡ በጎል የተኛው ሰብአ ሰገል ከሰገዱለት ልዩ አይደለም፡፡ እርሱ በኔ ህልው ነው፡፡ እኔም በእርሱ ህልው ነኝ፡፡

በሥጋውም ተገልጦ ይታያል፤ በመለኮቱ ተኣምራትን ያደርጋል፡፡ ከማርያም በሥጋ ለተወለደው ልደቱ አባትን አትፈልጉ፡፡ ከዓለም ሁሉ በፊት ከኔ ለተወለደው ልደቱም እናትን አትመርምሩ፡፡ መለኮቱንም ከትስብእቱ አትለዩ፡፡

በእርሱ መጨመርና መለየት የለበትምና፡፡ ክርስቶስ ብቻውን አምላክ ብቻውንም ሰው አይምሰላችሁ፡፡ ሰው የሆነ አምላክ ነው እንጂ፡፡ የዓለም ሁሉ መድኃኒት ወልድ ዋሕድ በተጠመቀ ጊዜ እግዚአብሔር አብ እንዲህ በማለት ተናገረ።

ዳግመኛም የወልድ ፊቱ በደብረ ታቦር በተለወጠ፣ መልኩም እንደ ፀሐይ በደቀ መዛሙርቱ ፊት ባበራ ጊዜ እግዚአብሔር አብ እንዲህ አለው፡፡ ‹‹በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው፡፡ እርሱን ስሙት››፡፡

ይቀጥላል.....

(ድርሳነ ሠለስቱ ሊቃውንት በመምህር ቃለጽድቅ ሕግነህ የተተረጎመ ገጽ 55-67)

#ይቀላቀሉን!
@Ethio_Betecrstian



tgoop.com/Ethio_Betecrstian/5040
Create:
Last Update:



የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ድርሳን ስለ ጌታችን ጥምቀት


እነሆ በዚች ዕለት በውኃ በመንፈስ ቅዱስና በእሳት እጠመቃለሁ፡፡ ውኃው የኃጢአትን እድፍ የማጠራበት ነው፡፡ በመንፈስ ቅዱስም መሬታውያኑን ሰማያውያን አደርግበታለሁ፡፡ በእሳቱም የኃጢአት እሾህን አቃጥልበታለሁ።

ዮሐንስም ይህን ነገር በሰማ ጊዜ በታላቅ ፍርሀትና መንቀጥቀጥ በብዙ ትሕትናም በጌታ ኢየሱስ ራስ ላይ እጁን ዘርግቶ አጠመቀው፡፡ ሰነፎች አይሁድ ይህን ባዩ ጊዜ ዮሐንስ ከክርስቶስ ይልቅ እጅግ ይከብራል፡፡ ክርስቶስም ከእርሱ ያንሳል፡፡ እንዲህስ ባይሆን ኑሮ ከእርሱ ባልተጠመቀም ነበር አሉ፡፡

እግዚአብሔር አብም የአይሁድን ሐሳብ ያውቃልና ይህችን ሐሳብ ከልቡናቸው ያርቅ ዘንድና እርሱ በመለኮቱ ክብር ከእርሱ ጋር አንድ የሆነ የሚወደው ልጁ እንደ ሆነ ያስረዳቸው ዘንድ ወደደ፡፡

ስለዚህ ሰማይን ከፍቶ መንፈስ ቅዱስን በርግብ አምሳል ሰደደ፡፡ በራሱ ላይም ተቀመጠ፡፡ በታላቅ ቃልም በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው ብሎ ተናገረ። ዳግመኛም በሥጋ የተወለደው እርሱ በመለኮቱ ክብር ከእኔ ጋር አንድ ነው፡፡ ከቀደመ ግብሩ ሳይለወጥ ሰው ሆኗልና፡፡ እኔ የወለድሁት ማርያም ከወለደችው የተለየ አይደለም፡፡ በጎል የተኛው ሰብአ ሰገል ከሰገዱለት ልዩ አይደለም፡፡ እርሱ በኔ ህልው ነው፡፡ እኔም በእርሱ ህልው ነኝ፡፡

በሥጋውም ተገልጦ ይታያል፤ በመለኮቱ ተኣምራትን ያደርጋል፡፡ ከማርያም በሥጋ ለተወለደው ልደቱ አባትን አትፈልጉ፡፡ ከዓለም ሁሉ በፊት ከኔ ለተወለደው ልደቱም እናትን አትመርምሩ፡፡ መለኮቱንም ከትስብእቱ አትለዩ፡፡

በእርሱ መጨመርና መለየት የለበትምና፡፡ ክርስቶስ ብቻውን አምላክ ብቻውንም ሰው አይምሰላችሁ፡፡ ሰው የሆነ አምላክ ነው እንጂ፡፡ የዓለም ሁሉ መድኃኒት ወልድ ዋሕድ በተጠመቀ ጊዜ እግዚአብሔር አብ እንዲህ በማለት ተናገረ።

ዳግመኛም የወልድ ፊቱ በደብረ ታቦር በተለወጠ፣ መልኩም እንደ ፀሐይ በደቀ መዛሙርቱ ፊት ባበራ ጊዜ እግዚአብሔር አብ እንዲህ አለው፡፡ ‹‹በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው፡፡ እርሱን ስሙት››፡፡

ይቀጥላል.....

(ድርሳነ ሠለስቱ ሊቃውንት በመምህር ቃለጽድቅ ሕግነህ የተተረጎመ ገጽ 55-67)

#ይቀላቀሉን!
@Ethio_Betecrstian

BY 🇨🇬 ደጉ ሳምራዊ (ኢትዮጵና ቅድስት ቤተክርስቲያን )


Share with your friend now:
tgoop.com/Ethio_Betecrstian/5040

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

"Doxxing content is forbidden on Telegram and our moderators routinely remove such content from around the world," said a spokesman for the messaging app, Remi Vaughn. In handing down the sentence yesterday, deputy judge Peter Hui Shiu-keung of the district court said that even if Ng did not post the messages, he cannot shirk responsibility as the owner and administrator of such a big group for allowing these messages that incite illegal behaviors to exist. With the sharp downturn in the crypto market, yelling has become a coping mechanism for many crypto traders. This screaming therapy became popular after the surge of Goblintown Ethereum NFTs at the end of May or early June. Here, holders made incoherent groaning sounds in late-night Twitter spaces. They also role-played as urine-loving Goblin creatures. It’s easy to create a Telegram channel via desktop app or mobile app (for Android and iOS): How to Create a Private or Public Channel on Telegram?
from us


Telegram 🇨🇬 ደጉ ሳምራዊ (ኢትዮጵና ቅድስት ቤተክርስቲያን )
FROM American