tgoop.com/Habibacalligraphy/1917
Last Update:
ለአዛኗ ስትሉ!
(ፉአድ ሙና)
.
ለጁሙዓ ሰላት ወደ መስጂድ ጎራ ማለቴ ነበር። ያረፈድኩ መስሎኛል። ወደ መስጂድ ስገባ ከአንድ አባት ውጪ ማንም እንደሌለ ታዘብኩ። ትንሽ ግራ ስለገባኝ ነጭ ጀለቢያ ለብሰው ወንበር ላይ የተጠቀመጡትን ጠና ያሉ ሰው ጠጋ ብዬ ጠየቅኳቸው።
«Isn't it a time for Jumua prayer?"
ሰውየው ፈገግ ብለው ከየት ሀገር እንደመጣሁ ጠየቁኝ። አጫወትኳቸው። ስለራሳቸው አጫወቱኝና «The Khutba will start at 15:10.» አሉኝ። ለአስር ሰላት አንድ ሰዓት ተኩል ሲቀረው መሆኑ ነው። ከጁሙዓ ኹጥባ ከአራት ሰዓታት በላይ ቀድሜ እንደመጣሁ ገባኝ።
ቁርዓን ከፍቼ እየቀራሁ እያለ እኚህ ሱማሌ አባት ወደ ጎኔ መጥተው ሻይ እፈልግ እንደሆን ጠየቁኝ። አመስግኜ እንደማልፈልግ ነገርኳቸው። በዚሁ ቀጥለን ማውጋት ጀመርን።
«I miss Azan so much!» አልኳቸው።
ሰውነታቸው እየተርገፈገፈ «You didn't! You didn't!!» አሉ። በእጃቸው ዝም እንድል ምልክት እየሰጡኝ ነበር። ግራ ገብቶኝ ስመለከታቸው አይናቸው እየደፈረሰ ከሀገሬ ከወጣሁ ምን ያህል ጊዜ እንደሆነኝ ደግመው ጠየቁኝ ። በቅርቡ እንደሆነ ነገርኳቸው።
«I didn't listen to the azan for more than twenty years. .... You didn't miss the azan! You didn't!» አሉኝ።
ልቤ ተፈረካከሰ። በጣም አሳዘኑኝ። ፊታቸው ላይ ያየሁት የናፍቆት እሳት ተጋባኝ። ሀያ አመታት ያለ አዛን ድምፅ? እንኳን እምነቴ አካሌ በንኖ የሚጠፋ መሰለኝ።
ከትካዜዬ ስመለስ ወደ ሀገራቸው መመለስ ይፈልጉ እንደሆን ጠየቅኳቸው።
«Africa is a war front. War is raging all over the continent.» አሉ።
ሀገሬን አሰብኳት። እንደሳቸው የምመለስበት የሌለኝ ብሆንስ ብዬ ተጨነቅኩ።ሀገራችን ውስጥ ያለው ግጭት ወደ የት እየወሰደን እንደሆነ ሳስብ ነገ የእርሳቸው እጣ ፈንታ ቢደርሰኝስ ብዬ ሰጋሁ።
ሀገራችሁን ጠብቋት ... ለአዛኗ ስትሉ!
አላሁመ ሰሊም! ሰሊም!
®️Fuadmuna
🎨 @Habibacalligraphy
BY Habiba Calligraphy
Share with your friend now:
tgoop.com/Habibacalligraphy/1917