HABIBACALLIGRAPHY Telegram 1939
የባከኑ ቀናት
ክፍል አራት
(ሂባ ሁዳ)
.
.
<<ምን በተማሪ ፊት?>> ኢክሩ ደንግጣ ራቢና ዩሲን አፈራርቃ እያየች።
<<አዎ ኢክሩ አደንግጪ። በዛ ላይ የምሣ ሰዐት ደርሶ ስለነበረ ብዙ ተማሪ ተሰብስቦ ነበር። በሬው ደንግጦ ሱሪው ከፍ ሲያደርግ አስተማሪው <አውርድ!> አለውና ለተወሰነ ደቂቃ እንደዛው እንዳስቆመው።
<ሌላ ምን እንዲቀጣ ትፈሊጊያለሽ?> ራቢን ጠየቃት።
<ቅጣት ይበቃዋል፤ ግን ለኔ ሂጃብ ማለት ለእሱ አውራውን ከሚሸፍንበት ሱሪ በላይ ነው። ማንም ሰው በሂጃቤ እንዲጫወትበት አልፈቅድለትም። የከፋ ችግር ይገጥመዋል፤ ስለዚህ አርፎ ይቀመጥ። ተገቢውን ቅጣት በተማሪ ፊት መሰጠቱ ለሌሎች ትምህርት ነው። እኔ ማንም ይሁን ማንም ሂጃቤን አይደለም እጄን እንኳን እንዲነካኝ አልፈቅድለትም። አመሰግናለሁ> አለች። እኛ ከዛ ቦታ ዞር ብንልም ለትምህርት ቤቱ የሣምንት መነጋገሪያ ሆነ። ክፍል ሲገባም እነ ባቢ የሌለ ሙድ ይይዙበት ነበር። እኛም ከነ ባቢ ጋር በደንብ ተግባባን። ታዲያ ይሄ በረከትን(በሬው) እልህ ውስጥ ከተተው፤ ዝም ብሎ ነገር ይፈልጋት ጀመር። መጣላት እንደሚፈልግ ያስታውቅበት ነበር። የሆነ ቀን እኔን ጠራኝ እና በተማሪው ፊት ይቅርታ እንድትጠይቀው ካልሆነ እንደሚመታት ነገረኝ።>>
<<ጭራሽ እሷ ይቅርታ ልትጠይቀው ማለት ነው?? ኧረ ሞራል ..>> በስሜት አብሬ ለፈለፍኩ። ኢክሩ ራቢን ያቀፈችበት እጇን ወደኔ አምጥታ አፌን ያዘችኝ።
<<ኢብቲ ዝምምምምምም በይ!>> በአይኖቿ ተማፀነችኝ። ወደ ራቢ ስመለከት የሌላ ሰው ታሪክ ይመስል እሷም ተመስጣ ነበር የምትስማው።
ዩስራ ቀጣዩን ስትጀምር ትኩረቴን ወደሷ አደርጌ ማዳመጥ ጀመርኩ።
<<ከዛ እንደሚመታት ሲነግረኝ ይቅርታ እንደምትጠይቀው ችግር እንደሌለው ቀለል አድርጌ ነገርኩት። እሱ የልብ ልብ ተሰምቶት ወደ ቤትሰዐት ላይ እንደሚሆን ነገረኝ፤ <እሺ እንዳልክ> አልኩት። የማይደርስ የለምና ያለኝ ሰዐት ላይ ደረስን።
.
አስተማሪው እንደወጣ በሩን ዘግቶ ሁሉንም እንዲቀመጡ ካደረገ ቡኃላ ከተማሪዎች ፊት ወጥቶ <እኔን ይቅርታ መጠየቅ የምትፈልግ ልጅ አለች እናም በናንተ ፊት የምትለኝን ሰምቼ ይቅርታ የሚገባት ከሆነ አደርግላታለው፤ ካልሆነ የሚገባትን እሰጣታለው> አለ። ተማሪው ግራ በመጋባት ዝም ብሎ መከታተል ጀመረ። በዚህ መሃል ባቢ ወደኛ ዞሮ <ከናንተ ጋር ነው?> ግራ እየተጋባ ጠየቀን። ራቢ <ኧረ አይደለም ባቢ...ማን እንደሆነች እኛም አናውቅም> አለችው፤ አዎ እሷም አታውቅም... ያለኝን አልገርኳትም ነበር። በሩን ከፍቶ ልጆች ማስገባት ጀመረ፤ ለካ ለሌላ ክፍል ጓደኞቹም ነግሯቸዋል። ነገሩ ትንሽ ከበድ እንዳለ ገባኝ ለራቢ ልንገራት አልንገራት እያልኩ ሁለት ሃሣብ ውስጥ ገባሁ።
ተማሪው እርስ በእርሱ ይንሸኳሸኳል፤ <እሺ ነይ ወደዚህ ምን እንደምትዪኝ ሁሉም መስማት ይፈልጋል> ራቢ ላይ ሁሉም አፈጠጠ፤ ግራ ገባት። እሷ የምታውቀው ነገር ስላልነበረ እሷን አልመሰላትም። <ዩስራ ምንድነው እኔ ነው እንዴ? እእ> ምንም መናገር አልቻልኩም። ተማሪው ሁሉ ወደኛ ዞሮ መመልከት ጀመረ።
<ምንድነው አልገባኝም?>
<ራቢ ቡኃላ አስረዳሻለው ይሄን እኔ እወጣዋለሁ ብዬ ስነሳ> ያዘችኝ።
<የት ነሽ ንገሪኝ!> አፈጠጠችብኝ። መጀመሪያ መንገር እንደነበረብኝ አሁን ተሰማኝ <መልሺልኝ ዩስራ!> ጮክ አለች። <ራቢ በአላህ ልቀቂኝ መጣሁ አንዴ ..> ባቢ ዞሮ <ምን ሆናቹ ነው?> ይለናል።
<ዝም በል አንተ ደግሞ> ራቢ ነበረች፤ በጣም ተናዳለች ማለት ነው።
<ሃሃሃ ምንነው ፈራሽ እንዴ!> የበረከት ድምጽ ተሰማ ሁሉም ፊቱን ወደሱ መለስ አደረገ። በጣም ብሽቅ አልኩኝ...እጇን ምንጭቅ አድርጌአት ወደ በረከት መሄድ ጀመርኩ። ከፊት ለፊቱ ቆምኩኝ፤ <ኦውውው እሷ ፈርታ ነው አፍራ አንቺን የላከችሽ?> በንቀት አይን እያየኝ። እኔ ወደ ራቢ ስመለከት ተናዳለች፣ግራ ተጋብታለች፣ ከተቀመጠችበት ተነስታ የሚሆነውን ታያለች...>>
.
ዩሲ ትረካዋን ሳትጨርስ የተማሪ ጫጫታ ስንስማ ወደ ክፍል መግቢያ ሰዐት እንደ ደረሰ ተረዳን። ዩስራ <<በቃ አንድ ቀን እጨርስላቹሃለው አሁን ወደ ክፍል እንሂድ>> ብላ ተነሳች።
<<ኧረ አልሰማሽም ምሳ ሰዐት ታሪኩን ሳጨርሺልን መብላት የለም>> ኢክሩ ሣቅ እያለች።
<<እኔም እስማማለሁ። ኢክሩ በቃ አትውጪ እኛ ሶስት ነን..>> ከኢክሩ ጋር ተቃቅፈን ተለያየን። ወደ ክፍላችን ለመሄድ ደረጃው መውረድ ስንጀምር እነ ራቢ ከሆነች ልጅ ጋር ሰላም ሲባባሉ እኔ ወደ ታች ወረድኩ። ደረጃው ላይ ተማሪ እየተተላለፈ በመሆኑ ለመቆም አይመችም ነበር። ደረጃውን ጨርሼ ፊቴን እነ ራቢ በሚመጡበት አቅጣጫ አድርጌ ቆሞኩኝ፤ ከኃላ ሲገፈትሩኝ ዞር ስል በረከትን አየሁት እኔ መሆኔን ሲያይ ደነገጠ።
<<ያምሃል ቀስ አትልም?>>
<<ሳላውቅ ነው>> በንቀት እያየኝ መለሰልኝ።
<<ምን ይመስላል ዝፍዝፍ..>>የቅድሙ የራቢ ሂጃብ እልህ አሲዞኛል። ጓደኞቹ ሲስቁበት <<ስርዐት ያዢ>> ብሎኝ ቆመ ተማሪው መሰብሰብ ጀመረ።
<<ባሊዝስ ምን ልታመጣ? ክብርህን ጠብቅ ክበረ ቢስ!>>
<<አንቺ! ምንድነው ያልሽው>> እጁን ሲሰነዝር ሽል ብዬ እኔ በተራዬ ልሰነዝር ስል ከኃላ ሌላ እጅ ያዘኝ። ዞር ስል ከማሂር ጋር ተገጣጠምን።
<<በሬው ምንድነው ከሴት ጋር ልትደባደብ ነው እንዴ?>> አፈጠጠበት።
<<ማሂ.. እናቴን ተሣፍጣኝ ነው ንቀታም ናት>>
<<አቦ ባክህ ጥፋ ከዚህ ሁለተኛ እንዳትናገራት! ነይ አንቺ ደግሞ>> እጄን ሣይለቀኝ ወደ ክፍል መሄድ ጀመርን። እሱ ከፊት በጣም እየፈጠነ ነበር፤ እጄን ስለያዘኝ እየጎተተኝ ማለት ይቻላል። ክፍል አስገብቶኝ ቦታዬ ጋር ስደርስ ለቀቀኝ። <<ቁጭ በይ!>> ሣልቃወመው ቁጭ አልኩ።
<<ከማንም ጋር እንዳትጣዪ እሱን እኔ አናግረዋለሁ>> ብሎኝ ትቶኝ ወጣ ።ግራ ገብቶኝ ቀና ስል ተማሪው አይን አይኔን ያየኛል... ልወጣ ስነሳ ባቢ ና አቤላ መጡ።
<<ኧረ ልጅት በአደባባይ ካልተደባደብኩ አልሻ?>> ባቢ አውርቶ ሳይጨርስ ራቢና ዩሲ አብረው መጡ።
<<እሺ የኔ ጀግና ለሁለት ደቂቃ ብንለያይ ድብልቅልቁን አውጣሽዋ>> ዩሲ እንደመሣቅ እያለች።
<<ዩስራ አንቺ እኮ ነሽ፤ ቅድም ያለፈ ታሪክ ነግረሽ እልህ ያስያዣት።>> ራቢ።
<<ባካችሁን ዝም በሉ። ይሄ ዝፍዝፍ ቆይ ልኩን አሣየዋለው።>>
<<ልኩንማ ሊያሳይልሽ ሄደ እኮ>> አቤላ ካጎነበሰበት ሣይነቃነቅ።
<<ማን??>> የሁላችንም ጥያቄ ነበር።
<<ኧረ <ማን?> ደስ ይላል።>> ባቢ ፈገግ እንዳለ <<እጅሽን ይዞ ይዚህ ድረስ ያመጣሽ ልጅ ነዋ!!>>
<<ምን ምን? ማን ነው?>> ዩስራ ና ራቢ አፈራርቀው አዩኝ።
<<እንዲህ ሼም ይዟትማ አልነግራችሁም..>> ባቢ ሳቅ እያለ።
<<ኧረ ባቢ እንሂድ እየረሸነው እንዳይሆን>> አቤላ ከክፍሉ ለመውጣት እየሰሰፈሰፈ ተነሣ።
<<አንተ እኮ ነህ እንከተለው ስልህ ..እሺ ጠብቀኝ>> ማሂር ጋ ለመሄድ ተጣደፉ። ገና ከክፍሉ ሳትወጡ
<<ውይይ መጣ በቃ!>> የሚል ድምፅ ሰማን፤ ራቢ። ወደ በሩ ስናይ ማሂር ነበር፤ ገብቶ ቦታው ላይ ተቀመጠ። እነ ባቢ ወደሱ ሲሄዱ ራቢና ዩስራ እርስ በእርስ ተያዩ። እኔ ባላየ አንገቴን ደፋሁ።

www.tgoop.com/Habibacalligraphy



tgoop.com/Habibacalligraphy/1939
Create:
Last Update:

የባከኑ ቀናት
ክፍል አራት
(ሂባ ሁዳ)
.
.
<<ምን በተማሪ ፊት?>> ኢክሩ ደንግጣ ራቢና ዩሲን አፈራርቃ እያየች።
<<አዎ ኢክሩ አደንግጪ። በዛ ላይ የምሣ ሰዐት ደርሶ ስለነበረ ብዙ ተማሪ ተሰብስቦ ነበር። በሬው ደንግጦ ሱሪው ከፍ ሲያደርግ አስተማሪው <አውርድ!> አለውና ለተወሰነ ደቂቃ እንደዛው እንዳስቆመው።
<ሌላ ምን እንዲቀጣ ትፈሊጊያለሽ?> ራቢን ጠየቃት።
<ቅጣት ይበቃዋል፤ ግን ለኔ ሂጃብ ማለት ለእሱ አውራውን ከሚሸፍንበት ሱሪ በላይ ነው። ማንም ሰው በሂጃቤ እንዲጫወትበት አልፈቅድለትም። የከፋ ችግር ይገጥመዋል፤ ስለዚህ አርፎ ይቀመጥ። ተገቢውን ቅጣት በተማሪ ፊት መሰጠቱ ለሌሎች ትምህርት ነው። እኔ ማንም ይሁን ማንም ሂጃቤን አይደለም እጄን እንኳን እንዲነካኝ አልፈቅድለትም። አመሰግናለሁ> አለች። እኛ ከዛ ቦታ ዞር ብንልም ለትምህርት ቤቱ የሣምንት መነጋገሪያ ሆነ። ክፍል ሲገባም እነ ባቢ የሌለ ሙድ ይይዙበት ነበር። እኛም ከነ ባቢ ጋር በደንብ ተግባባን። ታዲያ ይሄ በረከትን(በሬው) እልህ ውስጥ ከተተው፤ ዝም ብሎ ነገር ይፈልጋት ጀመር። መጣላት እንደሚፈልግ ያስታውቅበት ነበር። የሆነ ቀን እኔን ጠራኝ እና በተማሪው ፊት ይቅርታ እንድትጠይቀው ካልሆነ እንደሚመታት ነገረኝ።>>
<<ጭራሽ እሷ ይቅርታ ልትጠይቀው ማለት ነው?? ኧረ ሞራል ..>> በስሜት አብሬ ለፈለፍኩ። ኢክሩ ራቢን ያቀፈችበት እጇን ወደኔ አምጥታ አፌን ያዘችኝ።
<<ኢብቲ ዝምምምምምም በይ!>> በአይኖቿ ተማፀነችኝ። ወደ ራቢ ስመለከት የሌላ ሰው ታሪክ ይመስል እሷም ተመስጣ ነበር የምትስማው።
ዩስራ ቀጣዩን ስትጀምር ትኩረቴን ወደሷ አደርጌ ማዳመጥ ጀመርኩ።
<<ከዛ እንደሚመታት ሲነግረኝ ይቅርታ እንደምትጠይቀው ችግር እንደሌለው ቀለል አድርጌ ነገርኩት። እሱ የልብ ልብ ተሰምቶት ወደ ቤትሰዐት ላይ እንደሚሆን ነገረኝ፤ <እሺ እንዳልክ> አልኩት። የማይደርስ የለምና ያለኝ ሰዐት ላይ ደረስን።
.
አስተማሪው እንደወጣ በሩን ዘግቶ ሁሉንም እንዲቀመጡ ካደረገ ቡኃላ ከተማሪዎች ፊት ወጥቶ <እኔን ይቅርታ መጠየቅ የምትፈልግ ልጅ አለች እናም በናንተ ፊት የምትለኝን ሰምቼ ይቅርታ የሚገባት ከሆነ አደርግላታለው፤ ካልሆነ የሚገባትን እሰጣታለው> አለ። ተማሪው ግራ በመጋባት ዝም ብሎ መከታተል ጀመረ። በዚህ መሃል ባቢ ወደኛ ዞሮ <ከናንተ ጋር ነው?> ግራ እየተጋባ ጠየቀን። ራቢ <ኧረ አይደለም ባቢ...ማን እንደሆነች እኛም አናውቅም> አለችው፤ አዎ እሷም አታውቅም... ያለኝን አልገርኳትም ነበር። በሩን ከፍቶ ልጆች ማስገባት ጀመረ፤ ለካ ለሌላ ክፍል ጓደኞቹም ነግሯቸዋል። ነገሩ ትንሽ ከበድ እንዳለ ገባኝ ለራቢ ልንገራት አልንገራት እያልኩ ሁለት ሃሣብ ውስጥ ገባሁ።
ተማሪው እርስ በእርሱ ይንሸኳሸኳል፤ <እሺ ነይ ወደዚህ ምን እንደምትዪኝ ሁሉም መስማት ይፈልጋል> ራቢ ላይ ሁሉም አፈጠጠ፤ ግራ ገባት። እሷ የምታውቀው ነገር ስላልነበረ እሷን አልመሰላትም። <ዩስራ ምንድነው እኔ ነው እንዴ? እእ> ምንም መናገር አልቻልኩም። ተማሪው ሁሉ ወደኛ ዞሮ መመልከት ጀመረ።
<ምንድነው አልገባኝም?>
<ራቢ ቡኃላ አስረዳሻለው ይሄን እኔ እወጣዋለሁ ብዬ ስነሳ> ያዘችኝ።
<የት ነሽ ንገሪኝ!> አፈጠጠችብኝ። መጀመሪያ መንገር እንደነበረብኝ አሁን ተሰማኝ <መልሺልኝ ዩስራ!> ጮክ አለች። <ራቢ በአላህ ልቀቂኝ መጣሁ አንዴ ..> ባቢ ዞሮ <ምን ሆናቹ ነው?> ይለናል።
<ዝም በል አንተ ደግሞ> ራቢ ነበረች፤ በጣም ተናዳለች ማለት ነው።
<ሃሃሃ ምንነው ፈራሽ እንዴ!> የበረከት ድምጽ ተሰማ ሁሉም ፊቱን ወደሱ መለስ አደረገ። በጣም ብሽቅ አልኩኝ...እጇን ምንጭቅ አድርጌአት ወደ በረከት መሄድ ጀመርኩ። ከፊት ለፊቱ ቆምኩኝ፤ <ኦውውው እሷ ፈርታ ነው አፍራ አንቺን የላከችሽ?> በንቀት አይን እያየኝ። እኔ ወደ ራቢ ስመለከት ተናዳለች፣ግራ ተጋብታለች፣ ከተቀመጠችበት ተነስታ የሚሆነውን ታያለች...>>
.
ዩሲ ትረካዋን ሳትጨርስ የተማሪ ጫጫታ ስንስማ ወደ ክፍል መግቢያ ሰዐት እንደ ደረሰ ተረዳን። ዩስራ <<በቃ አንድ ቀን እጨርስላቹሃለው አሁን ወደ ክፍል እንሂድ>> ብላ ተነሳች።
<<ኧረ አልሰማሽም ምሳ ሰዐት ታሪኩን ሳጨርሺልን መብላት የለም>> ኢክሩ ሣቅ እያለች።
<<እኔም እስማማለሁ። ኢክሩ በቃ አትውጪ እኛ ሶስት ነን..>> ከኢክሩ ጋር ተቃቅፈን ተለያየን። ወደ ክፍላችን ለመሄድ ደረጃው መውረድ ስንጀምር እነ ራቢ ከሆነች ልጅ ጋር ሰላም ሲባባሉ እኔ ወደ ታች ወረድኩ። ደረጃው ላይ ተማሪ እየተተላለፈ በመሆኑ ለመቆም አይመችም ነበር። ደረጃውን ጨርሼ ፊቴን እነ ራቢ በሚመጡበት አቅጣጫ አድርጌ ቆሞኩኝ፤ ከኃላ ሲገፈትሩኝ ዞር ስል በረከትን አየሁት እኔ መሆኔን ሲያይ ደነገጠ።
<<ያምሃል ቀስ አትልም?>>
<<ሳላውቅ ነው>> በንቀት እያየኝ መለሰልኝ።
<<ምን ይመስላል ዝፍዝፍ..>>የቅድሙ የራቢ ሂጃብ እልህ አሲዞኛል። ጓደኞቹ ሲስቁበት <<ስርዐት ያዢ>> ብሎኝ ቆመ ተማሪው መሰብሰብ ጀመረ።
<<ባሊዝስ ምን ልታመጣ? ክብርህን ጠብቅ ክበረ ቢስ!>>
<<አንቺ! ምንድነው ያልሽው>> እጁን ሲሰነዝር ሽል ብዬ እኔ በተራዬ ልሰነዝር ስል ከኃላ ሌላ እጅ ያዘኝ። ዞር ስል ከማሂር ጋር ተገጣጠምን።
<<በሬው ምንድነው ከሴት ጋር ልትደባደብ ነው እንዴ?>> አፈጠጠበት።
<<ማሂ.. እናቴን ተሣፍጣኝ ነው ንቀታም ናት>>
<<አቦ ባክህ ጥፋ ከዚህ ሁለተኛ እንዳትናገራት! ነይ አንቺ ደግሞ>> እጄን ሣይለቀኝ ወደ ክፍል መሄድ ጀመርን። እሱ ከፊት በጣም እየፈጠነ ነበር፤ እጄን ስለያዘኝ እየጎተተኝ ማለት ይቻላል። ክፍል አስገብቶኝ ቦታዬ ጋር ስደርስ ለቀቀኝ። <<ቁጭ በይ!>> ሣልቃወመው ቁጭ አልኩ።
<<ከማንም ጋር እንዳትጣዪ እሱን እኔ አናግረዋለሁ>> ብሎኝ ትቶኝ ወጣ ።ግራ ገብቶኝ ቀና ስል ተማሪው አይን አይኔን ያየኛል... ልወጣ ስነሳ ባቢ ና አቤላ መጡ።
<<ኧረ ልጅት በአደባባይ ካልተደባደብኩ አልሻ?>> ባቢ አውርቶ ሳይጨርስ ራቢና ዩሲ አብረው መጡ።
<<እሺ የኔ ጀግና ለሁለት ደቂቃ ብንለያይ ድብልቅልቁን አውጣሽዋ>> ዩሲ እንደመሣቅ እያለች።
<<ዩስራ አንቺ እኮ ነሽ፤ ቅድም ያለፈ ታሪክ ነግረሽ እልህ ያስያዣት።>> ራቢ።
<<ባካችሁን ዝም በሉ። ይሄ ዝፍዝፍ ቆይ ልኩን አሣየዋለው።>>
<<ልኩንማ ሊያሳይልሽ ሄደ እኮ>> አቤላ ካጎነበሰበት ሣይነቃነቅ።
<<ማን??>> የሁላችንም ጥያቄ ነበር።
<<ኧረ <ማን?> ደስ ይላል።>> ባቢ ፈገግ እንዳለ <<እጅሽን ይዞ ይዚህ ድረስ ያመጣሽ ልጅ ነዋ!!>>
<<ምን ምን? ማን ነው?>> ዩስራ ና ራቢ አፈራርቀው አዩኝ።
<<እንዲህ ሼም ይዟትማ አልነግራችሁም..>> ባቢ ሳቅ እያለ።
<<ኧረ ባቢ እንሂድ እየረሸነው እንዳይሆን>> አቤላ ከክፍሉ ለመውጣት እየሰሰፈሰፈ ተነሣ።
<<አንተ እኮ ነህ እንከተለው ስልህ ..እሺ ጠብቀኝ>> ማሂር ጋ ለመሄድ ተጣደፉ። ገና ከክፍሉ ሳትወጡ
<<ውይይ መጣ በቃ!>> የሚል ድምፅ ሰማን፤ ራቢ። ወደ በሩ ስናይ ማሂር ነበር፤ ገብቶ ቦታው ላይ ተቀመጠ። እነ ባቢ ወደሱ ሲሄዱ ራቢና ዩስራ እርስ በእርስ ተያዩ። እኔ ባላየ አንገቴን ደፋሁ።

www.tgoop.com/Habibacalligraphy

BY Habiba Calligraphy




Share with your friend now:
tgoop.com/Habibacalligraphy/1939

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

As of Thursday, the SUCK Channel had 34,146 subscribers, with only one message dated August 28, 2020. It was an announcement stating that police had removed all posts on the channel because its content “contravenes the laws of Hong Kong.” The Channel name and bio must be no more than 255 characters long Developing social channels based on exchanging a single message isn’t exactly new, of course. Back in 2014, the “Yo” app was launched with the sole purpose of enabling users to send each other the greeting “Yo.” How to Create a Private or Public Channel on Telegram? To delete a channel with over 1,000 subscribers, you need to contact user support
from us


Telegram Habiba Calligraphy
FROM American