HABIBACALLIGRAPHY Telegram 1940
የባከኑ ቀናት
ክፍል አምስት
(ሂባ ሁዳ)
.
.
በትምህርት ሰዐት ወሬ ብሎ ነገር የለም፤ ትኩረታችን የሚሆነው ወደ አስተማሪው ነው። የትምህርት ሰዐት አልቆ የምሳ ሰዐት ላይ ደረስን። ተማሪው መውጣት ሲጀምር ራቢ አላንቀሣቅስ አለችኝ።
<<እሺ ምን ልንገርሽ?>>
<<የሆነውን ነዋ... አይደል>> ወደ ዩስራ እየተመለከትች ዩስራም አዎንታዊ ምላሽ ሰጠቻት። መልስ ሳልሰጣት ባቢ ወደኛ መጣ <<ዛሬ አትሰግዱም እንዴ?>>
<<ኧረ ባቢ እንሰግዳለን። ምነው አብረኸን ልትሰግድ ነው? እእ>> በዛው ደብተሬን እያስገባባሁ።
<<ሃሃ ምን ጣጣ አለው ..ባይሆን ውጪ ሰው እየጠበቅሽ ነው ጥራት ተብዬ ነው።>>
<<ማንን??>> ሶስታችንም እኩል ጠየቅነው።
<<አቤት ለወሬ.. ሂጂ አንቺ>>
<<እኔ?>> ግራ እየተጋባሁ።
<<አዎ>> እኔን እየተመለከተ። እነ ዩስራ ሳያቸው እንድሄድ ነገሩኝ... ባቢን ከነሱ ጋር ትቼ ወደ ውጪ ወጣሁ። ማንንም ሣጣ ሙድ እየያዙ ባልሆነ እያልኩ ልገባ ስል <<ኢብቲ>> የሚል ድምፅ ሰማሁ። ወደሰማሁበት ስዞር ማሂር ነው።
<<እንዴ ማሂር>> ፈገግ አልኩኝ ቆሞ ሲያየኝ የተጨነቀ ይመስላል። ምን ሆኖ ይሁን ብዬ ወደ ቆመበት ሄድኩኝ።
<<አንተ ነህ የፈለከኝ?>>
<<አዎ ኢብቲ ምን መሰለሽ.. እኔ ግን በመጀመሪያ ይቅርታ..>>
<<ለምን ይቅርታ?>> ግራ እየገባኝ ጠየኩት።
<<ቅድም>> አይን አይኔን ያየኛል <<ቅድም ምን?>>
<<ቅድም እጅሽን የያዝኩት ሣላስበው ነው። እና ደግሞ ኢብቲ ያልኩሽም ጓደኞችሽ ሲጠሩሽ ስለሰማሁ ነው ይቅርታ...>>
<<ለቅድሙ ችግር የለውም፤ እኔም ሳላስበው ስለነበረ ነው። እንደውም አናደድኩህ መሰለኝ፤ በኔ ችግር አንተንም ስላስገባሁህ ይቅርታ። ግን ኢብቲ ምናምን ያልከው አልገባኝም..>>
<<ኢብቲ ስልሽ ደስ እንደማይልሽ አላውቅም ነበር። ቅድም ነው ባቢ <ለምን እጇን ያዝካት ተናዳብሃለች። ደግሞ ኢብቲ አትበላት ይደብራታል> ብሎኝ ነው። ከዛ <እና> ስለው አቤላ ደግሞ <ይቅርታ እንጠይቃት> ብሎኝ ነው።>>
<<ሃሃሃ ኧረ እነዚህ የተመቱ ሙድ ያዙ ማለት ነው>> መሣቄን ሣላቆም።
<<ማለት? እንዴት?>> ድንብርብር አለ።
<<እንዴ እኔ ኢብቲ ስላልከኝ ለምን እጣላሃለው? ራሱም እንደዛ አይደል የሚጠራኝ>>
<<እውነት! የምርሽን ነው?>>
<<አዎ ማሂ እውነቴን ነው።>>
<<ማሂ ስትዪኝ ደግሞ ደስ ይላል አጠራርሽ>>
<<ከአጠራሬ አመስለኝም <ሎጋው> እንዳልልህ ነው? እእ አትዋሽ..>>
<<ሃሃሃ አዎ ነቃሽብኝ። በናትሽ እንደነሱ አትጥሪኝ ማሂ በይኝ>>
<<ሰዎችን በማያስደስታቸው ስም አልጣራም! ችግር የለውም እሺ ማሂ ነው የምልህ>>
<<አመሰግናለሁ>> እጁን ዘረጋ።ሣየው
<<ውይ ይቅርታ>> እጆቹን ሰበሰበ.. ሃፍረት የተሰማው ይመስላል።
<<ቆይ እነዚህ ልጀችማ እንሰራላቸዋለን...>>
<<እንዳይሰሩልን ፍራ! አሁንም ባቢ ምን እንደሚሰራ አይታወቅም>> እንየው ብለን ወደ ክፍል ስንመለከት አቤላን አየነው። <<ያውልህ አቤላ>> በእጄ አቤል ወዳለበት እየጠቆምኩ።
<<ኧረ ሁሉም አሉ እንጂ ነይ እዚህ ጋር>> ብሎኝ በእሱ በኩል ሁኜ ወደ በሩ ስመለከት አቤላ፣ባቢ፣ራቢ፣ዩሲ ና ኢክራም ተሰብስበው እያዩን ነው። እንዳየናቸው ሲያቁ መሣቅ ጀመሩ። እነ ባቢ ወደኛ መጡ << አንተ ምን አባህ እየሰራህ ነው?>> ማሂ የባቢን ጆሮ ለመያዝ ይታገላል።
<<ኧረ ላሽ ራስህ እስካሁን ምን እያወራህ ነበር>>
<<በቃ ልሂድ>> ብያቸው ወደነ ራቢ አመራሁ። መሄድ ስጀምር ባቢ ምን እንደለኝ አልስማሁትም ግን አቤላ ና ማሂ ሣቃቸው ይሰማኛል።
*
እነ ራቢ ጋር ከመድረሴ ኢክሩ እየሣቀች <<ማሂር ነዋ ስሙ? በአላህ ሲገርም>> አለች።
<<ታዲያ ለዛ አይደል በአንዴ እንዲ የተግባቡልሽ>> ዩስሪ ነበረች ።
<<ራቢ ምነው?>> ራቢ ከወትሮዋ ዝም ማለቷ ገርሞኛል።
<<ምንም የኔ ውድ ጉድሽን ሁሉ ባቢ ነግሮናል።>>
<<እስካሁን እሱ እያወራቹ ነበር? ልጁ ግን እብድ ነገር ነው። አሁንም የሱ ስራ ነው እኮ ሃሃ>> ማሂ ላይ የሰራው ትዝ ብሎኝ ድጋሚ እየሳቅኩ።
<<አዎ ኢብቲ.. ለዛ እኮ ነበር የሣቅንባቹ በማታውቁት ነገር ሃሃሃ። አይ ባቢ ገና መች ሆነና ስራው ብዙ ነው...>> ራቢ።
<<ኧረ በልተን ወደ ሰላት>> ዩስራ ምሣቃችንን አወጣጣች።
<<ኧረ የቅድሙን ሣትነግሪን የምን መብላት ነው?>> ኢክሩ ምሣቃውን እየተቀበለቻት።
<<ሆሆ አንቺም እንደ ኢብቲ ስታገኝው ካልመታሁህ ብትዪሣ?>>
<<ሃሃ ራቢ ደግሞ ነገር አትረሺማ?>>
<<እንዴት ይሄን የመሰለ ነገር ትረሣለች? በትረካ መልኩ ነው ያቀረበችልኝ>> ኢክሩ
ራቢን እየተመለከተች።
<<ነገረችኝ ነው የምትይኝ እእ?>> ከበረከት ጋር የተፈጠረው ወሬ ሆኖ ኢክሩ ጋር መድረሱ እየገረመኝ።
<<አዎ ኢብቲ.. ለዛ አይደል እንዲ ሣቅ በሣቅ የሆነችው ሃሃሃሃ>>
<<እብዶች ናችሁ እኮ...>>
<<እሺ አታረሣሱ በቃ እየበላን ይነገረን ዩስሪ ጀምሪ።>> ኢክሩ ለትረካው ቸኩላለች።
<<ኧረ እየሰሙ መብላት ቀላል ነው እያውሩ መብላቱ ነው ከባድ>> ዩስራ የምሣቃችንን ደረደረች።
<<ሃሃሃሃ አይዞሽ ሁላችንም እናጎርስሻለን አንቺ ብቻ ተሪኪልን>> ራቢን እጇን አስታጥቤያት ስጨርስ እኔን ታስጣጥበኛለች።
ዩስሪ ሃይላንዱን እየተቀበለችኝ <<እሺ ግን በአንድ ነገር እንስማማ>>
<<በምን?>>
<<ስጨርስላቹ ዛሬ ኢክሩ ና ኢብቲ ሎሊፖፕ ትገዛላችሁ>>
<<እእ ኧረ ይሄማ ምርጥ ሃሣብ ነው ተስማምተናል።>>
<<ራቢ እኛ እኮ ነን የተባልነው አንቺ ብር አታወጪ ተስማምተናል ትያለሻ አናታም>>
<<እኮ አየሺልኛ ኢብቲ>> ኢክሩ ቀበል አድርጋ።
<<በቃ ጣጣ የለውም ተያቸው እንገዛለን። አሁን ሰዐት አትግደይ ጀምሪ>>
<<ቆይ ከምግቡ ጋር ቢስሚላህ ብዬ ሃሃ ሃሃ እሺ ምን ላይ ነበርን...
*
<እሷ ፈርታ ነው አፍራ አንቺን የላከችሽ?> ወደ ራቢ ስመለከት ተናዳለች፣ ግራ ተጋብታለች፤ ከተቀመጠችበት ተነስታ የሚሆነውን ታያለች። <እሺ ይቅርታ እንድትጠይቅህ ለምን እንደፈለክ ለተማሪው እኔ ልንገርልህ... በዚህ እንኳን ላግዝህ እንጂ!> ፊቱ ላይ የደስታና የኩራት ስሜቶች ይነበባሉ። ነገሩን ባልጠበቀው መልኩ ለመፍታት አሪፍ መንገድ እየተጠቀምኩ ነው። እሱ ያለውን አንድ በአንድ ደገምኩለት ማለትም መጀመሪያ ላይ ይቅርታ ልትጠይቀኝ ትፈልጋለች ያለውን ከዛም ንግግሬን ቀጠልኩ <አሁን በደንብ አዳምጡኝ የእስካሁኑ ንግግርም ሆነ ሃሣብ ከፊት ለፊታችሁ የተቀመጠው ራስ ወዳድ አሊያም ከኔ በላይ ሰው የለም እያለ የሚያንቧርቀው ክብረ-ቢስ የሆነው በረከት እንጂ የኔ ወይ የጓደኛዬ ፍላጎትም አይደለም ስለዚህ ለኔ እንዳለኝ ይሆናል። ማለትም ጓደኛዬ (ራቢ) ይቅርታ እንድትጠይቀው ካልሆነ ግን ነገሩን ወደ ጥል እንደሚቀይረው አስጠንቅቆኛል። እኔ እንዲህ አይነት ርካሽ ጥያቄ ከኔ አልፎ ራቢ ጋር እንዲደርስ አላደረኩም። እንደሌሎች ተማሪዎች ነገሩ አሁን መስማቷ ነው። ስለዚህ ነገሩን ከኔ ጋር እንፈታዋለን ምን ይመስልሃል?>
.
.
ይቀጥላል...

www.tgoop.com/Habibacalligraphy



tgoop.com/Habibacalligraphy/1940
Create:
Last Update:

የባከኑ ቀናት
ክፍል አምስት
(ሂባ ሁዳ)
.
.
በትምህርት ሰዐት ወሬ ብሎ ነገር የለም፤ ትኩረታችን የሚሆነው ወደ አስተማሪው ነው። የትምህርት ሰዐት አልቆ የምሳ ሰዐት ላይ ደረስን። ተማሪው መውጣት ሲጀምር ራቢ አላንቀሣቅስ አለችኝ።
<<እሺ ምን ልንገርሽ?>>
<<የሆነውን ነዋ... አይደል>> ወደ ዩስራ እየተመለከትች ዩስራም አዎንታዊ ምላሽ ሰጠቻት። መልስ ሳልሰጣት ባቢ ወደኛ መጣ <<ዛሬ አትሰግዱም እንዴ?>>
<<ኧረ ባቢ እንሰግዳለን። ምነው አብረኸን ልትሰግድ ነው? እእ>> በዛው ደብተሬን እያስገባባሁ።
<<ሃሃ ምን ጣጣ አለው ..ባይሆን ውጪ ሰው እየጠበቅሽ ነው ጥራት ተብዬ ነው።>>
<<ማንን??>> ሶስታችንም እኩል ጠየቅነው።
<<አቤት ለወሬ.. ሂጂ አንቺ>>
<<እኔ?>> ግራ እየተጋባሁ።
<<አዎ>> እኔን እየተመለከተ። እነ ዩስራ ሳያቸው እንድሄድ ነገሩኝ... ባቢን ከነሱ ጋር ትቼ ወደ ውጪ ወጣሁ። ማንንም ሣጣ ሙድ እየያዙ ባልሆነ እያልኩ ልገባ ስል <<ኢብቲ>> የሚል ድምፅ ሰማሁ። ወደሰማሁበት ስዞር ማሂር ነው።
<<እንዴ ማሂር>> ፈገግ አልኩኝ ቆሞ ሲያየኝ የተጨነቀ ይመስላል። ምን ሆኖ ይሁን ብዬ ወደ ቆመበት ሄድኩኝ።
<<አንተ ነህ የፈለከኝ?>>
<<አዎ ኢብቲ ምን መሰለሽ.. እኔ ግን በመጀመሪያ ይቅርታ..>>
<<ለምን ይቅርታ?>> ግራ እየገባኝ ጠየኩት።
<<ቅድም>> አይን አይኔን ያየኛል <<ቅድም ምን?>>
<<ቅድም እጅሽን የያዝኩት ሣላስበው ነው። እና ደግሞ ኢብቲ ያልኩሽም ጓደኞችሽ ሲጠሩሽ ስለሰማሁ ነው ይቅርታ...>>
<<ለቅድሙ ችግር የለውም፤ እኔም ሳላስበው ስለነበረ ነው። እንደውም አናደድኩህ መሰለኝ፤ በኔ ችግር አንተንም ስላስገባሁህ ይቅርታ። ግን ኢብቲ ምናምን ያልከው አልገባኝም..>>
<<ኢብቲ ስልሽ ደስ እንደማይልሽ አላውቅም ነበር። ቅድም ነው ባቢ <ለምን እጇን ያዝካት ተናዳብሃለች። ደግሞ ኢብቲ አትበላት ይደብራታል> ብሎኝ ነው። ከዛ <እና> ስለው አቤላ ደግሞ <ይቅርታ እንጠይቃት> ብሎኝ ነው።>>
<<ሃሃሃ ኧረ እነዚህ የተመቱ ሙድ ያዙ ማለት ነው>> መሣቄን ሣላቆም።
<<ማለት? እንዴት?>> ድንብርብር አለ።
<<እንዴ እኔ ኢብቲ ስላልከኝ ለምን እጣላሃለው? ራሱም እንደዛ አይደል የሚጠራኝ>>
<<እውነት! የምርሽን ነው?>>
<<አዎ ማሂ እውነቴን ነው።>>
<<ማሂ ስትዪኝ ደግሞ ደስ ይላል አጠራርሽ>>
<<ከአጠራሬ አመስለኝም <ሎጋው> እንዳልልህ ነው? እእ አትዋሽ..>>
<<ሃሃሃ አዎ ነቃሽብኝ። በናትሽ እንደነሱ አትጥሪኝ ማሂ በይኝ>>
<<ሰዎችን በማያስደስታቸው ስም አልጣራም! ችግር የለውም እሺ ማሂ ነው የምልህ>>
<<አመሰግናለሁ>> እጁን ዘረጋ።ሣየው
<<ውይ ይቅርታ>> እጆቹን ሰበሰበ.. ሃፍረት የተሰማው ይመስላል።
<<ቆይ እነዚህ ልጀችማ እንሰራላቸዋለን...>>
<<እንዳይሰሩልን ፍራ! አሁንም ባቢ ምን እንደሚሰራ አይታወቅም>> እንየው ብለን ወደ ክፍል ስንመለከት አቤላን አየነው። <<ያውልህ አቤላ>> በእጄ አቤል ወዳለበት እየጠቆምኩ።
<<ኧረ ሁሉም አሉ እንጂ ነይ እዚህ ጋር>> ብሎኝ በእሱ በኩል ሁኜ ወደ በሩ ስመለከት አቤላ፣ባቢ፣ራቢ፣ዩሲ ና ኢክራም ተሰብስበው እያዩን ነው። እንዳየናቸው ሲያቁ መሣቅ ጀመሩ። እነ ባቢ ወደኛ መጡ << አንተ ምን አባህ እየሰራህ ነው?>> ማሂ የባቢን ጆሮ ለመያዝ ይታገላል።
<<ኧረ ላሽ ራስህ እስካሁን ምን እያወራህ ነበር>>
<<በቃ ልሂድ>> ብያቸው ወደነ ራቢ አመራሁ። መሄድ ስጀምር ባቢ ምን እንደለኝ አልስማሁትም ግን አቤላ ና ማሂ ሣቃቸው ይሰማኛል።
*
እነ ራቢ ጋር ከመድረሴ ኢክሩ እየሣቀች <<ማሂር ነዋ ስሙ? በአላህ ሲገርም>> አለች።
<<ታዲያ ለዛ አይደል በአንዴ እንዲ የተግባቡልሽ>> ዩስሪ ነበረች ።
<<ራቢ ምነው?>> ራቢ ከወትሮዋ ዝም ማለቷ ገርሞኛል።
<<ምንም የኔ ውድ ጉድሽን ሁሉ ባቢ ነግሮናል።>>
<<እስካሁን እሱ እያወራቹ ነበር? ልጁ ግን እብድ ነገር ነው። አሁንም የሱ ስራ ነው እኮ ሃሃ>> ማሂ ላይ የሰራው ትዝ ብሎኝ ድጋሚ እየሳቅኩ።
<<አዎ ኢብቲ.. ለዛ እኮ ነበር የሣቅንባቹ በማታውቁት ነገር ሃሃሃ። አይ ባቢ ገና መች ሆነና ስራው ብዙ ነው...>> ራቢ።
<<ኧረ በልተን ወደ ሰላት>> ዩስራ ምሣቃችንን አወጣጣች።
<<ኧረ የቅድሙን ሣትነግሪን የምን መብላት ነው?>> ኢክሩ ምሣቃውን እየተቀበለቻት።
<<ሆሆ አንቺም እንደ ኢብቲ ስታገኝው ካልመታሁህ ብትዪሣ?>>
<<ሃሃ ራቢ ደግሞ ነገር አትረሺማ?>>
<<እንዴት ይሄን የመሰለ ነገር ትረሣለች? በትረካ መልኩ ነው ያቀረበችልኝ>> ኢክሩ
ራቢን እየተመለከተች።
<<ነገረችኝ ነው የምትይኝ እእ?>> ከበረከት ጋር የተፈጠረው ወሬ ሆኖ ኢክሩ ጋር መድረሱ እየገረመኝ።
<<አዎ ኢብቲ.. ለዛ አይደል እንዲ ሣቅ በሣቅ የሆነችው ሃሃሃሃ>>
<<እብዶች ናችሁ እኮ...>>
<<እሺ አታረሣሱ በቃ እየበላን ይነገረን ዩስሪ ጀምሪ።>> ኢክሩ ለትረካው ቸኩላለች።
<<ኧረ እየሰሙ መብላት ቀላል ነው እያውሩ መብላቱ ነው ከባድ>> ዩስራ የምሣቃችንን ደረደረች።
<<ሃሃሃሃ አይዞሽ ሁላችንም እናጎርስሻለን አንቺ ብቻ ተሪኪልን>> ራቢን እጇን አስታጥቤያት ስጨርስ እኔን ታስጣጥበኛለች።
ዩስሪ ሃይላንዱን እየተቀበለችኝ <<እሺ ግን በአንድ ነገር እንስማማ>>
<<በምን?>>
<<ስጨርስላቹ ዛሬ ኢክሩ ና ኢብቲ ሎሊፖፕ ትገዛላችሁ>>
<<እእ ኧረ ይሄማ ምርጥ ሃሣብ ነው ተስማምተናል።>>
<<ራቢ እኛ እኮ ነን የተባልነው አንቺ ብር አታወጪ ተስማምተናል ትያለሻ አናታም>>
<<እኮ አየሺልኛ ኢብቲ>> ኢክሩ ቀበል አድርጋ።
<<በቃ ጣጣ የለውም ተያቸው እንገዛለን። አሁን ሰዐት አትግደይ ጀምሪ>>
<<ቆይ ከምግቡ ጋር ቢስሚላህ ብዬ ሃሃ ሃሃ እሺ ምን ላይ ነበርን...
*
<እሷ ፈርታ ነው አፍራ አንቺን የላከችሽ?> ወደ ራቢ ስመለከት ተናዳለች፣ ግራ ተጋብታለች፤ ከተቀመጠችበት ተነስታ የሚሆነውን ታያለች። <እሺ ይቅርታ እንድትጠይቅህ ለምን እንደፈለክ ለተማሪው እኔ ልንገርልህ... በዚህ እንኳን ላግዝህ እንጂ!> ፊቱ ላይ የደስታና የኩራት ስሜቶች ይነበባሉ። ነገሩን ባልጠበቀው መልኩ ለመፍታት አሪፍ መንገድ እየተጠቀምኩ ነው። እሱ ያለውን አንድ በአንድ ደገምኩለት ማለትም መጀመሪያ ላይ ይቅርታ ልትጠይቀኝ ትፈልጋለች ያለውን ከዛም ንግግሬን ቀጠልኩ <አሁን በደንብ አዳምጡኝ የእስካሁኑ ንግግርም ሆነ ሃሣብ ከፊት ለፊታችሁ የተቀመጠው ራስ ወዳድ አሊያም ከኔ በላይ ሰው የለም እያለ የሚያንቧርቀው ክብረ-ቢስ የሆነው በረከት እንጂ የኔ ወይ የጓደኛዬ ፍላጎትም አይደለም ስለዚህ ለኔ እንዳለኝ ይሆናል። ማለትም ጓደኛዬ (ራቢ) ይቅርታ እንድትጠይቀው ካልሆነ ግን ነገሩን ወደ ጥል እንደሚቀይረው አስጠንቅቆኛል። እኔ እንዲህ አይነት ርካሽ ጥያቄ ከኔ አልፎ ራቢ ጋር እንዲደርስ አላደረኩም። እንደሌሎች ተማሪዎች ነገሩ አሁን መስማቷ ነው። ስለዚህ ነገሩን ከኔ ጋር እንፈታዋለን ምን ይመስልሃል?>
.
.
ይቀጥላል...

www.tgoop.com/Habibacalligraphy

BY Habiba Calligraphy




Share with your friend now:
tgoop.com/Habibacalligraphy/1940

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

Ng was convicted in April for conspiracy to incite a riot, public nuisance, arson, criminal damage, manufacturing of explosives, administering poison and wounding with intent to do grievous bodily harm between October 2019 and June 2020. The court said the defendant had also incited people to commit public nuisance, with messages calling on them to take part in rallies and demonstrations including at Hong Kong International Airport, to block roads and to paralyse the public transportation system. Various forms of protest promoted on the messaging platform included general strikes, lunchtime protests and silent sit-ins. Telegram Android app: Open the chats list, click the menu icon and select “New Channel.” Commenting about the court's concerns about the spread of false information related to the elections, Minister Fachin noted Brazil is "facing circumstances that could put Brazil's democracy at risk." During the meeting, the information technology secretary at the TSE, Julio Valente, put forward a list of requests the court believes will disinformation. How to build a private or public channel on Telegram?
from us


Telegram Habiba Calligraphy
FROM American