HABIBACALLIGRAPHY Telegram 1942
የባከኑ ቀናት
ክፍል ስድስት
(ሂባ ሁዳ)
.
<< <እንዲው እንዳማረብህ ይቅርታ ልጠይቅህ> ፈገግ አለልኝ፤ በዚህ ቅፅበት ጥሬ እህል እንደሆነ ተሰማኝ። ወደ ተማሪዎች ዞር አልኩ የሚሆነውን ለማየት የቸኮሉ ይመስላሉ። ራቢ እንደተናደደችብኝ ታስታውቃለች፤ ባቢ አጠገቧ አለ... ብዙ ጥያቄ እንዳለው አይኖቹ ይናገራሉ። ፊቴን ወደ በረከት መለስ አደረኩ ምን አልባት ይህ ቅጽበት ለሱ ድል ከማድረግ በላይ በሃሴት የተሞላ ነበር። ከታች ወደ ላይ ተመለከትኩት ትልቅ ድብ የማይ መሰለኝ... ግዝፈቱ አላስፈራኝም። ወደ ኃላ ሄድኩ፤ ከበረከት ጀርባ ቆምኩኝ። ከየት ባመጣሁት ሃይል እና ግፊት እንደሆነ ባላውቅም በቀኝ እጄ አንገቱን እንቅ አድርጌ እንዴት መሬት ላይ እንደተዘረረ አሁንም ድረስ ይገርመኛል፤ ክፍሉ በአንዴ ወደ ሁከት ተቀየረ፤ ክብ ሰርተው መሃል አስገቡን። ከወደቀበት ተነስቶ አንድ ቦክስ ሰነዘረብኝ አልሣተኝም ነበር እኔም በርግጫ አልኩት። ታውቃላቹ ያኔ አምስተኛ ክፍል እያለን ከወንዶች ጋር እንደባደብ የነበረው ጠቅሞኛል... ግን ቦክሱ አቅም አሣጥቶኝ ነበር እናም ከኃላ አንድ ልጅ ሲገፋኝ ወደኩኝ። በረከት አጋጣሚውን ለመጠቀም በጉልበቱ ተንበረከከ በቦክስ ሊደግመኝ ሲል ከኃላ ተገፋና ወደቀ፤ ሲዞር ራቢ ናት። እኔን ትቶ ሲነሣ አብሬው ተነሣሁ፤ ወደ ራቢ ተጠግቶ እጁን ሲሰነዝር እጁን ጋም አድርጋ በቴስታ መለሰችው። ትዝ ይለኛል የተማሪው ፉጨት ምናምን.. ቴስታውን መቋቋም አልቻለም እኛም አጋጣሚውን ተጠቅመን ለሁለት ቀጠቀጥነው። ከስር የተደረቡም ነበሩ.. በቃ ክፍሉ ፉጨት በፉጨት ሆነ። ከዛ እኛ ክፍሉን ለቀን ወጣን፤ በንጋታው ትምህርት ቤት ስንገባ በቃ የሌለ አከባብደው አዩን። ከዛ ጊዜ ጀምሮ እስካሁን ክብሮ ነን፤ በረከትም ይቅርታ ጠየቀን ግን አሁንም ድረስ ይፈራናል በቃ ይኸው ነው።>>
<<በለውውው የኔ ውዶች አኮራቹኝ>> ኢክሩ ዩሲን ስታቅፍት እኔ ራቢን አቀፍኳት።
<<አሪፍ አድርጋቹ ነው የቀጣቹት የኔ ጀግናዎች። አሁንም ቢሆን ማንም ከልኩ አያልፍም፤ በየትኛውም መንገድ እኛ ላይ እንዲደርሱብን አንፈቅድላቸውም። ነገራቶችን በቅን መንገድ እንፈታቸዋለን፤ ድንበሩ አልፎ ለሚመጣብን የሚገባውን እንሰጠዋለን። አይደል ውዶቼ >> ሶስቱንም አፈራርቄ አየሁዋቸው።
ኢክሩ ከውብ ፈገግታዋ ጋር አይን አይኔን እያየች <<ኢብቲ አንቺ እኮ አትናገሪ.. ንግግሮችሽ ሁሌም ወደ ልባችን ይገባሉ፤ ደግሞ አራት ነን አላህ እስካለያየን ድረስ..>>
<<እንዴ ሰዐቱን እዩትማ!>> ራቢ ሰዐቷን አየት አደረገች።
<<ወይኔ ሰላት ረፈደብን ገና አንድ ምሣቃ ይቀረናል እኮ.. እዛ ከሄድንማ አንደርስም በቃ እዚው እንስገድ እእ ውዶች>> ዩስራ ምሣቃዎቹን ዘጋጋች። በዩስሪ ሃሣብ ተስማምተን የክፍላችንን በር ዘግተን ሂጃብ አንጥፈን ወደ ሰላታችን ገባን፤ ስንጨርስ ከክፍል ወጥተን ዞር ዞር ማለት ጀመርን። በዛው ሎሊፖፕ ገዝተን ተመለስን። እንደለመድነው ኢክሩን ሸኝተን ወደ ክፍላችን ገባን።
*
እኛ ቦታችን ጋር ተቀመጥን እነ ባቢ ደግሞ ከፊታችን ተቀምጠው እየተተራረቡ ፈታ ያረጉናል፤ እኛ እንስቃለን ሙድ እንይዛለን። እንዲህ እያለን አስተማሪው መጣ፤ ብዛት ያላቸው ወረቀቶች ይዟል። የክፍል ሃላፊያችን እንደሆነና በቡድን ሊከፋፍለን እንደሆነ ነገረን። ጎበዝ ተማሪዎችን የቡድን መሪ እንዲሁም ጸሃፊ እንደሚሆኑ እያስረዳን አምና የሚያውቋቸው ጎበዝ ተማሪዎችን ስም መጥራት ጀመረ። አራት ተማሪዎች ተጠሩ ስምንት ቡድን ስለሆነ ተጨማሪ አራት ተማሪ እንደሚፈልግ ነገረን። <ከሌላ ትምህርት ቤት የመጣችሁ ከሰማንያ በላይ ነጥብ ያላችሁ..> ሲል ሁሉም ዝም ሲሉ መጣሁ ብሎ ከክፍል ወጣ። ራቢ <ለምን አትሆኚም?> ብላ ተቆጣችኝ። እንደማልፈልግና ባይሆን እነሱ ለምን እንደማይሆኑ ስጠይቃቸው እነሱም እንደማይፈልጉ ነገሩኝ። ሶስታችንም የቡድን መሪ ከሆንን አንድ ላይ መሆን ስለማንችል ነው።
ባቢ <<ዱዝ ሁነሽ ነዋ ከዛ ትምህርት ቤት የተባረርሽው.. እኛማ ጠጋ ጠጋ ያልነው ቀለሜ መስለሽን አይይይይ ተበላን!>>
<<ሃሃ ባክህ አላወካትም ሚኒስትሪ በሷ ነው የምታልፈው ለዛውም ሰቅለህ>> ራቢ ጥብርር እያለች መለሰችለት። ራቢና ባቢ እየተከራከሩ አስተማሪው መጣ።
<<እሺ አሁን ስማቹን የምጠራቹ ወደዚህ ትመጣላችሁ>> ብሎ ስም መጥራት ጀመረ። ከአራቱ ተማሪዎች ሶስቱን ጠራ አንዱን ቀነሰው ከዛም ራቢያና ዩስራ ጠራ <<እንዴት እናንተን እረሳለሁ? እናንተስ እንዴት ዝም ትላላችሁ? አምናም የቡድን መሪ ነበራቹ አይደል>> ብሎ ሌላ ተማሪዎችን ጠራ... ሁለቱ አዲስ ነበሩ፤ የፈሩ ይመስላሉ። ቀጥሎ ኢንቲሣር ብሎ ተጣራ ራቢ <<ኢብቲሣምን ነው?>> ጠየቀችው። ድጋሚ ወረቀቱን አይቶ <<ይቅርታ ኢብቲሣም የት አለች?>>
<<ኢብቲ ነይ>> ዩሲ ከነሱ ጋር በመጠራቴ ደስ ብሏት፤ እኔ ግን መውጣት አልፈለኩም። ከተቀመጥኩበት ተነስቼ ቲቸር ይቅርታ <<እኔ የቡድን መሪ መሆን አልፈልግም>> አልኩት።
<<ለምን?>>
<<በቃ ስለማልፈልግ ነው ...>>
አስተማሪው ቆጣ እያለ <<መጀመሪያ ከሰማንያ በላይ ነጥብ ያላችሁ ስል ዝም አልሽ። ዘጠና አራት ነጥብ ይዘሽ በዚህ መሪ አልሆንም ትያለሽ?>>
<<እሺ በቃ ጸሃፊ እሆናለው በዩስራ ወይም በራቢያ ቡድን>> እየፈራሁ ነበር የተናገርኩት።
<<እኔ መች ምረጪ አልኩሽ?>> አስተማሪው ተቆጣ። ምንም አማራጭ እንደሌለኝ ሣውቅ ወጥቼ ከነ ዩሲ ጋር ተቀላቀልኩ። መዳድቦ ከጨረሰ ቡኃላ የቡድን አባላት ያለበትን ወረቀት ለየግል ሰጠን ወረቀቱን ይዘን ወደ ቦታችን ተመለስን።
አስተምሮ ሲጨርስ ከነገ ጀምሮ ሁሉም ተማሪ በየቡድኑ እንዲቀመጥ ካልሆነ እርምጃ እንደሚወስድ ነግሮን ወጣ። ባቢ ወረቀቶቹን ተቀብሎን የቡድኖቹን ክፍፍል ማየት ጀመረ <<በለው አቤላ ከራቢያ ጋር ነህ ብዙም አልራክም፤ እኔና አንተን የት ከቶን ይሁን>> ማሂን እያየ። የነሱን ስም ፍለጋ ቀጣዩን ወረቀት ማየት ጀመረ።
<<በለውውው እኔ ደግሞ ከዩስራ ጋር ዋው>>
<<እኔን ከኢብቲ ጋር አርጎኝ ነዋ እየው እስቲ>> ማሂር ለማየት እየቸኮለ። ባቢ ለኔ የተሰጠኝን ወረቀት ማየት ጀመረ።
<<ቲሽ ሎጋው እዚህም የለህም>> ማሂ ከፋው ከጓደኞቹ ጋር ስለተለየ መሰለኝ እኛም ዝም አልን። የሱ ስም የሌላ ቡድን መሪ ወረቀት ላይ ስለሚሆን የት ቡድን እንደሆነ ለማወቅ አልቻልንም።
<<ቆይ እንዲ የደበራችሁ የተለያየ ቡድን ስለሆናቹ ነው? እህ... ክፍል ሁላ ባለመለያየታቹ አመስግኑ>> ቀለክ ላደርገው እየሞከርኩ። ማንም ምንም አልተናገረም ባቢ ንግግሩን ቀጠለ <<እሺ ለምን እዚው ቅርብ ቅርብ አናደርገውም እእ.. አስተማሪው ቦታ ከሚመርጥልን እኛ እንደምንፈልገው እናድርገው እእ.. በናታችሁ ዝም አትበሉ ከቀጣዩ ክላስ ቡኃላ እናስተካክላለን እሺ>> ራቢም ተስማማች።
<<እሺ>> ቀጣዩን ክላስ ከተማርን ቡኃላ ወደ ቤት ሰዐት ላይ ሁሉም ተማሪ ሲወጣ እኔና ዩስራ ውጪ ሆነን እነሱ ለአራት አስተካክለው ጠሩን።
ስንገባ ሌላ ክፍል ነው የሚመስለው። ስምንት ቡድን ሰርተው የቡድን ቁጥር ከፋፍለው ነበር። እኔ ቡድን አምስት፣ እነዩስራ ስድስት፣ ራቢ ደግሞ ሰባት አደረጉን፤ ያው እንዳንራራቅም ነው ቅርብ ለቅርብ ነን።
www.tgoop.com/Habibacalligraphy



tgoop.com/Habibacalligraphy/1942
Create:
Last Update:

የባከኑ ቀናት
ክፍል ስድስት
(ሂባ ሁዳ)
.
<< <እንዲው እንዳማረብህ ይቅርታ ልጠይቅህ> ፈገግ አለልኝ፤ በዚህ ቅፅበት ጥሬ እህል እንደሆነ ተሰማኝ። ወደ ተማሪዎች ዞር አልኩ የሚሆነውን ለማየት የቸኮሉ ይመስላሉ። ራቢ እንደተናደደችብኝ ታስታውቃለች፤ ባቢ አጠገቧ አለ... ብዙ ጥያቄ እንዳለው አይኖቹ ይናገራሉ። ፊቴን ወደ በረከት መለስ አደረኩ ምን አልባት ይህ ቅጽበት ለሱ ድል ከማድረግ በላይ በሃሴት የተሞላ ነበር። ከታች ወደ ላይ ተመለከትኩት ትልቅ ድብ የማይ መሰለኝ... ግዝፈቱ አላስፈራኝም። ወደ ኃላ ሄድኩ፤ ከበረከት ጀርባ ቆምኩኝ። ከየት ባመጣሁት ሃይል እና ግፊት እንደሆነ ባላውቅም በቀኝ እጄ አንገቱን እንቅ አድርጌ እንዴት መሬት ላይ እንደተዘረረ አሁንም ድረስ ይገርመኛል፤ ክፍሉ በአንዴ ወደ ሁከት ተቀየረ፤ ክብ ሰርተው መሃል አስገቡን። ከወደቀበት ተነስቶ አንድ ቦክስ ሰነዘረብኝ አልሣተኝም ነበር እኔም በርግጫ አልኩት። ታውቃላቹ ያኔ አምስተኛ ክፍል እያለን ከወንዶች ጋር እንደባደብ የነበረው ጠቅሞኛል... ግን ቦክሱ አቅም አሣጥቶኝ ነበር እናም ከኃላ አንድ ልጅ ሲገፋኝ ወደኩኝ። በረከት አጋጣሚውን ለመጠቀም በጉልበቱ ተንበረከከ በቦክስ ሊደግመኝ ሲል ከኃላ ተገፋና ወደቀ፤ ሲዞር ራቢ ናት። እኔን ትቶ ሲነሣ አብሬው ተነሣሁ፤ ወደ ራቢ ተጠግቶ እጁን ሲሰነዝር እጁን ጋም አድርጋ በቴስታ መለሰችው። ትዝ ይለኛል የተማሪው ፉጨት ምናምን.. ቴስታውን መቋቋም አልቻለም እኛም አጋጣሚውን ተጠቅመን ለሁለት ቀጠቀጥነው። ከስር የተደረቡም ነበሩ.. በቃ ክፍሉ ፉጨት በፉጨት ሆነ። ከዛ እኛ ክፍሉን ለቀን ወጣን፤ በንጋታው ትምህርት ቤት ስንገባ በቃ የሌለ አከባብደው አዩን። ከዛ ጊዜ ጀምሮ እስካሁን ክብሮ ነን፤ በረከትም ይቅርታ ጠየቀን ግን አሁንም ድረስ ይፈራናል በቃ ይኸው ነው።>>
<<በለውውው የኔ ውዶች አኮራቹኝ>> ኢክሩ ዩሲን ስታቅፍት እኔ ራቢን አቀፍኳት።
<<አሪፍ አድርጋቹ ነው የቀጣቹት የኔ ጀግናዎች። አሁንም ቢሆን ማንም ከልኩ አያልፍም፤ በየትኛውም መንገድ እኛ ላይ እንዲደርሱብን አንፈቅድላቸውም። ነገራቶችን በቅን መንገድ እንፈታቸዋለን፤ ድንበሩ አልፎ ለሚመጣብን የሚገባውን እንሰጠዋለን። አይደል ውዶቼ >> ሶስቱንም አፈራርቄ አየሁዋቸው።
ኢክሩ ከውብ ፈገግታዋ ጋር አይን አይኔን እያየች <<ኢብቲ አንቺ እኮ አትናገሪ.. ንግግሮችሽ ሁሌም ወደ ልባችን ይገባሉ፤ ደግሞ አራት ነን አላህ እስካለያየን ድረስ..>>
<<እንዴ ሰዐቱን እዩትማ!>> ራቢ ሰዐቷን አየት አደረገች።
<<ወይኔ ሰላት ረፈደብን ገና አንድ ምሣቃ ይቀረናል እኮ.. እዛ ከሄድንማ አንደርስም በቃ እዚው እንስገድ እእ ውዶች>> ዩስራ ምሣቃዎቹን ዘጋጋች። በዩስሪ ሃሣብ ተስማምተን የክፍላችንን በር ዘግተን ሂጃብ አንጥፈን ወደ ሰላታችን ገባን፤ ስንጨርስ ከክፍል ወጥተን ዞር ዞር ማለት ጀመርን። በዛው ሎሊፖፕ ገዝተን ተመለስን። እንደለመድነው ኢክሩን ሸኝተን ወደ ክፍላችን ገባን።
*
እኛ ቦታችን ጋር ተቀመጥን እነ ባቢ ደግሞ ከፊታችን ተቀምጠው እየተተራረቡ ፈታ ያረጉናል፤ እኛ እንስቃለን ሙድ እንይዛለን። እንዲህ እያለን አስተማሪው መጣ፤ ብዛት ያላቸው ወረቀቶች ይዟል። የክፍል ሃላፊያችን እንደሆነና በቡድን ሊከፋፍለን እንደሆነ ነገረን። ጎበዝ ተማሪዎችን የቡድን መሪ እንዲሁም ጸሃፊ እንደሚሆኑ እያስረዳን አምና የሚያውቋቸው ጎበዝ ተማሪዎችን ስም መጥራት ጀመረ። አራት ተማሪዎች ተጠሩ ስምንት ቡድን ስለሆነ ተጨማሪ አራት ተማሪ እንደሚፈልግ ነገረን። <ከሌላ ትምህርት ቤት የመጣችሁ ከሰማንያ በላይ ነጥብ ያላችሁ..> ሲል ሁሉም ዝም ሲሉ መጣሁ ብሎ ከክፍል ወጣ። ራቢ <ለምን አትሆኚም?> ብላ ተቆጣችኝ። እንደማልፈልግና ባይሆን እነሱ ለምን እንደማይሆኑ ስጠይቃቸው እነሱም እንደማይፈልጉ ነገሩኝ። ሶስታችንም የቡድን መሪ ከሆንን አንድ ላይ መሆን ስለማንችል ነው።
ባቢ <<ዱዝ ሁነሽ ነዋ ከዛ ትምህርት ቤት የተባረርሽው.. እኛማ ጠጋ ጠጋ ያልነው ቀለሜ መስለሽን አይይይይ ተበላን!>>
<<ሃሃ ባክህ አላወካትም ሚኒስትሪ በሷ ነው የምታልፈው ለዛውም ሰቅለህ>> ራቢ ጥብርር እያለች መለሰችለት። ራቢና ባቢ እየተከራከሩ አስተማሪው መጣ።
<<እሺ አሁን ስማቹን የምጠራቹ ወደዚህ ትመጣላችሁ>> ብሎ ስም መጥራት ጀመረ። ከአራቱ ተማሪዎች ሶስቱን ጠራ አንዱን ቀነሰው ከዛም ራቢያና ዩስራ ጠራ <<እንዴት እናንተን እረሳለሁ? እናንተስ እንዴት ዝም ትላላችሁ? አምናም የቡድን መሪ ነበራቹ አይደል>> ብሎ ሌላ ተማሪዎችን ጠራ... ሁለቱ አዲስ ነበሩ፤ የፈሩ ይመስላሉ። ቀጥሎ ኢንቲሣር ብሎ ተጣራ ራቢ <<ኢብቲሣምን ነው?>> ጠየቀችው። ድጋሚ ወረቀቱን አይቶ <<ይቅርታ ኢብቲሣም የት አለች?>>
<<ኢብቲ ነይ>> ዩሲ ከነሱ ጋር በመጠራቴ ደስ ብሏት፤ እኔ ግን መውጣት አልፈለኩም። ከተቀመጥኩበት ተነስቼ ቲቸር ይቅርታ <<እኔ የቡድን መሪ መሆን አልፈልግም>> አልኩት።
<<ለምን?>>
<<በቃ ስለማልፈልግ ነው ...>>
አስተማሪው ቆጣ እያለ <<መጀመሪያ ከሰማንያ በላይ ነጥብ ያላችሁ ስል ዝም አልሽ። ዘጠና አራት ነጥብ ይዘሽ በዚህ መሪ አልሆንም ትያለሽ?>>
<<እሺ በቃ ጸሃፊ እሆናለው በዩስራ ወይም በራቢያ ቡድን>> እየፈራሁ ነበር የተናገርኩት።
<<እኔ መች ምረጪ አልኩሽ?>> አስተማሪው ተቆጣ። ምንም አማራጭ እንደሌለኝ ሣውቅ ወጥቼ ከነ ዩሲ ጋር ተቀላቀልኩ። መዳድቦ ከጨረሰ ቡኃላ የቡድን አባላት ያለበትን ወረቀት ለየግል ሰጠን ወረቀቱን ይዘን ወደ ቦታችን ተመለስን።
አስተምሮ ሲጨርስ ከነገ ጀምሮ ሁሉም ተማሪ በየቡድኑ እንዲቀመጥ ካልሆነ እርምጃ እንደሚወስድ ነግሮን ወጣ። ባቢ ወረቀቶቹን ተቀብሎን የቡድኖቹን ክፍፍል ማየት ጀመረ <<በለው አቤላ ከራቢያ ጋር ነህ ብዙም አልራክም፤ እኔና አንተን የት ከቶን ይሁን>> ማሂን እያየ። የነሱን ስም ፍለጋ ቀጣዩን ወረቀት ማየት ጀመረ።
<<በለውውው እኔ ደግሞ ከዩስራ ጋር ዋው>>
<<እኔን ከኢብቲ ጋር አርጎኝ ነዋ እየው እስቲ>> ማሂር ለማየት እየቸኮለ። ባቢ ለኔ የተሰጠኝን ወረቀት ማየት ጀመረ።
<<ቲሽ ሎጋው እዚህም የለህም>> ማሂ ከፋው ከጓደኞቹ ጋር ስለተለየ መሰለኝ እኛም ዝም አልን። የሱ ስም የሌላ ቡድን መሪ ወረቀት ላይ ስለሚሆን የት ቡድን እንደሆነ ለማወቅ አልቻልንም።
<<ቆይ እንዲ የደበራችሁ የተለያየ ቡድን ስለሆናቹ ነው? እህ... ክፍል ሁላ ባለመለያየታቹ አመስግኑ>> ቀለክ ላደርገው እየሞከርኩ። ማንም ምንም አልተናገረም ባቢ ንግግሩን ቀጠለ <<እሺ ለምን እዚው ቅርብ ቅርብ አናደርገውም እእ.. አስተማሪው ቦታ ከሚመርጥልን እኛ እንደምንፈልገው እናድርገው እእ.. በናታችሁ ዝም አትበሉ ከቀጣዩ ክላስ ቡኃላ እናስተካክላለን እሺ>> ራቢም ተስማማች።
<<እሺ>> ቀጣዩን ክላስ ከተማርን ቡኃላ ወደ ቤት ሰዐት ላይ ሁሉም ተማሪ ሲወጣ እኔና ዩስራ ውጪ ሆነን እነሱ ለአራት አስተካክለው ጠሩን።
ስንገባ ሌላ ክፍል ነው የሚመስለው። ስምንት ቡድን ሰርተው የቡድን ቁጥር ከፋፍለው ነበር። እኔ ቡድን አምስት፣ እነዩስራ ስድስት፣ ራቢ ደግሞ ሰባት አደረጉን፤ ያው እንዳንራራቅም ነው ቅርብ ለቅርብ ነን።
www.tgoop.com/Habibacalligraphy

BY Habiba Calligraphy




Share with your friend now:
tgoop.com/Habibacalligraphy/1942

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

Those being doxxed include outgoing Chief Executive Carrie Lam Cheng Yuet-ngor, Chung and police assistant commissioner Joe Chan Tung, who heads police's cyber security and technology crime bureau. The Standard Channel Concise Other crimes that the SUCK Channel incited under Ng’s watch included using corrosive chemicals to make explosives and causing grievous bodily harm with intent. The court also found Ng responsible for calling on people to assist protesters who clashed violently with police at several universities in November 2019. Telegram channels enable users to broadcast messages to multiple users simultaneously. Like on social media, users need to subscribe to your channel to get access to your content published by one or more administrators.
from us


Telegram Habiba Calligraphy
FROM American