HABIBACALLIGRAPHY Telegram 1943
የባከኑ ቀናት
ክፍል ሰባት
(ሂባ ሁዳ)
.
.
ዛሬ ራቢ ቆይታብናለች። እኛም በጣም ሲረፍድ ጥለናት ሄድን። ጊቢ ስንገባ በማርፈዳችን ተቀጥተን የተመታውን እጃችንን እያሻሸን ወደ ክፍል አመራን። አስተማሪው ገብቶ ማስተማሩን ጀምሮ ነበር፤ ትንሽ ካስቆመን ቡኃላ እንድንቀመጥ ፈቀደልን። ሁሉም በቡድን ቡድን ተቀምጦል ራቢም አለች። እንዴ እስካሁን እሷን ስንጥብቅ አርፍደን እሷ ግን እዚህ ናት የተመታሁትም አሞኝ ስለነበር ተናድጄ ራቢን ገፍቻት አለፍኩ። ትናንት በተነጋገርነው ቦታ ላይ ቁጭ አልኩኝ። ደብተሬን ሣወጣ ባቢን አየሁት በእጁ ሃይ አለኝ ብናደድም ፈገግ አስባለኝ ከእሱ አጠገብ ዩሲ አለች እሷ ግን አልተናደደችም ነበር። ከእነሱ ፊት ደግሞ የነ ራቢ ቡድን አለ ከራቢ ጋር አይን ለአይን ስንገጣጠም ዞር አልኩባት። አጠገቧ አቤላ አለ... ባቢ እንዳለውም አልተራራቅንም፤ ፊት ለፊት ለመተያየት እንዲመች አድርገው ነው ያስተካከሉት። <<ትምህርቱን ረሣሁት እኮ እናንተን ሣይ ብዙ ጻፋቹ እንዴ?>> ብዬ ወደ ብላክቦርዱ ሣይ ከማሂ ጋር ተገጣጠምን። እስካሁን አላስተዋልኩትም ነበር፤ ስገባም ከአጠገቡ ነበር ያልፍኩት። ደግሞ ርቀት አለን እንዴት እዛ ሊሄድ ቻለ? ..ወይ ጉድ ብዙ ነገር ሳብሰለስል አስተማሪው ሳልፅፍ አጠፋብኝ። ቀጣዩን መፃፍ ጀመረ፤ በቃ አንደኛዬን በኃላ እፅፈዋለሁ ብዬ ተውኩት። ሲያስረዳ ከደብተሬ ጀርባ አጭር ማስታወሻ መያዝ ጀመርኩ፤ ዛሬ ደግሞ አስተማሪዎች ላይ በላይ ነው የሚገቡት ምንም ክፍተት አልተፈጠረም። ይኸው የእረፍት ሰዐት ደርሶ አስተማሪው ወጣ።
<<ኡፍፍፍ ጭንቀት ሊገለኝ ነበር እኮ..>> ባቢ ከቦታው እየተነሣ።
<<ድሮም እኮ የትምህርት ነገር አይሆንልህ>> ራቢ ሂጃቧን እያስተካከለች ትመልስለታለች።
ደብተሬን አስገባብቼ ወደ በሩ በችኮላ መሄድ ጀመርኩ። ራቢ ቦርሣዋን እየዘጋች <<ኢብቲ በአላህ ጠብቂኝ...>> አለችኝ። ማሂ ወደነ ባቢ ጋር እየሄደ ነበር፤ መሃል ላይ ተገጣጠምን። ራቢም ወደኛ እየመጣች ነበር። <<በናትህ እንዳታሣልፋት>> ራቢ እንዲያስቆምላት ጠየቀችው። ማሂ ከፊቴ እንደቆመ ገፍትሬው አለፍኩ። ከክፍል ስወጣ ኢክሩ እየመጣች አገኘኋት። ተቃቅፈን ሰላም ስንባባል ራቢ መጣች... ሁለታችንንም አቀፈችን ምንም አላኳትም። ግንባሬን ሣመችኝ፤ እንደማኩረፍ እያልኩ <<በቃ አረሳሳሽ?>>
<<ኢብቲ ደግሞ ይቅርታ.. ቆይ ልንገርሽ ለምን እንዳልመጣሁ..>>
<<ኧረ ተይው ላለፈ ነገር። በርግጥ ተናድጄብሽ ነበር ግን አሁን አስጠፋሽብኝ በሰላም ከሆነ ጣጣ የለውም።>> ለማብረድ እየሞከርኩ።
<<ለዚህ እኮ ነው ልዩ ነሽ የምልሽ። ነይ በዚህ>> ዘላ ጉንጬን ሣመችኝ። እርቋት አይደለም መዝለል ስለምትወድ እንጂ.. ዩሲ ብንጠብቃትም ከክፍል ስላልወጣች ተያይዘን ወደ ክፍል ገባን። በሩን ተደግፎ የቆመው ባቢ <<ቅድም ስትጨቃጨቁ ወታቹ አሁን ተቃቅፎ መግባት ጠላትን ለማናደድ ይመስላል።>>
<<ገና ከመታረቃችን ልታጣላን ነው እንዴ ሆ!>> ራቢ ከአጠገቡ ቆማ መልስ ሰጠችው። እኔና ኢክሩ ወደ ውስጥ ገባን። ኢክሩ ዩሲን ሰላም ብላት አዲሱን ቦታችንን አሳይቻት ያለፈኝን ልትፅፍልኝ ተቀመጠች። ዩሲም እየፃፈች ነበር፤ አብረው መፃፍ ጀመሩ። እኔም እነ ባቢ ጋር ሄጄ ተቀላቀልኳቸው።
*
እንዲህ እንዲህ እያል ጊዜው ሄደ... ቁምነገር ያልተሰራባቸው ቀናት ተቆጠሩ። ከሙሉ ተማሪው ጋር ተግባባን ከነ ባቢ ጋር ደግሞ በጣም ተቀራረብን። ላየን እንደ አዲስ ተማሪ ሳይሆን ከድሮ ጀምሮ የምንተዋወቅ እንመስል ነበር። የክፍል ሃላፊያችን ካልገባ በቀር በቡድን አንቀመጥም። ሶስታችንም ከፊት ካለው ወንበር አብረን እንቀመጣለን አስተማሪ እስኪ ገባ ባለን ክፍተት እንጠያየቃለን። ዩስራ ሂሣብ ትምህርት ነፍሷ ነው፤ እኔ ደግሞ ብዙም አይደለሁም ባይሎጂ ግን የሚችለኝ የለም። ራቢ ደግሞ ኬሚስትሪ የግሏ ነው፤ በየትምህርቱ ላይ የተለያየ ቦታ መስጠታችን እኛን ጠቅሞናል። ሶስታችንም አንድ ላይ ስለምንሰራ የክፍሉ አሪፍ ውጤት እንድንይዝ ረድቶናል።
*
<<ኧረ ልጅት ምንድነው እናቷን ከገበያ እስክትመጣ የምትጠብቅ ልጅ የመሰልሽው>> ባቢ ወደኔ እየመጣ ንግግሩን ቀጠለ። ከነሱ ቀድሜ ክፍል ተቀምጬ ነበር የመጡት። በቀናት ሂደት ያልተቀየረው የባቢ ተጫዋች ምላስ ነው። <<እእ እሱ ካልተመቸሽ ደግሞ ፎንቃዋን የምትጠብቅ አፍቃሪ የመሰልሽው ይሁና>>
<<ባቢ ይሄ ከፎንቃም በላይ ነው። ከትምሮ ይሁን ከአስተማሪው አልተለየም እንጂ!>> አቤላ ተከትሎት እየገባ ጭንቅላቱን ከግራ ወደ ቀኝ ያዞራል። እንዲ የሚያደርገው እኔን ለማናደድ ሲፈልግ ነው። የምርም ግን ያናድደኛል፤ ይኸው ተሣካለት።
<<እስቲ አቤላ ነገር ከምትበላ ሂድ ብላክቦርዱን አፅዳው>> ያናደደኝን ልመልስለት እየሞከርኩ።
<<ባክሽ አልሰማሽም፤ ዛሬ እኔ አላፀዳውም>>
<<ነው?>>
<<እናቴን አዎ ኢብቲ ምን ታመጪያለሽ>>
<<ኧረ.. ምንም እንዴት እንደማስጠፋህ አሳይሃለው ...>>
<<ይኸው እየነጠረ መጣልሽ>> ባቢ ወደ ቦታው ተመለሰ፤ የባይሎጂ አስተማሪ ገባ።
<<ሄይ ሄይ ተማሪዎች ዛሬ ማን ነው የሚያፀዳው?>>
<<እኔ አፀዳለው ቲቸር>>
<<ኦውው ዛሬ ኢብቲሣም ናት>> ሲያቀብለኝ ተቀበልኩት። ለማፅዳት ወደ ብላክ ቦርዱ ከዞርኩበት ወደ ተማሪው መለስ ብዬ <<ኧረ ችግር የለውም>> አልኩ፤ አቤላን እያየሁ። ከባቢ ጋር ተጠቃቀስን።
<<ምን?>> አቤላ ግራ እየተጋባ ያየኛል። ባቢ ወደ አቤላ በመዞር <<ኢብቱ አንቺ ጥቁር ሂጃብ ስላደረግሽ ብናኙ እንዳያበላሽብሽ ብሎ ነው>>
<<እሺ አቤላ አመሰግናለው ይኸው ና አጥፋ>> ዳስተሩን አስቀምጬው ተቀምጥኩ። አቤላ እየበሸቅ አጥፍቶ ጨረሰ።
<<እናቴን ባልሰራላቹ>> ብሎኝ ወደ ቦታው ሄደ። ባይሎጂ መምህራችን የእለቱን ትምህርት ጀመረ
.
የዛሬው ትምህረት ትንሽ ውስብስብ ያለ ነው፤ በዛ ላይ አስተማሪው ቸኩሏል።
<<ኡፍ ምንድነው የሚደበላልቀው?>> ራቢ ትነጫነጫለች።
<<ራቢ ዝም ብለሽ ከተከታተልሹ ግልፅ ይሆንልሻል።>>
<<ባክሽ ዛሬ ምን እንደሚል ሁላ መረዳት አልቻልኩም በቃ ኢብቲ እንደለመደብሽ በኃላ ታስረጂኛለሽ>> ደብተሯ ላይ ጋደም አለችበት። ዩሲ እየተደገፍቻት <<ስሚ ቀጣይ ኬሚስትሪ እኮ ነው እንቅልፍ እንዳይወስድሽ ..>>
<<እሱ መች ጠፋኝ.. ነቃ ብዬ እንድማር አሁን እረፍት ላድርግ እንጂ፤ ባይሆን ዝም በሉ ና ተከታተሉት።>> አለችና ተጋደመች። ትንሽ እንደተማርን <<ለዛሬ ይበቃል ጥያቄ ያለው አለ?>> ሶስት ልጆች ጥያቄ አቀረቡለት። የነሱን ከመለሰ በኋላ..
<<ቲቸር>> ማሂ ፀጉሩን እያሻሸ ጠራው።
<<ወዬ>> ጋወኑን ለማውለቅ እየተቻኮለ <<ኧረ ምንም አልገባኝም አትደግምልኝም?>> ባይሎጂ መምህራችን ፈታ ያለ ስለሆነ ነገር አያከርም።
<<በጣም አሪፍ ኢብቲሣም ታስረዳሃለች። የናንተንም ጥያቄ እሷ ትመልስላችሁ፤ የቀረ ካለ ደግሞ ነገ እናያለን በሉ ተማሪዎች ባይ ባይ>>.. ቲቸር ፊቱን ወደኔ አዞረ።
<<ኢብቲሣም እንቺም ዛሬ አልገባሽም?>>
<<አይ ገብቶኛል ግን ሰዐት አለን አላለቀም እኮ>>
www.tgoop.com/Habibacalligraphy



tgoop.com/Habibacalligraphy/1943
Create:
Last Update:

የባከኑ ቀናት
ክፍል ሰባት
(ሂባ ሁዳ)
.
.
ዛሬ ራቢ ቆይታብናለች። እኛም በጣም ሲረፍድ ጥለናት ሄድን። ጊቢ ስንገባ በማርፈዳችን ተቀጥተን የተመታውን እጃችንን እያሻሸን ወደ ክፍል አመራን። አስተማሪው ገብቶ ማስተማሩን ጀምሮ ነበር፤ ትንሽ ካስቆመን ቡኃላ እንድንቀመጥ ፈቀደልን። ሁሉም በቡድን ቡድን ተቀምጦል ራቢም አለች። እንዴ እስካሁን እሷን ስንጥብቅ አርፍደን እሷ ግን እዚህ ናት የተመታሁትም አሞኝ ስለነበር ተናድጄ ራቢን ገፍቻት አለፍኩ። ትናንት በተነጋገርነው ቦታ ላይ ቁጭ አልኩኝ። ደብተሬን ሣወጣ ባቢን አየሁት በእጁ ሃይ አለኝ ብናደድም ፈገግ አስባለኝ ከእሱ አጠገብ ዩሲ አለች እሷ ግን አልተናደደችም ነበር። ከእነሱ ፊት ደግሞ የነ ራቢ ቡድን አለ ከራቢ ጋር አይን ለአይን ስንገጣጠም ዞር አልኩባት። አጠገቧ አቤላ አለ... ባቢ እንዳለውም አልተራራቅንም፤ ፊት ለፊት ለመተያየት እንዲመች አድርገው ነው ያስተካከሉት። <<ትምህርቱን ረሣሁት እኮ እናንተን ሣይ ብዙ ጻፋቹ እንዴ?>> ብዬ ወደ ብላክቦርዱ ሣይ ከማሂ ጋር ተገጣጠምን። እስካሁን አላስተዋልኩትም ነበር፤ ስገባም ከአጠገቡ ነበር ያልፍኩት። ደግሞ ርቀት አለን እንዴት እዛ ሊሄድ ቻለ? ..ወይ ጉድ ብዙ ነገር ሳብሰለስል አስተማሪው ሳልፅፍ አጠፋብኝ። ቀጣዩን መፃፍ ጀመረ፤ በቃ አንደኛዬን በኃላ እፅፈዋለሁ ብዬ ተውኩት። ሲያስረዳ ከደብተሬ ጀርባ አጭር ማስታወሻ መያዝ ጀመርኩ፤ ዛሬ ደግሞ አስተማሪዎች ላይ በላይ ነው የሚገቡት ምንም ክፍተት አልተፈጠረም። ይኸው የእረፍት ሰዐት ደርሶ አስተማሪው ወጣ።
<<ኡፍፍፍ ጭንቀት ሊገለኝ ነበር እኮ..>> ባቢ ከቦታው እየተነሣ።
<<ድሮም እኮ የትምህርት ነገር አይሆንልህ>> ራቢ ሂጃቧን እያስተካከለች ትመልስለታለች።
ደብተሬን አስገባብቼ ወደ በሩ በችኮላ መሄድ ጀመርኩ። ራቢ ቦርሣዋን እየዘጋች <<ኢብቲ በአላህ ጠብቂኝ...>> አለችኝ። ማሂ ወደነ ባቢ ጋር እየሄደ ነበር፤ መሃል ላይ ተገጣጠምን። ራቢም ወደኛ እየመጣች ነበር። <<በናትህ እንዳታሣልፋት>> ራቢ እንዲያስቆምላት ጠየቀችው። ማሂ ከፊቴ እንደቆመ ገፍትሬው አለፍኩ። ከክፍል ስወጣ ኢክሩ እየመጣች አገኘኋት። ተቃቅፈን ሰላም ስንባባል ራቢ መጣች... ሁለታችንንም አቀፈችን ምንም አላኳትም። ግንባሬን ሣመችኝ፤ እንደማኩረፍ እያልኩ <<በቃ አረሳሳሽ?>>
<<ኢብቲ ደግሞ ይቅርታ.. ቆይ ልንገርሽ ለምን እንዳልመጣሁ..>>
<<ኧረ ተይው ላለፈ ነገር። በርግጥ ተናድጄብሽ ነበር ግን አሁን አስጠፋሽብኝ በሰላም ከሆነ ጣጣ የለውም።>> ለማብረድ እየሞከርኩ።
<<ለዚህ እኮ ነው ልዩ ነሽ የምልሽ። ነይ በዚህ>> ዘላ ጉንጬን ሣመችኝ። እርቋት አይደለም መዝለል ስለምትወድ እንጂ.. ዩሲ ብንጠብቃትም ከክፍል ስላልወጣች ተያይዘን ወደ ክፍል ገባን። በሩን ተደግፎ የቆመው ባቢ <<ቅድም ስትጨቃጨቁ ወታቹ አሁን ተቃቅፎ መግባት ጠላትን ለማናደድ ይመስላል።>>
<<ገና ከመታረቃችን ልታጣላን ነው እንዴ ሆ!>> ራቢ ከአጠገቡ ቆማ መልስ ሰጠችው። እኔና ኢክሩ ወደ ውስጥ ገባን። ኢክሩ ዩሲን ሰላም ብላት አዲሱን ቦታችንን አሳይቻት ያለፈኝን ልትፅፍልኝ ተቀመጠች። ዩሲም እየፃፈች ነበር፤ አብረው መፃፍ ጀመሩ። እኔም እነ ባቢ ጋር ሄጄ ተቀላቀልኳቸው።
*
እንዲህ እንዲህ እያል ጊዜው ሄደ... ቁምነገር ያልተሰራባቸው ቀናት ተቆጠሩ። ከሙሉ ተማሪው ጋር ተግባባን ከነ ባቢ ጋር ደግሞ በጣም ተቀራረብን። ላየን እንደ አዲስ ተማሪ ሳይሆን ከድሮ ጀምሮ የምንተዋወቅ እንመስል ነበር። የክፍል ሃላፊያችን ካልገባ በቀር በቡድን አንቀመጥም። ሶስታችንም ከፊት ካለው ወንበር አብረን እንቀመጣለን አስተማሪ እስኪ ገባ ባለን ክፍተት እንጠያየቃለን። ዩስራ ሂሣብ ትምህርት ነፍሷ ነው፤ እኔ ደግሞ ብዙም አይደለሁም ባይሎጂ ግን የሚችለኝ የለም። ራቢ ደግሞ ኬሚስትሪ የግሏ ነው፤ በየትምህርቱ ላይ የተለያየ ቦታ መስጠታችን እኛን ጠቅሞናል። ሶስታችንም አንድ ላይ ስለምንሰራ የክፍሉ አሪፍ ውጤት እንድንይዝ ረድቶናል።
*
<<ኧረ ልጅት ምንድነው እናቷን ከገበያ እስክትመጣ የምትጠብቅ ልጅ የመሰልሽው>> ባቢ ወደኔ እየመጣ ንግግሩን ቀጠለ። ከነሱ ቀድሜ ክፍል ተቀምጬ ነበር የመጡት። በቀናት ሂደት ያልተቀየረው የባቢ ተጫዋች ምላስ ነው። <<እእ እሱ ካልተመቸሽ ደግሞ ፎንቃዋን የምትጠብቅ አፍቃሪ የመሰልሽው ይሁና>>
<<ባቢ ይሄ ከፎንቃም በላይ ነው። ከትምሮ ይሁን ከአስተማሪው አልተለየም እንጂ!>> አቤላ ተከትሎት እየገባ ጭንቅላቱን ከግራ ወደ ቀኝ ያዞራል። እንዲ የሚያደርገው እኔን ለማናደድ ሲፈልግ ነው። የምርም ግን ያናድደኛል፤ ይኸው ተሣካለት።
<<እስቲ አቤላ ነገር ከምትበላ ሂድ ብላክቦርዱን አፅዳው>> ያናደደኝን ልመልስለት እየሞከርኩ።
<<ባክሽ አልሰማሽም፤ ዛሬ እኔ አላፀዳውም>>
<<ነው?>>
<<እናቴን አዎ ኢብቲ ምን ታመጪያለሽ>>
<<ኧረ.. ምንም እንዴት እንደማስጠፋህ አሳይሃለው ...>>
<<ይኸው እየነጠረ መጣልሽ>> ባቢ ወደ ቦታው ተመለሰ፤ የባይሎጂ አስተማሪ ገባ።
<<ሄይ ሄይ ተማሪዎች ዛሬ ማን ነው የሚያፀዳው?>>
<<እኔ አፀዳለው ቲቸር>>
<<ኦውው ዛሬ ኢብቲሣም ናት>> ሲያቀብለኝ ተቀበልኩት። ለማፅዳት ወደ ብላክ ቦርዱ ከዞርኩበት ወደ ተማሪው መለስ ብዬ <<ኧረ ችግር የለውም>> አልኩ፤ አቤላን እያየሁ። ከባቢ ጋር ተጠቃቀስን።
<<ምን?>> አቤላ ግራ እየተጋባ ያየኛል። ባቢ ወደ አቤላ በመዞር <<ኢብቱ አንቺ ጥቁር ሂጃብ ስላደረግሽ ብናኙ እንዳያበላሽብሽ ብሎ ነው>>
<<እሺ አቤላ አመሰግናለው ይኸው ና አጥፋ>> ዳስተሩን አስቀምጬው ተቀምጥኩ። አቤላ እየበሸቅ አጥፍቶ ጨረሰ።
<<እናቴን ባልሰራላቹ>> ብሎኝ ወደ ቦታው ሄደ። ባይሎጂ መምህራችን የእለቱን ትምህርት ጀመረ
.
የዛሬው ትምህረት ትንሽ ውስብስብ ያለ ነው፤ በዛ ላይ አስተማሪው ቸኩሏል።
<<ኡፍ ምንድነው የሚደበላልቀው?>> ራቢ ትነጫነጫለች።
<<ራቢ ዝም ብለሽ ከተከታተልሹ ግልፅ ይሆንልሻል።>>
<<ባክሽ ዛሬ ምን እንደሚል ሁላ መረዳት አልቻልኩም በቃ ኢብቲ እንደለመደብሽ በኃላ ታስረጂኛለሽ>> ደብተሯ ላይ ጋደም አለችበት። ዩሲ እየተደገፍቻት <<ስሚ ቀጣይ ኬሚስትሪ እኮ ነው እንቅልፍ እንዳይወስድሽ ..>>
<<እሱ መች ጠፋኝ.. ነቃ ብዬ እንድማር አሁን እረፍት ላድርግ እንጂ፤ ባይሆን ዝም በሉ ና ተከታተሉት።>> አለችና ተጋደመች። ትንሽ እንደተማርን <<ለዛሬ ይበቃል ጥያቄ ያለው አለ?>> ሶስት ልጆች ጥያቄ አቀረቡለት። የነሱን ከመለሰ በኋላ..
<<ቲቸር>> ማሂ ፀጉሩን እያሻሸ ጠራው።
<<ወዬ>> ጋወኑን ለማውለቅ እየተቻኮለ <<ኧረ ምንም አልገባኝም አትደግምልኝም?>> ባይሎጂ መምህራችን ፈታ ያለ ስለሆነ ነገር አያከርም።
<<በጣም አሪፍ ኢብቲሣም ታስረዳሃለች። የናንተንም ጥያቄ እሷ ትመልስላችሁ፤ የቀረ ካለ ደግሞ ነገ እናያለን በሉ ተማሪዎች ባይ ባይ>>.. ቲቸር ፊቱን ወደኔ አዞረ።
<<ኢብቲሣም እንቺም ዛሬ አልገባሽም?>>
<<አይ ገብቶኛል ግን ሰዐት አለን አላለቀም እኮ>>
www.tgoop.com/Habibacalligraphy

BY Habiba Calligraphy




Share with your friend now:
tgoop.com/Habibacalligraphy/1943

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

fire bomb molotov November 18 Dylan Hollingsworth yau ma tei Hashtags Telegram Channels requirements & features The imprisonment came as Telegram said it was "surprised" by claims that privacy commissioner Ada Chung Lai-ling is seeking to block the messaging app due to doxxing content targeting police and politicians. Channel login must contain 5-32 characters
from us


Telegram Habiba Calligraphy
FROM American