HABIBACALLIGRAPHY Telegram 1946
የባከኑ ቀናት
ክፍል ዘጠኝ
(ሂባ ሁዳ)
.
.
<<በቃ እደጠረጠርኩት... ይወድሻል..>> ራቢ ነበረች።
<<አንቺ ደግሞ ሁሌ መጠርጠር.. እንደዛ እንኳን አይሆንም ዝም ብለሽ ነው።>> ምንም ልትሰማኝ አልቻለችም።
<<አንቺ እኮ ቆየ ይወዳታል ማለት ከጀመርሽ፤ አይደለም ይሄ ተጨምሮ>> ዩሲ የቀረውን ምግብ እየጎረሰች።
<<እሺ ካላመናችሁኝ የባለፈው ብቻ እኮ በቂ ማረጋገጫ ነበር እኮ እእ ምን ልትሉ>> ሁለታችንም ተያይተን <<የቱ?>> አልናት ለማስታወስ..
<<ባለፈው የብሄር ብሄረሰቦች ቀን ጊቢ ውስጥ ሲከበር ማሂር ስልኩን ክፍል ውስጥ ቻርጅ ላይ አድርጎ <ማንም እንዳይነካው!> ብሎ ወጣ። ቻርጅ አስቸግሮት አናዶት ነበር... አቤላ ላይ ሁላ <ለምን ነካኸው> ብሎ ጓ! ብሎ ነበር። እሱ ሲወጣ ኢብቲ ገባች። ስልኩ የማሂ እንደሆነ ስታውቅ ጋላሪ ላይ ገብታ ስትመሰጥ የሆነ ሰው ሄዶ ለማሂር ነገረው። ከውጪ ሲገባ በዛ አካሄዱ ላየውሟ የሌለ ያስፈራ ነበር፤ በሩን እንዴት ብርግድ እንዳደረገው ኢብቲም ደንግጣ ስልኩን ለቀቀችው፤ ማሂር ሄዶ እነሣውና <አንቺ ነሽ እንዴ የነካሽው? ደግሞ ተይው ግላሱ ነው አልተጎዳም> ቢላትስ፤ ከኋላ የነበረው ተማሪ እኮ ከአሁን አሁን አጋጫት እያለ... ሃሃሃሃ... አጅሬው ኢብቲ መሆኗን ሲያውቅ ምንም እንዳልተፈጠር <ስጨርሺ ቻርጅ ላይ አድርጊው ካስቸገረሽ ደግሞ ጥሪኝ> ብሎ ላሽ ቢልስ። እኔ ደግሞ ለኢብቲ ያለውን ቦታ ማየት ቻልኳ! እእ ምን ልትሉ ነው?>>
<<እኔ ግን ምንም እንዳዛ አላስብም ራቢ። ምን አልባት ሌላ ነገር ይሆናል እኮ ማን ያውቃል ..>> ሃሳቧ የሚያሳምን ነገር አለው፤ ግን ለመከላከል ሞከርኩ።
<<እኔም ኢብቲ እንዳለችው ነው። ራቢ እኛ በዚህ እድሜያችን እንዴት ይሄን እናስባለን? ማይሆን ነገር እኮ ነው።
እንርሣው ባይሆን የቅድሙን ጥያቄዎች እንስራቸው ምን ትላላችሁ?>> ዩሲ ጉዳዩን ለማስቀር ተባበረችኝ።
<<ካላችሁ ምን ይደረጋል ግን እኔ ያልኩት እውነት መሆኑን በቅርቡ ታረጋግጣላችሁ ጠብቁ ብቻ <ራቢ ብለሽ ነበርሽ> ስትሉ መስማቴ የማይቀር ነው>>
<<አንቺ ደግሞ አንዴ ነገር ከጀመርሽ ቡኃላ አትፋቺም ዩሲ እንጀምር በቃ!!>> ነገሩን ዘጋሁት።
*
ያን ቀን ከትምህርት ቤት መልስ ጥያቄዎችን ሰርተን ከተለያየን በኃላ ዛሬ መገናኘታችን ነው። እንደተለመደው ክፍል ገብተን መማር ከጀመርን ሰዐታት አልፈዋል። ምሳ ሰዕት ላይ ዩሲ ማሂን እንዳወራው አስታወሰችኝና የተቀመጠበት ሄድኩኝ።
<<ሰላም ማሂሬ>> ለማውራት እንዲመቸኝ ከጎኑ እየተቀመጥኩ።
<<እእ እንዴት ነሽ?>>
<<አልሃምዱሊላህ አለሁልህ.. ምነው አሞሃል እንዴ?>> ፊቱ ልክ አለመሰለኝም።
<<ብታመምስ...ማንም ለማከም ፍቃደኛ ካልሆነ..>>
<<ማለት እንዴት?>>
<<ካልገባሽ አንድ ቀን ይገባሻል...>>
ምንም ማሂ አልመስልሽ አለኝ። ቢያንስ የቅዳሜውን ባወራው በዛው ወሬ መቀየሻ ይሆነኛል ብዬ አሰብኩ።
<<እኔ ምልህ ማሂ..>>ምን ብዬ እንደምጀምርለት ሃሳብ ስፈልግ።
<<ምን ነው ችግር አለ?>> ከአይኔ ላይ ፍርሃቴን ያነበበው መሰለኝ።
<<ሣይሆን... ቅዳሜ በጣም ቸኩዬ ስለነበረ ነው የሄድኩት እሺ ..>>
<<እሺ>> እሱ በግድ ፈገግ ለማለት ይሞክራል፤ እኔ ደግሞ እያባበልኩት መሰለኝ። ትንሽ ዝም ካልን በኃላ
<<እና አሁን ንገረኛ ምንድነው ማሂ ...>>
<<ኧረ.. አሁንስ ጊዜ አለሽ ማለት ነው?>>
<<ያኔ እኮ...>>አላስጨረሰኝም
<<ነገርሽኝ እኮ በቃ!>>
<<እህህህ ማሂ አሁን ንገረኝ እያልኩሃ>> ንግግራችን ወደ ጭቅጭቅ መስመር መቀየር ጀመረ።
<<ምን እንድነግርሽ ነው የምትፈልጊው?>> ድምፁ ላይ ቁጣ ታክሎበታል። <<ልትነግረኝ የነበረውን ነዋ ቀስ ለማለት እየሞከርኩ ...>>
<<ተውኩት በቃ!>>
<<እህህህ ማሂር አታድርቀኝ እንግዲ...>>
<<ሁሉም ነገር ላንቺ ቀልድ ነዋ የሚመስልሽ..ለማንኛውም ማርፈድ ከትምህርት ቤት ይልቅ ህይወት ላይ ዋጋ ያስከፍላል!>> ሲቃ በተሞላበት ድምፅ። <<አመሰግናለሁ>> ብሎኝ እየፈጠነ ወደ ውጪ ወጣ። እኔም ምንም መናገር አልቻልኩም ነበር እዛው ቁጭ አልኩ። <ያ ኢላሂ ምን ጉድ ነው? ኡፍፍፍ ኢብቲሣም ምንድነው ያደረግሽው.. ቲሽሽሽ> በራሴ ተናደድኩ። ያኔ ጥዬው ባልሄድ ይሄ ሁሉ አይፈጠርም ነበር። ምናለ ባዳመጥኩት... በራሴ ተናድጃለው፤ ከፍቶኛልም። እዛው ወንበሩ ላይ ድፍት ብዬ ባለቅስ ደስ ይለኝ ነበር።
*
<<ምንሼ እስካሁን እእ? ስሚ አታዝጊ ተነሺና ተናገሪ...>> አንገቴን ቀና አድርጋ እስክነግራት ትጠብቀኛለች፤ ራቢ።
<<ምንም አላለኝም>>
<<ሃሃሃሃ ኧረ ባኪ እስካሁን አብራቹ ስትጫወቱ ነበራ ታዲያ ማን አሸነፈ? ሃሃሃ>> ራቢ የሚያበሽቅ ሳቋን ለቀቀችው። ምንም መናገር ስላልፈለኩ ዝም አልኳት። እሷ ግን ምንም ልትረዳኝ አልቻለችም።
<<ኧረ ይሄ ነገር ምንድነው እእ? ሚስጥር ነው እንዴ እህቴ..>> አላስጨረስኳትም
<<ኡፍፍፍ አንቺ ደግሞ ችግር አለብሽ አትፋቺም! ዞር በይ በናትሽ .. >>
<<እህህ ኢብቲ በአላህ ምን ሁነሽ ነው?>> ድምጿ ይሰማኛል ላዳምጣት ግን አልፈለኩም።
<<ውዴ ወዴት ነው ጥድፊያው?>>ዩሲ ነበረች።
<<መጣሁ። እንዳትከተይኝ!>> ፈርታኝ <እሺ> ብላ እዛው ቀረች።ብቻዬን አንድ ጥግ ስር ቁጭ ብዬ ደቂቃዎች አለፉ። ልቤ መረጋጋት አልቻለም፤ ላስብ ብሻም ራሴን መሰብሰብ ግን አልቻልኩም። ከራሴ ጋር ስወዛገብ ጊቢው ጭር አለ። እኔም ወደ ክፍል ሄድኩኝ፤ ብዙ አልፎኛል መሰለኝ አስተማሪው እያረመ ነበር። ስገባ አላየኝም... ሄጄ ተቀመጥኩ። ወደ ኃላ ስዞር ማሂን አየሁት፤ መልሼ ዞሬ ተቀመጥኩ። ራቢ ፈርታኝ ፊቷን አዙራ ተቀመጠች። የመውጫ ሰዐታችን ደርሶ እስክንለያይ ድረስ ምንም ሳንነጋገር ተለያየን።
.
.
ይቀጥላል...

www.tgoop.com/Habibacalligraphy



tgoop.com/Habibacalligraphy/1946
Create:
Last Update:

የባከኑ ቀናት
ክፍል ዘጠኝ
(ሂባ ሁዳ)
.
.
<<በቃ እደጠረጠርኩት... ይወድሻል..>> ራቢ ነበረች።
<<አንቺ ደግሞ ሁሌ መጠርጠር.. እንደዛ እንኳን አይሆንም ዝም ብለሽ ነው።>> ምንም ልትሰማኝ አልቻለችም።
<<አንቺ እኮ ቆየ ይወዳታል ማለት ከጀመርሽ፤ አይደለም ይሄ ተጨምሮ>> ዩሲ የቀረውን ምግብ እየጎረሰች።
<<እሺ ካላመናችሁኝ የባለፈው ብቻ እኮ በቂ ማረጋገጫ ነበር እኮ እእ ምን ልትሉ>> ሁለታችንም ተያይተን <<የቱ?>> አልናት ለማስታወስ..
<<ባለፈው የብሄር ብሄረሰቦች ቀን ጊቢ ውስጥ ሲከበር ማሂር ስልኩን ክፍል ውስጥ ቻርጅ ላይ አድርጎ <ማንም እንዳይነካው!> ብሎ ወጣ። ቻርጅ አስቸግሮት አናዶት ነበር... አቤላ ላይ ሁላ <ለምን ነካኸው> ብሎ ጓ! ብሎ ነበር። እሱ ሲወጣ ኢብቲ ገባች። ስልኩ የማሂ እንደሆነ ስታውቅ ጋላሪ ላይ ገብታ ስትመሰጥ የሆነ ሰው ሄዶ ለማሂር ነገረው። ከውጪ ሲገባ በዛ አካሄዱ ላየውሟ የሌለ ያስፈራ ነበር፤ በሩን እንዴት ብርግድ እንዳደረገው ኢብቲም ደንግጣ ስልኩን ለቀቀችው፤ ማሂር ሄዶ እነሣውና <አንቺ ነሽ እንዴ የነካሽው? ደግሞ ተይው ግላሱ ነው አልተጎዳም> ቢላትስ፤ ከኋላ የነበረው ተማሪ እኮ ከአሁን አሁን አጋጫት እያለ... ሃሃሃሃ... አጅሬው ኢብቲ መሆኗን ሲያውቅ ምንም እንዳልተፈጠር <ስጨርሺ ቻርጅ ላይ አድርጊው ካስቸገረሽ ደግሞ ጥሪኝ> ብሎ ላሽ ቢልስ። እኔ ደግሞ ለኢብቲ ያለውን ቦታ ማየት ቻልኳ! እእ ምን ልትሉ ነው?>>
<<እኔ ግን ምንም እንዳዛ አላስብም ራቢ። ምን አልባት ሌላ ነገር ይሆናል እኮ ማን ያውቃል ..>> ሃሳቧ የሚያሳምን ነገር አለው፤ ግን ለመከላከል ሞከርኩ።
<<እኔም ኢብቲ እንዳለችው ነው። ራቢ እኛ በዚህ እድሜያችን እንዴት ይሄን እናስባለን? ማይሆን ነገር እኮ ነው።
እንርሣው ባይሆን የቅድሙን ጥያቄዎች እንስራቸው ምን ትላላችሁ?>> ዩሲ ጉዳዩን ለማስቀር ተባበረችኝ።
<<ካላችሁ ምን ይደረጋል ግን እኔ ያልኩት እውነት መሆኑን በቅርቡ ታረጋግጣላችሁ ጠብቁ ብቻ <ራቢ ብለሽ ነበርሽ> ስትሉ መስማቴ የማይቀር ነው>>
<<አንቺ ደግሞ አንዴ ነገር ከጀመርሽ ቡኃላ አትፋቺም ዩሲ እንጀምር በቃ!!>> ነገሩን ዘጋሁት።
*
ያን ቀን ከትምህርት ቤት መልስ ጥያቄዎችን ሰርተን ከተለያየን በኃላ ዛሬ መገናኘታችን ነው። እንደተለመደው ክፍል ገብተን መማር ከጀመርን ሰዐታት አልፈዋል። ምሳ ሰዕት ላይ ዩሲ ማሂን እንዳወራው አስታወሰችኝና የተቀመጠበት ሄድኩኝ።
<<ሰላም ማሂሬ>> ለማውራት እንዲመቸኝ ከጎኑ እየተቀመጥኩ።
<<እእ እንዴት ነሽ?>>
<<አልሃምዱሊላህ አለሁልህ.. ምነው አሞሃል እንዴ?>> ፊቱ ልክ አለመሰለኝም።
<<ብታመምስ...ማንም ለማከም ፍቃደኛ ካልሆነ..>>
<<ማለት እንዴት?>>
<<ካልገባሽ አንድ ቀን ይገባሻል...>>
ምንም ማሂ አልመስልሽ አለኝ። ቢያንስ የቅዳሜውን ባወራው በዛው ወሬ መቀየሻ ይሆነኛል ብዬ አሰብኩ።
<<እኔ ምልህ ማሂ..>>ምን ብዬ እንደምጀምርለት ሃሳብ ስፈልግ።
<<ምን ነው ችግር አለ?>> ከአይኔ ላይ ፍርሃቴን ያነበበው መሰለኝ።
<<ሣይሆን... ቅዳሜ በጣም ቸኩዬ ስለነበረ ነው የሄድኩት እሺ ..>>
<<እሺ>> እሱ በግድ ፈገግ ለማለት ይሞክራል፤ እኔ ደግሞ እያባበልኩት መሰለኝ። ትንሽ ዝም ካልን በኃላ
<<እና አሁን ንገረኛ ምንድነው ማሂ ...>>
<<ኧረ.. አሁንስ ጊዜ አለሽ ማለት ነው?>>
<<ያኔ እኮ...>>አላስጨረሰኝም
<<ነገርሽኝ እኮ በቃ!>>
<<እህህህ ማሂ አሁን ንገረኝ እያልኩሃ>> ንግግራችን ወደ ጭቅጭቅ መስመር መቀየር ጀመረ።
<<ምን እንድነግርሽ ነው የምትፈልጊው?>> ድምፁ ላይ ቁጣ ታክሎበታል። <<ልትነግረኝ የነበረውን ነዋ ቀስ ለማለት እየሞከርኩ ...>>
<<ተውኩት በቃ!>>
<<እህህህ ማሂር አታድርቀኝ እንግዲ...>>
<<ሁሉም ነገር ላንቺ ቀልድ ነዋ የሚመስልሽ..ለማንኛውም ማርፈድ ከትምህርት ቤት ይልቅ ህይወት ላይ ዋጋ ያስከፍላል!>> ሲቃ በተሞላበት ድምፅ። <<አመሰግናለሁ>> ብሎኝ እየፈጠነ ወደ ውጪ ወጣ። እኔም ምንም መናገር አልቻልኩም ነበር እዛው ቁጭ አልኩ። <ያ ኢላሂ ምን ጉድ ነው? ኡፍፍፍ ኢብቲሣም ምንድነው ያደረግሽው.. ቲሽሽሽ> በራሴ ተናደድኩ። ያኔ ጥዬው ባልሄድ ይሄ ሁሉ አይፈጠርም ነበር። ምናለ ባዳመጥኩት... በራሴ ተናድጃለው፤ ከፍቶኛልም። እዛው ወንበሩ ላይ ድፍት ብዬ ባለቅስ ደስ ይለኝ ነበር።
*
<<ምንሼ እስካሁን እእ? ስሚ አታዝጊ ተነሺና ተናገሪ...>> አንገቴን ቀና አድርጋ እስክነግራት ትጠብቀኛለች፤ ራቢ።
<<ምንም አላለኝም>>
<<ሃሃሃሃ ኧረ ባኪ እስካሁን አብራቹ ስትጫወቱ ነበራ ታዲያ ማን አሸነፈ? ሃሃሃ>> ራቢ የሚያበሽቅ ሳቋን ለቀቀችው። ምንም መናገር ስላልፈለኩ ዝም አልኳት። እሷ ግን ምንም ልትረዳኝ አልቻለችም።
<<ኧረ ይሄ ነገር ምንድነው እእ? ሚስጥር ነው እንዴ እህቴ..>> አላስጨረስኳትም
<<ኡፍፍፍ አንቺ ደግሞ ችግር አለብሽ አትፋቺም! ዞር በይ በናትሽ .. >>
<<እህህ ኢብቲ በአላህ ምን ሁነሽ ነው?>> ድምጿ ይሰማኛል ላዳምጣት ግን አልፈለኩም።
<<ውዴ ወዴት ነው ጥድፊያው?>>ዩሲ ነበረች።
<<መጣሁ። እንዳትከተይኝ!>> ፈርታኝ <እሺ> ብላ እዛው ቀረች።ብቻዬን አንድ ጥግ ስር ቁጭ ብዬ ደቂቃዎች አለፉ። ልቤ መረጋጋት አልቻለም፤ ላስብ ብሻም ራሴን መሰብሰብ ግን አልቻልኩም። ከራሴ ጋር ስወዛገብ ጊቢው ጭር አለ። እኔም ወደ ክፍል ሄድኩኝ፤ ብዙ አልፎኛል መሰለኝ አስተማሪው እያረመ ነበር። ስገባ አላየኝም... ሄጄ ተቀመጥኩ። ወደ ኃላ ስዞር ማሂን አየሁት፤ መልሼ ዞሬ ተቀመጥኩ። ራቢ ፈርታኝ ፊቷን አዙራ ተቀመጠች። የመውጫ ሰዐታችን ደርሶ እስክንለያይ ድረስ ምንም ሳንነጋገር ተለያየን።
.
.
ይቀጥላል...

www.tgoop.com/Habibacalligraphy

BY Habiba Calligraphy




Share with your friend now:
tgoop.com/Habibacalligraphy/1946

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

Deputy District Judge Peter Hui sentenced computer technician Ng Man-ho on Thursday, a month after the 27-year-old, who ran a Telegram group called SUCK Channel, was found guilty of seven charges of conspiring to incite others to commit illegal acts during the 2019 extradition bill protests and subsequent months. How to create a business channel on Telegram? (Tutorial) With Bitcoin down 30% in the past week, some crypto traders have taken to Telegram to “voice” their feelings. Healing through screaming therapy Telegram users themselves will be able to flag and report potentially false content.
from us


Telegram Habiba Calligraphy
FROM American