HABIBACALLIGRAPHY Telegram 1947
የባከኑ ቀናት
ክፍል አስር
(ሂባ ሁዳ)
.
.
የስምንተኛ ክፍል የብሔራዊ ፈተና መፈተኛ ጊዜ ደርሰ፤ እንደ አጋጣሚ ረመዳንም አብሮ ገባ። የፈተናችን ቀን የጀመረው በረመዳን የመጀመሪያ ቀን ነበር።
.
የጠዋቱን ከተፈተንን በኃላ ለዙሁር ሰላት ወደ መስጂድ አመራን፤ ድባቡ ልዩ ነበር። ግማሹ ጥግ ጥግ ይዞ ቁርዐኑን ይቀራል ሌላው ደግሞ ሱና ሰላቶችን ይሰግዳል። ሰግደን ወደ ምንፈተንበት ትምህርት ቤት አመራን መንገድ ላይ እነ አቤላን አግኝተን ስንተራረብ ት/ቤት ደረስን። ከማሂ ጋር እንደበፊቱ ባይሆንም እናወራለን። እሱ በጣም ሊቀርበኝ ቢፈልግም እኔ ግን ከላይ ከላይ ነው የማወራው፤ በአገኘሁት ጊዜ ያኔ እያውራሁት ጥሎኝ የሄደው ቀድሞ ይታወሰኛል። እስካሁን ተናድጄበታለሁ፤ እሱ ግን ረስቶት መሰለኝ ኩርፊያውን ትቶ ምንም እንዳልተፈጠረ ያወራኛል።
የመጀመሪያ ቀን ፈተናችንን ደስ በሚል ሁኔታ አጠናቀቅን። ብዙዎች ቀላል ነው ብለዋል፤ አቤላ ከዘጠና በላይ አመጣለው ብሎ ይፎክራል። ከእኔ ጋር አንድ ክፍል ውስጥ ነው የምንፈተነው ሙሉ መልሳችን አንድ አይነት ሣይሆን አይቀርም። ማሂ፣ ዩሲና ራቢ ግን ሌላ ሌላ ክፍል ነው የሚፈተኑት።
ከምንፈተንበት ትምህርት ቤት እስከምንማርበት ትምህርት ቤት ርቀት ቢኖረውም እያወራን ስለነበረ ሳይታወቀን ደረስን። ሁሉም በየአቅጣጫው ተበታተነ እኛም ስለ ነገው ፈተና እያወራን ሰፈራችን ስንደርስ ተለያየን።
*
ዛሬ ፈተናው ትንሽ ከበድ ይል ነበር፤ ግን እንደምንም የጠዋቱን ጨርሰን ወጣን። ከአቤላ ጋር ውጪ ላይ ቁጭ ብለን ስንዛዛግ ማሂና ባቢ መጥተው ተቀላቀሉን። ፈተናውን ስላልሰሩ ተናደዋል።
<<እና ፈተና እንዴት ነበር?>> እንዳገኘኋቸው ያቀረብኩት ጥያቄ ነበር።
<<አቦ ተይን ቀናችን አይደለም የሆነ ገገማ ፈታኝ ነበር ምንም አላሰራንም>> ባቢ ብስጭት ብሎ መለሰ።
<<ማሂ አንተስ አልሰራህም?>>
<<ባክሽ ከኃላ ላሉት አስኮረጅክ ብሎኝ ቀማኝ ያውም ሣልጨርስ በቃ>>
<<የከሰዐቱን ትሰራላችሁ። እእ.. አይዟችሁ እሺ...>> ሁለቱም አሳዘኑኝ አቤላም እነሱ ስላልሰሩ ደበረው።
<<አቦ በቃ እዚው ዱቅ እንበል ሙዳችን ተከንቶማ ወዴት እንቀየሳለን>> አቤላ ከአንዱ ዛፍ ስር ሲቀመጥ አብረውት ቁጭ አሉ።
<<ኢብቲ ነያ ተቀመጪ>> ባቢ እንድቀመጥ ተጠጋልኝ።
<<ኧረ መስጂድ ልሄድ ነው ባቢ..>>
<<እንዴ ምን ልትሰሪ?>> ማሂ በመገረም እያየኝ።
<<ሃሃሃ አንተ ደግሞ ልጫወት ልበልህ..>> አጠያየቁ ገርሞኝ እያየሁት።
<<ጀለሶችሽ መጡ>> አቤላ ወደነ ዩሲ እየጠቆመኝ። <<ደግሞ እዳትቆዪ አብረን እንገባለን>>
<<እሺ በቃ ቻው..>> ተሰነባብተናቸው ተለያየን።
*
ከነ ዩሲ ጋር መስጂድ ደርሰን ተመለስን። የመጨረሻውን ፈተና ለመፈተን ሁሉም ጓጉቷል መፈተኛ ጊቢ ጋር ስንደርስ ተማሪው ጢቅ ብሏል። ጭራሽ የሚገባው በፍተሻ ነው፤ ሰልፉ ደግሞ ረዘም ያለ ነበር። መጨረሻ ላይ እኛ ነበርን አቤላ መጥቶ ጠራኝና ከፊት ሊያስገበኝ እነባቢ ወደ ተሰለፉበት መሄድ ጀመርን።
<<እኔ ምልሽ ኢብቲ>>
<<ወዬ አቤላ>>
<<ከዛሬ በኃላ በቃ አንገናኝም ማለት ነው?>>
<<ኧረ ለምን? ውጤት ሲወጣ እንገናኛለን እኮ..>>
<<እስከዛስ አንቺም ጀለሶችሽም ስልክ የላችሁ ..ከነ ማሂ ጋ እኮ እያወራን ነበር እሱም ደብሮታል ልንለያይ መሆኑ...>>
<<እህ አቤላ...ዘጠኝም አብረን እንመዘገባለን አያሣስብም ኮ....>>
<<እሱማ አዎ ግን ያው...>> የምናወራውን ሳንጨርስ እነ ባቢ ጋ ደረስን << እነዚያው እነባቢ.. ነይ በዚህ ጋ>> ባቢ የሃይላንድ ሚሪንዳ እየጠጣ ነበር። አቤላን ሲያየው ለማሂ አቀበለው።
<<ኧረ አልሰማቹም ብትጨርሱት>> አቤላ ፈጠን ብሎ ወደ ማሂ ሲንደረደር፤ ማሂ ለአቤላ ወይስ ለባቢ ሊያዳላ ነው ብዬ የሚሆነው ስጠብቅ... ያላስብኩት ነገር ተፈጠረ።
<<እንዴ ማሂ!!>> ሚሪንዳውን የሚጠጣውን ማሂን አይቼ ከድንጋጤ ጋር ስጮህ ሶስቱም ወደኔ ዞሩ። መደንገጤን ሲያዩ መጨቃጨቃቸውን አቆሙና ማሂ ላይ አፈጠጡበት። ማሂ ግራ ገብቶት <<እእ ምን ሁነሽ ነው አስደነገጥሽኝ እኮ>> የተደፋበትን ሚሪንዳ እየጠራረገ ከኔ ምላሽ ይጠብቃል።
<<እህ በረመዳኑ ትጠጣለህ እንዴ! ፆመኛ ነሃ ረስተኸው ነዋ...>> አይን አይኑን ሳየው አንገቱን ደፋ። እነ አቤላ ዝም ብለው ፊት ፊታችንን ያዩናል።
<<እናንተ ልጁን አሳሳታቹታ...ሃሃሃሃ ቀልበ_ቢስ ሁላ። ማሂ በል ተጉመጥመጥ>> ማሂ ካቀረቀረበት ሲነሳ አይኑ በእምባ ተሞልቶ ነበር።
<<እህ ማሂ ምን ሆነህ ነው?>> ጥያቄን ሳይመልስ ከመሮጥ ባልተናነሰ መልኩ ከአጠገቤ ራቅ ብሎ ሄደ።
<<ምንድነው ባቢ ንገረኝ?>> ግራ እብደገባኝ በሚያሳብቅ አስተያየት።
<<ኧረ ምንም አላውቅም..>> ፊቱን አዞሮ መለሰልኝ።
<<አቦ ተናገር በናትህ ምንም እየገባኝ አይደለም ችግር አለ እንዴ? ማሂ ለምንድነው እንዲህ የሚሆነው?>>
<<እሺ ለሱ አትናገሪውም እእ ብንግርሽ? ማይልኝ..>>
<<ኡፍ ባቢ አዎ ተናገር...>> እስክሰማው ጓጓቻለው። ምን ይሁን? ማሂ ምንድነው ያልነገረኝ? ለምንስ ይፈራኛል? የራሴ ጥያቄ ነው።
<<ምን መሰለሽ ኢብቲ...>> ባቢ ንግግሩን እንዲቀጥል በጭንቅላቴ ምልክት ሰጠሁት።
<<ማሂር እንዳንቺ አይደለም>>
<<ማለት?>> ምንም ለማለት እንደፈለገ
አልገባኝም።
<<ስልሽ አለ አይደል... ምንም አያውቅም>>
<<ባቢ በግልፅ ንገረኝ። እሱ ህጻን አይደለም እኮ ምንድነው የማያውቀው?>>
<<ማሂሮ ኮ አይሰግድም፣ አይፆምም በቃ ስለ እምነታቹ ምንም አያርፍም... እንዳንቺ ቁርዐን ቤት ምንናምን እሱ ጋ ወፍ የለም! አላ በቃ ማወቅ ይፈልጋል፤ ግን ደግሞ የሚረዳው ሰው አላገኘም። አንቺ ደግሞ በጣም ጎበዝ ነሽ እኔ ከማውቃቸው.. እሱም ደግሞ ለዛ ነው አንቺን መቅረብ የሚፈልገው። ብዙ እንደምትረጂውና እንደምትለውጪው አምኖ ነበር። ግን አንቺ ልታዳምጭው አልፈለግሽም፤ ስለሱ እኮ ምንም አታውቂም። ሊነግርሽ ቢፈልግም መንገዱን ትዘጊበታለሽ፤ በፊት ሙስሊም ጀለሶች ነበሩን እነሱ ከማሳወቅ ይልቅ ሙድ መያዣ አደረጉት። ለምን? ባለማወቁ ምክንያት! ምንአልባት አንቺ ታስተካኪዋለሽ ብለን ነበር፤ ግን ምን ያረጋል...በቃ ምንም ነው ልትረጂው ያልቻልሽው... ኢብቲ እንደነገርኩሽ ካወቀ ያልቅልኛል። የነገርኩሽም አንቺም ሳታውቂ እንዳሁኑ በሞራሉ ከምትጫወጪበትና እሱም ባንቺ ቅስሙ ከሚሰበር ብዬ ነው። በቃ ሁሉንም ባላየ እለፊው አታስጨንቂው፤ በናትሽ አሁንም በቃ እያለቀሰ ነው የሚሆነው እስቲ ልየው...>> ባቢ ከአይኔ እስኪጠፋ በሄደበት መስመር ፈዝዤ ቀረሁ። ምንድነው የሆነው? እኔስ ምንድነው ያደረኩት? ምንድነው የሰማሁት? ሁሉም ድንግርግር አለብኝ። ጭራሽ ያልጠበቁት ነገር በአንዴ መዐት የወረደብኝ ያህል ከበደኝ። ከየት መጣ ያላልኩት እምባ ሂጃቤ ድረስ አበስብሶኛል። መሬትና ሰማዩ እየተሽከረከረ መሰለኝ፤ አይኔ ብዥዥዥዥ አለብኝ። ምን ያህል ደቂቃ እዛው እንደነበርኩ አላውቅም ብቻ አቤላ መጥቶ ፊቴን እንዳስታጠበኝ ትዝ ይለኛል። ከዛም መፈተኛ ክፍል ውስጥ ምን ሁና ነው ብለው ሲጠይቁትም ይሰማኝ ነበር። አጠገቤ ቁጭ ብሎ አይዞሽ ምናምንም ሲለኝም ነበር።



tgoop.com/Habibacalligraphy/1947
Create:
Last Update:

የባከኑ ቀናት
ክፍል አስር
(ሂባ ሁዳ)
.
.
የስምንተኛ ክፍል የብሔራዊ ፈተና መፈተኛ ጊዜ ደርሰ፤ እንደ አጋጣሚ ረመዳንም አብሮ ገባ። የፈተናችን ቀን የጀመረው በረመዳን የመጀመሪያ ቀን ነበር።
.
የጠዋቱን ከተፈተንን በኃላ ለዙሁር ሰላት ወደ መስጂድ አመራን፤ ድባቡ ልዩ ነበር። ግማሹ ጥግ ጥግ ይዞ ቁርዐኑን ይቀራል ሌላው ደግሞ ሱና ሰላቶችን ይሰግዳል። ሰግደን ወደ ምንፈተንበት ትምህርት ቤት አመራን መንገድ ላይ እነ አቤላን አግኝተን ስንተራረብ ት/ቤት ደረስን። ከማሂ ጋር እንደበፊቱ ባይሆንም እናወራለን። እሱ በጣም ሊቀርበኝ ቢፈልግም እኔ ግን ከላይ ከላይ ነው የማወራው፤ በአገኘሁት ጊዜ ያኔ እያውራሁት ጥሎኝ የሄደው ቀድሞ ይታወሰኛል። እስካሁን ተናድጄበታለሁ፤ እሱ ግን ረስቶት መሰለኝ ኩርፊያውን ትቶ ምንም እንዳልተፈጠረ ያወራኛል።
የመጀመሪያ ቀን ፈተናችንን ደስ በሚል ሁኔታ አጠናቀቅን። ብዙዎች ቀላል ነው ብለዋል፤ አቤላ ከዘጠና በላይ አመጣለው ብሎ ይፎክራል። ከእኔ ጋር አንድ ክፍል ውስጥ ነው የምንፈተነው ሙሉ መልሳችን አንድ አይነት ሣይሆን አይቀርም። ማሂ፣ ዩሲና ራቢ ግን ሌላ ሌላ ክፍል ነው የሚፈተኑት።
ከምንፈተንበት ትምህርት ቤት እስከምንማርበት ትምህርት ቤት ርቀት ቢኖረውም እያወራን ስለነበረ ሳይታወቀን ደረስን። ሁሉም በየአቅጣጫው ተበታተነ እኛም ስለ ነገው ፈተና እያወራን ሰፈራችን ስንደርስ ተለያየን።
*
ዛሬ ፈተናው ትንሽ ከበድ ይል ነበር፤ ግን እንደምንም የጠዋቱን ጨርሰን ወጣን። ከአቤላ ጋር ውጪ ላይ ቁጭ ብለን ስንዛዛግ ማሂና ባቢ መጥተው ተቀላቀሉን። ፈተናውን ስላልሰሩ ተናደዋል።
<<እና ፈተና እንዴት ነበር?>> እንዳገኘኋቸው ያቀረብኩት ጥያቄ ነበር።
<<አቦ ተይን ቀናችን አይደለም የሆነ ገገማ ፈታኝ ነበር ምንም አላሰራንም>> ባቢ ብስጭት ብሎ መለሰ።
<<ማሂ አንተስ አልሰራህም?>>
<<ባክሽ ከኃላ ላሉት አስኮረጅክ ብሎኝ ቀማኝ ያውም ሣልጨርስ በቃ>>
<<የከሰዐቱን ትሰራላችሁ። እእ.. አይዟችሁ እሺ...>> ሁለቱም አሳዘኑኝ አቤላም እነሱ ስላልሰሩ ደበረው።
<<አቦ በቃ እዚው ዱቅ እንበል ሙዳችን ተከንቶማ ወዴት እንቀየሳለን>> አቤላ ከአንዱ ዛፍ ስር ሲቀመጥ አብረውት ቁጭ አሉ።
<<ኢብቲ ነያ ተቀመጪ>> ባቢ እንድቀመጥ ተጠጋልኝ።
<<ኧረ መስጂድ ልሄድ ነው ባቢ..>>
<<እንዴ ምን ልትሰሪ?>> ማሂ በመገረም እያየኝ።
<<ሃሃሃ አንተ ደግሞ ልጫወት ልበልህ..>> አጠያየቁ ገርሞኝ እያየሁት።
<<ጀለሶችሽ መጡ>> አቤላ ወደነ ዩሲ እየጠቆመኝ። <<ደግሞ እዳትቆዪ አብረን እንገባለን>>
<<እሺ በቃ ቻው..>> ተሰነባብተናቸው ተለያየን።
*
ከነ ዩሲ ጋር መስጂድ ደርሰን ተመለስን። የመጨረሻውን ፈተና ለመፈተን ሁሉም ጓጉቷል መፈተኛ ጊቢ ጋር ስንደርስ ተማሪው ጢቅ ብሏል። ጭራሽ የሚገባው በፍተሻ ነው፤ ሰልፉ ደግሞ ረዘም ያለ ነበር። መጨረሻ ላይ እኛ ነበርን አቤላ መጥቶ ጠራኝና ከፊት ሊያስገበኝ እነባቢ ወደ ተሰለፉበት መሄድ ጀመርን።
<<እኔ ምልሽ ኢብቲ>>
<<ወዬ አቤላ>>
<<ከዛሬ በኃላ በቃ አንገናኝም ማለት ነው?>>
<<ኧረ ለምን? ውጤት ሲወጣ እንገናኛለን እኮ..>>
<<እስከዛስ አንቺም ጀለሶችሽም ስልክ የላችሁ ..ከነ ማሂ ጋ እኮ እያወራን ነበር እሱም ደብሮታል ልንለያይ መሆኑ...>>
<<እህ አቤላ...ዘጠኝም አብረን እንመዘገባለን አያሣስብም ኮ....>>
<<እሱማ አዎ ግን ያው...>> የምናወራውን ሳንጨርስ እነ ባቢ ጋ ደረስን << እነዚያው እነባቢ.. ነይ በዚህ ጋ>> ባቢ የሃይላንድ ሚሪንዳ እየጠጣ ነበር። አቤላን ሲያየው ለማሂ አቀበለው።
<<ኧረ አልሰማቹም ብትጨርሱት>> አቤላ ፈጠን ብሎ ወደ ማሂ ሲንደረደር፤ ማሂ ለአቤላ ወይስ ለባቢ ሊያዳላ ነው ብዬ የሚሆነው ስጠብቅ... ያላስብኩት ነገር ተፈጠረ።
<<እንዴ ማሂ!!>> ሚሪንዳውን የሚጠጣውን ማሂን አይቼ ከድንጋጤ ጋር ስጮህ ሶስቱም ወደኔ ዞሩ። መደንገጤን ሲያዩ መጨቃጨቃቸውን አቆሙና ማሂ ላይ አፈጠጡበት። ማሂ ግራ ገብቶት <<እእ ምን ሁነሽ ነው አስደነገጥሽኝ እኮ>> የተደፋበትን ሚሪንዳ እየጠራረገ ከኔ ምላሽ ይጠብቃል።
<<እህ በረመዳኑ ትጠጣለህ እንዴ! ፆመኛ ነሃ ረስተኸው ነዋ...>> አይን አይኑን ሳየው አንገቱን ደፋ። እነ አቤላ ዝም ብለው ፊት ፊታችንን ያዩናል።
<<እናንተ ልጁን አሳሳታቹታ...ሃሃሃሃ ቀልበ_ቢስ ሁላ። ማሂ በል ተጉመጥመጥ>> ማሂ ካቀረቀረበት ሲነሳ አይኑ በእምባ ተሞልቶ ነበር።
<<እህ ማሂ ምን ሆነህ ነው?>> ጥያቄን ሳይመልስ ከመሮጥ ባልተናነሰ መልኩ ከአጠገቤ ራቅ ብሎ ሄደ።
<<ምንድነው ባቢ ንገረኝ?>> ግራ እብደገባኝ በሚያሳብቅ አስተያየት።
<<ኧረ ምንም አላውቅም..>> ፊቱን አዞሮ መለሰልኝ።
<<አቦ ተናገር በናትህ ምንም እየገባኝ አይደለም ችግር አለ እንዴ? ማሂ ለምንድነው እንዲህ የሚሆነው?>>
<<እሺ ለሱ አትናገሪውም እእ ብንግርሽ? ማይልኝ..>>
<<ኡፍ ባቢ አዎ ተናገር...>> እስክሰማው ጓጓቻለው። ምን ይሁን? ማሂ ምንድነው ያልነገረኝ? ለምንስ ይፈራኛል? የራሴ ጥያቄ ነው።
<<ምን መሰለሽ ኢብቲ...>> ባቢ ንግግሩን እንዲቀጥል በጭንቅላቴ ምልክት ሰጠሁት።
<<ማሂር እንዳንቺ አይደለም>>
<<ማለት?>> ምንም ለማለት እንደፈለገ
አልገባኝም።
<<ስልሽ አለ አይደል... ምንም አያውቅም>>
<<ባቢ በግልፅ ንገረኝ። እሱ ህጻን አይደለም እኮ ምንድነው የማያውቀው?>>
<<ማሂሮ ኮ አይሰግድም፣ አይፆምም በቃ ስለ እምነታቹ ምንም አያርፍም... እንዳንቺ ቁርዐን ቤት ምንናምን እሱ ጋ ወፍ የለም! አላ በቃ ማወቅ ይፈልጋል፤ ግን ደግሞ የሚረዳው ሰው አላገኘም። አንቺ ደግሞ በጣም ጎበዝ ነሽ እኔ ከማውቃቸው.. እሱም ደግሞ ለዛ ነው አንቺን መቅረብ የሚፈልገው። ብዙ እንደምትረጂውና እንደምትለውጪው አምኖ ነበር። ግን አንቺ ልታዳምጭው አልፈለግሽም፤ ስለሱ እኮ ምንም አታውቂም። ሊነግርሽ ቢፈልግም መንገዱን ትዘጊበታለሽ፤ በፊት ሙስሊም ጀለሶች ነበሩን እነሱ ከማሳወቅ ይልቅ ሙድ መያዣ አደረጉት። ለምን? ባለማወቁ ምክንያት! ምንአልባት አንቺ ታስተካኪዋለሽ ብለን ነበር፤ ግን ምን ያረጋል...በቃ ምንም ነው ልትረጂው ያልቻልሽው... ኢብቲ እንደነገርኩሽ ካወቀ ያልቅልኛል። የነገርኩሽም አንቺም ሳታውቂ እንዳሁኑ በሞራሉ ከምትጫወጪበትና እሱም ባንቺ ቅስሙ ከሚሰበር ብዬ ነው። በቃ ሁሉንም ባላየ እለፊው አታስጨንቂው፤ በናትሽ አሁንም በቃ እያለቀሰ ነው የሚሆነው እስቲ ልየው...>> ባቢ ከአይኔ እስኪጠፋ በሄደበት መስመር ፈዝዤ ቀረሁ። ምንድነው የሆነው? እኔስ ምንድነው ያደረኩት? ምንድነው የሰማሁት? ሁሉም ድንግርግር አለብኝ። ጭራሽ ያልጠበቁት ነገር በአንዴ መዐት የወረደብኝ ያህል ከበደኝ። ከየት መጣ ያላልኩት እምባ ሂጃቤ ድረስ አበስብሶኛል። መሬትና ሰማዩ እየተሽከረከረ መሰለኝ፤ አይኔ ብዥዥዥዥ አለብኝ። ምን ያህል ደቂቃ እዛው እንደነበርኩ አላውቅም ብቻ አቤላ መጥቶ ፊቴን እንዳስታጠበኝ ትዝ ይለኛል። ከዛም መፈተኛ ክፍል ውስጥ ምን ሁና ነው ብለው ሲጠይቁትም ይሰማኝ ነበር። አጠገቤ ቁጭ ብሎ አይዞሽ ምናምንም ሲለኝም ነበር።

BY Habiba Calligraphy


Share with your friend now:
tgoop.com/Habibacalligraphy/1947

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

Step-by-step tutorial on desktop: Invite up to 200 users from your contacts to join your channel To upload a logo, click the Menu icon and select “Manage Channel.” In a new window, hit the Camera icon. 5Telegram Channel avatar size/dimensions Users are more open to new information on workdays rather than weekends.
from us


Telegram Habiba Calligraphy
FROM American