tgoop.com/Habibacalligraphy/1948
Last Update:
ከደቂቃዎች በኃላ ተረጋጋሁ፤ ወደራሴ ስመለስ የማጠቁርበት እርሳሴን መፈለግ ጀመርኩ።
.
<<አቦ አስቦክተሺኝ ነበር እኮ...ሆ... ወይ አትናገሪ ወይ ነቃ አትዪ.. በስማም የሌለ ክብድ ብሎኝ ነበር ኮ። ባለቀ ሰዐት ጉድ ልንሆን? ዘጠና ብዬ ስጎርር ዘጭ ልታስብዪኝ!? ፈጣሪ ሆይ ተመስገን>> ብሎ ብርክክ ሲል ክላሱ ሁላ በሳቅ አጥለቀለቀው።
<<ሃሃሃ...አንተ በቃ ፈታ አልክብኛ? ኧረ ግን አቤላ ተቀየምኩህ>> እንደማኩረፍ ብዬ እያየሁት።
<<ማሪያምን ኢብቲዬ ጭንቅ ብሎኝ ነበር.. >>
<<ኧረ ፈታኙ መጣ>>
<<ስድስት ስድስት>> ሲል ሁሉም ተስተካክሎ ቁጭ አለ፥ ፈታኙ።
*
<<የዛሬው ደግሞ ከስከዛሬው ሁሉ ቀላል ነበር ደስ ሲል አ አቤላ? ደግሞ በጣም ቀላል..>> ከመፈተኛ ክፍል ወደ ውጪ እየወጣን።
<<ኧረ ምን አውቄ.. ቀለሜዋ አንቺ ..ብቻ ላጥ ላጥ ስታረጊው እኔም ከስር ከስርሽ ኮፒ አደረኩልሽ>> ደስ እንዳለው ከፊቱ ላይ ይነበባል።
<<ደግሞ ማንም አልወጣም እኮ... አባቴ.. ቸኮልን መሰለኝ>> ዞር ዞር ስንል ከሁለታችን ውጪ ማንም አልነበረም።
<<እና የዛሬው ፈተና ኮ ያንቺ ስለሆነ ነው። ቲቸር ራሱ ባይሎጂን ከኢብቲሳም ገልብጡ አልነበር ያለው? አንቺና ባይሎጂ ኮ በቃ ቤተሰብ ሆናችሁዋል።>>
<<ሃሃ አንተ ደግሞ አታመሳስል እኮ.. ስማማ... ማሂ ና ባቢ ሰርተው ይሆን?>>
<<ኧረ እንጃ በናትሽ፤ ካልሰሩ የመጭ ነው ሚደብረኝ... ደግሞ ማሂሮ ሲገባ ከፍቶት ስለነበረ ተረጋግቶ የሚሰራም አይመስለኝም።>> እንዲሁ እየተነጋገርን የተወሰኑ ተማሪዎች ብቅ ብቅ ማለት ጀመሩ። ከተማሪው መሃል ባቢ ወደኛ መጣ።
<<እእ እንዴት ነበር ተሰራ?>> አቤላ አይን አይኑን እያየ ይጥይቃል።
<<ባክህ ያው ነው ትንሽ ነው የሰራሁት..>>
<<እና ብራዘርስ እየሰራ ነው..?>>
<<ማ? ማሂሮ? እሱኮ ሄደ>>
<<ወዴት?>> ሁላታችንም ሳናስበው ጮክ ማለታችን አስደንግጦት
<<እህህ... ቀስ በሉ፤ እቸኩላለው ብሎ ላጥ አለ። ምንም አላናግር ብሎኝ ሄደ ወዲያው እንደወጣን...>>
<<በቃ ቻው እሺ>> ብዬ እኔም ትቻቸው ሄድኩ። አቤላ ቢጠራኝም እየፈጠንኩ በሌላ አቅጣጫ ሄድኩ። እነዩሲ ሲመጡ በነኢክሩ ሰፈር አድርገን ሄድን፤ ሁላችንም ደብሮናል። እንደ ሌላው ቀን ፈታ ብለን ማውራት አልቻልም። ያው ትምህርት ከተዘጋ ሁሌ ስለማንገናኝ አብረን ስለ ማንውል እንጂ መድረሳ ለአጭር ሰዐት እንገናኛለን፤ ግን እንደ ልብ የምናወራበት ሰዐት አናገኝም። እሱን እያስብን ለመለያየት በቆምንበት መንገድ ላይ ብዙ ከቆየን በኋላ እንደምንም ተቃቅፈን ተለያየን። እኔና ዩስ እሰከ ሰፈር አንድ ላይ ብንጓዝም በሃሳብ ግን ሁለታችንም ለየብቻ ነበርን።
.
.
ይቀጥላል...
www.tgoop.com/Habibacalligraphy
BY Habiba Calligraphy
![](https://photo2.tgoop.com/u/cdn4.cdn-telegram.org/file/uaIMNMHTH0WpwzooUkSBQxNSl-iNboeevZojLGdsnsbyiwMV1AXG6ZpLiM8u_wtDhys75OdXEQoymv-UADQj47TdgMDco468S1izi7DgwsF9mMQ0Rz2sv_PyH8UAQ-TNWmzcHJWHjMXeBoTri8wqocVuIRxEajtRx3AnrltkHv8fuXTxAujIi1Gltz4-R9JdBV3wtohHYBODOayXpkXpE8N4BHHFE-yhF1Tyi-O372tq0AYi4lvVDQjPjYhx5GMx7TCkOnvwNxlNJYRvvTX8eXh1JmNYUSrJuGFKwn4ROPlU7RYj3P2yu3hGHjZi7EBvkwHuhK4NXHA7n_lTmxHliw.jpg)
Share with your friend now:
tgoop.com/Habibacalligraphy/1948