HABIBACALLIGRAPHY Telegram 1951
የባከኑ ቀናት
ክፍል አስራ አንድ
(ሂባ ሁዳ)
.
.
እነ ዩሲ በር ጋር ደርሰን ሁለታችንም ቆምን። እኔ ዝም ብያት ወደ ቤታቸው ስገባ ተከተለችኝ፤ ሳሎን በግማሽ በኩል በተነጠፈው መጅሊስ ላይ ዘፍ አልኩ። ዩስሪ ከደቂቃዎች ቡኃላ ልብሷን ቀያይራ አጠገቤ ቁጭ አለች፤ ዝም ብላ እኔ እስክነግራት ትጠብቃለች። ሁሌም በከፋኝ ሰዐት እነሱ ቤት ሄጄ ነው የሚወጣልኝ... ሁሉንም ዝርግፍግፍ አድርጌ እነግራታለሁ። ከኔ በላይ እሷ ትጨነቃለች፤ ዛሬ ግን ዝምታዬ በዛባት መሰለኝ ለማውራት ተገደደች።
<<ኢብቲዬ ሀቢብቲ ምንድነው የሆንሽው? ቅድም ጀምረሽ ልክ እንዳነበርሽ እኮ አውቃለሁ፤ ብቻችንን ስንሆን እናወራለን ብዬ ነው ዝም ያልኩት>> ምንም ሳልመልስላት ስቀር አላስቻላትም ድጋሚ ሌላ ቃላት ሰነ ዘረች... <<ማሂ ነው አይደል? እንዲ ያስከፋሽ.. እእ ኢብቲ ምን እንደተፈጠረ ንገሪኝ በአላህ እያስጨነቅሽኝ ነው>>
<<ዩሲ እሱኮ ምንም አላደረገም እኔ ነኝ እንጂ የጎዳሁት። ልቡን ስብርብር ነው ኮ ያደረኩት ምን አይነት ልጅ ነኝ!? አመት ሙሉ አጠገቤ ከችግሩ ጋር ሲታገል የነበረን ሰው እንዴት እገፋዋለሁ?...ዩሲ ንገሪኝ እስቲ ምን አይነት ግዴለሽ ሰው እንደሆንኩ..>> በመሃል ትንፋሼ መቆራረጥ ጀመረ፤ ከዚህ በላይ ማውራት አልቻልኩም። ዩሲ አቅፍኝ ማልቀስ ስትጀምር ይባሱኑ ስቅስቅ ብዬ አለቀስኩ። ሰዐቱ ወደ መምሸት ሲጠጋጋ ፊቴን ታጥቤ ወደ ቤት ገባሁ። ወንድሜ ፈተና ያልሰራሁ መስሎት ቢጨነቅም ትንሽ እንደደከመኝ ተናግሬ ከኢፍጣር ቡኃላ ወደ መኝታዬ ሄጄ ከራሴ ጋር ብዙ ተጨቃጨቅኩ። ከረጅም የድካም ሰዐታት በኃላ እንቅልፍ አሸለበኝ።
*
*
ከሁለት ወራት ቡኃላ የሚንስትሪ ውጤት ለመቀበል ትምህርት ቤት ተሰብስበናል። ከረጅም ጊዜ የናፍቆት ወሬ በኃላ ተማሪዎቹ ውጤት ለመቀበል ተሰለፉ፤ እኛ መጨረሻ ላይ እንቀበላለን ብለን ጥግ ላይ ቁጭ አልን። እነ አቤላ ተሰልፈዋል እሱ ዘጠና አመጣለሁ ብሎ አሲዟል፤ ባቢም ከኃላው ነበረ፤ ማሂን ግን አላየሁትም። ዛሬ ደግሞ በጣም እፈልገዋለሁ... ብዙ ነገር ላወራው ተዘጋጅቼበት ነው የመጣሁት፤ በዛ ላይ ናፍቆኛል። ባቢ ጋር ሄጄ ስጠይቀው እንደማይመጣ ነገረኝ። ለምን ምናምን ሣልል ቀጥ ብዬ ስሄድ ከኃላ ሂጃቤ ሲጎተት ለማስለቀቅ ዞር ስል በአየሁት ነገር ድንግጥ አልኩኝ <<ኢብቲዬ>> ብሎ እጁን ሲዘረጋ እንዴት እንደሆነ ባላውቅም ስጠጋው እቅፍ አደረገኝ፤ ምናልባት መተቃቀፋችን የመጀመሪያም የመጨረሻም መሰለኝ... ትንሽ እንደቆየን ድንግጥ ብዬ ከእቅፉ ወጣሁ።
<<እእ ይቅርታ ሳላስበው ነው...>> እንደመሳቀቅ ሲል አሳዘነኝ።
<<ኧረ ችግር የለውም ማሂ ...>>
<<እና ደህና ነሽ? እንዴት ነሽ ተጠፍፋን ኣ?>>
<<አለሁ አልሃምዱሊላህ አንተ እንዴት ነህ እእ ሁሉ ሰላም ነው?>>
<<አዎ ሰላም ነው። ደግሞ ረፍቱ ተስማምቶሻል እእ አምሮብሻል..>>
<<ሙድ አትያዝብኛ አንተ ነህ ያማረብህ እኮ...>>
<<ሃሃሃ ኧረ ባክሽ... ስገባ እኮ ሳይሽ ወዳንቺው መጣሁ፤ ጀለሶችን አላገኘዃቸውም ከመጣሽ ቆየሽ እንዴ?>>
<<ኧረ እዛ ጋር ተሰልፈዋል። አንተን ፈልጌ እኮ ባቢ አይመጣም ሲለኝ ወደዚህ ስመጣ ነው ያገኘሁህ አላወቁም መሰለኝ
እንደምትመጣ...>>
<<ኧረ ያውቃል ሊያዝግሽ ፈልጎ ነው ይሄ ዱዝ..እና ፈልገሽኝ ነው እእ?>> ፊቱ ላይ ፈገግታ ሞላ ሞላ ብሏል።
<<አዋ! ማሂ እፈልግሃለው ..እንዲ ቁመን አይደለም በቃ እንጨርስና እናወራለን።>>
<<ኧረ ደስ ይለኛል..በቃ እነ ባቢ ጋ ልሂድ እስኪ ..>> ፈጠን እያለ ወደ ተሰለፉት ልጆች አመራ። እሱ ወዳዛ ሲሄድ እነኢክሩ ወደኔ መጡ። ኢክራም ቸኩላ ሰለነበረ ካልተቀበልኩ ብላ ሄድን፤ እኔ ግን ፈራሁ። ውጪ ላይ ቆሜ እነሱ ገቡና እየሳቁ ወጡ እንደምታልፍ እርግጠኛ ነበርኩና ጥምጥም አልኩባት፤ ወዲያው ሸኝተናት ተመለስን።
*
እነ ባቢ ለመቀበል እየገቡ ነበር እኔን ሲያዩ ቆም አሉ፤ እኔም ወደነሱ ሄድኩ። <<ባቢ ምነው? እእ..>> ሶስቱም የተጨነቁ መሰለኝ።
<<ኢብቲ ሁላችንም እናልፋለና? ፈራን እኮ..>> አቤላ ቀጠለ
<<እኔ እኮ ምንም አልመሰለኝም ነበር ኡፍፍ አሁን ግን እነዚህ አንቦቆቦቁኝ>> አቤላ እንዲህ ማለቱ አስገርሞኛል።
<<አቦ ፈታ በሉ እናልፋለን። አሁን ግቡ በቃ..>>
<<ኢብቲ አንቺ ለምን አሁን አትቀበይም ነይ አብረን እንግባ እእ..>> ማሂ።
<<አይ ቀስ ብዬ እቀበላለው እስቲ የአቤላንም ልየው። ያው አንዳይነት ነገር ነው እኮ ውጤታችን የሚሆነው...>>
<<በናትሽ ነይ አብረሽኝ ..እንደውም የቅድሙን አሁን እናውራና በኃላ አብረን እንቀበላለን እእ..>>
<<ኧረ አያሣስብክ እሱ ይደርሳል ..>>
<<እኔ ግን አሁን ብናወራ ይሻለኝ ነበር..ደግሞ አሁንም ስልክ የለሽማ?>>
<<አዎ ምነው? ልትገዛልኝ ነው? ሃሃሃሃ>>
<<የኔን ውሰጂው እኔ ኮ ሌላም አለኝ እቤት ...ሲሙን ላውጣውና ስልኩን ይዘሽው ትሄጃለሽ በቃ እሺ..>>
<<አንተ ደግሞ አታምርራ .. እኔ እኮ ቀፎ ስለሌለኝ አይደለም እቤት አይፈቀድልኝም። ገና በስምንተኛ ክፍል ነው የምባለው..>>
<<እንዳዛ ከሆነ እሺ፤ ግን እኮ ቁጥሬ ራሱ የለሽማ? ነይ ልፃፍልሽ ..>>
<<በኃላ ትሰጠኛለህ ኧረ ግባ እነ ባቢ አስጠበካቸው እኮ..>> እሺ ብሎ ወደ በሩ አመራ። በሩ ጋር ሲደርስ ዞር ብሎ አየኝ፤ በጣም ፈርቷል። አስተያየቱ አሁንም አይኔ ላይ አለ። ርቆ እንደሚሄድ ሰው ፍዝዝ ብሎ ነበር፤ እንዲገባ በአይኔ ምልክት ስሰጠው ገባ።
*
ከነ ራቢ ጋር ባቢ ማሂ ና አቤላ ስንት እንደሚያመጡ እየገመትን፤ የሶስቱንም ግምት ያገኘ ሎሊፖፕ እንደሚገዛለት ተስማምተን እስኪወጡ ዛፍ ስር ቁጭ ብለን መጠበቅ ጀመርን። ከደቂቃዎች ነኃላ የሆነች ልጅ እያለቀሰች ስትወጣ ደንግጠን ወደ በሩ ሄድን። ወደ ዘጠነኛ ክፍል ስላላለፈች ወደ አንዱ ጥግ ሄዳ ማልቀሷን ቀጠለች። ፍርሃታችን ይባሱኑ ጨመረ፤ ራቢ እጄን ጭምድድ አድርጋ <<ኧረ ፈራሁ እኛስ እናልፋለን ወይይ?>> አለች።
<<እንጃ አላውቅም። ራቢ እነ ማሂ ለምን ቆዩ?>> ዩሲ ነበረች በር በሩን እያየች። ወዲያው ማሂ እየሮጠ ወጣ ከተቀመጥኩበት ብድግ ብዬ በፍጥነት ወደሱ ስሄድ እነ አቤላም ከኃላው እየሮጡ መጡ። እሱ ጋር ከመድረሴ በፊት ወደ ጊቢው መውጫ እየፈጠነ መራመዱን ቀጠለ ከኃላ ባቢ ቢጠራውም ሊቆም አልቻለም።
እንደምንም ልደርስበፍት ሁለት እርምጃ ያህል ሲቀረኝ የጊቢውን በር በእግሩ ጠልዞ ወዲያው ወጣ። ተከትዬው ብወጣም እሱ ላይ መድረስ አልቻልኩም። ብጠራውም እጁን እያወናጨፈ ርቆ ሄደ። እኔም ባለሁበት ከአይኔ እስኪጠፋ ተከተልኩት። እነ ዩሲ መጥተው ወደ ውስጥ ገባን አቤላና ባቢ ተመልሰው መጡ።
<<በናትሽ ማሄሬ ኮ ወደቀ በአንድ ነጥብ ቲሽሽሽ ብሽቅ ነው ያኩት>> አቤላ ተናዶ ያወራል፤ ሌላው ዝም ብሎ ቁጭ ቁጭ ብሏል። ዛሬም ያልሆነ ስህተት ሰራሁ፤ ምን አለ መጀመሪያ ብናወራ እሱም እናውራ ሲለኝ እሺ ብለውስ? በቃ ሁሌ የራሴን ሃሳብ ብቻ ነው የምፈፅመው። ለዛሬ እንኳን እሱን ብሰማውስ እንዴት ከስህተቴ አልማርም? እሺ ካሁን ቡኃላ የት ነው የማገኘው? ጭራሽ ስልኩ ቁጥሩን ሲሰጠኝም አልተቀበልኩትም! ኧረ ኢብቲሣም ምንድነው ያደረግሽው? የነበረኝን አንድ እድል ባልሆነ መንገድ አጣሁ እኮ። ሁለት ወር ሙሉ ስጠብቀው የነበረው ቀን በአንዴ እንዲህ ምንም ሳላደርግ ሊያልፈኝ ነው እንዴ? እነዚያ የባከኑ ቀናቶችን በዛሬ አስተካክላው ብዬ ምንም ሳላደርግ እንዲሁ ባክነው ቀሩ ማለት ነው?



tgoop.com/Habibacalligraphy/1951
Create:
Last Update:

የባከኑ ቀናት
ክፍል አስራ አንድ
(ሂባ ሁዳ)
.
.
እነ ዩሲ በር ጋር ደርሰን ሁለታችንም ቆምን። እኔ ዝም ብያት ወደ ቤታቸው ስገባ ተከተለችኝ፤ ሳሎን በግማሽ በኩል በተነጠፈው መጅሊስ ላይ ዘፍ አልኩ። ዩስሪ ከደቂቃዎች ቡኃላ ልብሷን ቀያይራ አጠገቤ ቁጭ አለች፤ ዝም ብላ እኔ እስክነግራት ትጠብቃለች። ሁሌም በከፋኝ ሰዐት እነሱ ቤት ሄጄ ነው የሚወጣልኝ... ሁሉንም ዝርግፍግፍ አድርጌ እነግራታለሁ። ከኔ በላይ እሷ ትጨነቃለች፤ ዛሬ ግን ዝምታዬ በዛባት መሰለኝ ለማውራት ተገደደች።
<<ኢብቲዬ ሀቢብቲ ምንድነው የሆንሽው? ቅድም ጀምረሽ ልክ እንዳነበርሽ እኮ አውቃለሁ፤ ብቻችንን ስንሆን እናወራለን ብዬ ነው ዝም ያልኩት>> ምንም ሳልመልስላት ስቀር አላስቻላትም ድጋሚ ሌላ ቃላት ሰነ ዘረች... <<ማሂ ነው አይደል? እንዲ ያስከፋሽ.. እእ ኢብቲ ምን እንደተፈጠረ ንገሪኝ በአላህ እያስጨነቅሽኝ ነው>>
<<ዩሲ እሱኮ ምንም አላደረገም እኔ ነኝ እንጂ የጎዳሁት። ልቡን ስብርብር ነው ኮ ያደረኩት ምን አይነት ልጅ ነኝ!? አመት ሙሉ አጠገቤ ከችግሩ ጋር ሲታገል የነበረን ሰው እንዴት እገፋዋለሁ?...ዩሲ ንገሪኝ እስቲ ምን አይነት ግዴለሽ ሰው እንደሆንኩ..>> በመሃል ትንፋሼ መቆራረጥ ጀመረ፤ ከዚህ በላይ ማውራት አልቻልኩም። ዩሲ አቅፍኝ ማልቀስ ስትጀምር ይባሱኑ ስቅስቅ ብዬ አለቀስኩ። ሰዐቱ ወደ መምሸት ሲጠጋጋ ፊቴን ታጥቤ ወደ ቤት ገባሁ። ወንድሜ ፈተና ያልሰራሁ መስሎት ቢጨነቅም ትንሽ እንደደከመኝ ተናግሬ ከኢፍጣር ቡኃላ ወደ መኝታዬ ሄጄ ከራሴ ጋር ብዙ ተጨቃጨቅኩ። ከረጅም የድካም ሰዐታት በኃላ እንቅልፍ አሸለበኝ።
*
*
ከሁለት ወራት ቡኃላ የሚንስትሪ ውጤት ለመቀበል ትምህርት ቤት ተሰብስበናል። ከረጅም ጊዜ የናፍቆት ወሬ በኃላ ተማሪዎቹ ውጤት ለመቀበል ተሰለፉ፤ እኛ መጨረሻ ላይ እንቀበላለን ብለን ጥግ ላይ ቁጭ አልን። እነ አቤላ ተሰልፈዋል እሱ ዘጠና አመጣለሁ ብሎ አሲዟል፤ ባቢም ከኃላው ነበረ፤ ማሂን ግን አላየሁትም። ዛሬ ደግሞ በጣም እፈልገዋለሁ... ብዙ ነገር ላወራው ተዘጋጅቼበት ነው የመጣሁት፤ በዛ ላይ ናፍቆኛል። ባቢ ጋር ሄጄ ስጠይቀው እንደማይመጣ ነገረኝ። ለምን ምናምን ሣልል ቀጥ ብዬ ስሄድ ከኃላ ሂጃቤ ሲጎተት ለማስለቀቅ ዞር ስል በአየሁት ነገር ድንግጥ አልኩኝ <<ኢብቲዬ>> ብሎ እጁን ሲዘረጋ እንዴት እንደሆነ ባላውቅም ስጠጋው እቅፍ አደረገኝ፤ ምናልባት መተቃቀፋችን የመጀመሪያም የመጨረሻም መሰለኝ... ትንሽ እንደቆየን ድንግጥ ብዬ ከእቅፉ ወጣሁ።
<<እእ ይቅርታ ሳላስበው ነው...>> እንደመሳቀቅ ሲል አሳዘነኝ።
<<ኧረ ችግር የለውም ማሂ ...>>
<<እና ደህና ነሽ? እንዴት ነሽ ተጠፍፋን ኣ?>>
<<አለሁ አልሃምዱሊላህ አንተ እንዴት ነህ እእ ሁሉ ሰላም ነው?>>
<<አዎ ሰላም ነው። ደግሞ ረፍቱ ተስማምቶሻል እእ አምሮብሻል..>>
<<ሙድ አትያዝብኛ አንተ ነህ ያማረብህ እኮ...>>
<<ሃሃሃ ኧረ ባክሽ... ስገባ እኮ ሳይሽ ወዳንቺው መጣሁ፤ ጀለሶችን አላገኘዃቸውም ከመጣሽ ቆየሽ እንዴ?>>
<<ኧረ እዛ ጋር ተሰልፈዋል። አንተን ፈልጌ እኮ ባቢ አይመጣም ሲለኝ ወደዚህ ስመጣ ነው ያገኘሁህ አላወቁም መሰለኝ
እንደምትመጣ...>>
<<ኧረ ያውቃል ሊያዝግሽ ፈልጎ ነው ይሄ ዱዝ..እና ፈልገሽኝ ነው እእ?>> ፊቱ ላይ ፈገግታ ሞላ ሞላ ብሏል።
<<አዋ! ማሂ እፈልግሃለው ..እንዲ ቁመን አይደለም በቃ እንጨርስና እናወራለን።>>
<<ኧረ ደስ ይለኛል..በቃ እነ ባቢ ጋ ልሂድ እስኪ ..>> ፈጠን እያለ ወደ ተሰለፉት ልጆች አመራ። እሱ ወዳዛ ሲሄድ እነኢክሩ ወደኔ መጡ። ኢክራም ቸኩላ ሰለነበረ ካልተቀበልኩ ብላ ሄድን፤ እኔ ግን ፈራሁ። ውጪ ላይ ቆሜ እነሱ ገቡና እየሳቁ ወጡ እንደምታልፍ እርግጠኛ ነበርኩና ጥምጥም አልኩባት፤ ወዲያው ሸኝተናት ተመለስን።
*
እነ ባቢ ለመቀበል እየገቡ ነበር እኔን ሲያዩ ቆም አሉ፤ እኔም ወደነሱ ሄድኩ። <<ባቢ ምነው? እእ..>> ሶስቱም የተጨነቁ መሰለኝ።
<<ኢብቲ ሁላችንም እናልፋለና? ፈራን እኮ..>> አቤላ ቀጠለ
<<እኔ እኮ ምንም አልመሰለኝም ነበር ኡፍፍ አሁን ግን እነዚህ አንቦቆቦቁኝ>> አቤላ እንዲህ ማለቱ አስገርሞኛል።
<<አቦ ፈታ በሉ እናልፋለን። አሁን ግቡ በቃ..>>
<<ኢብቲ አንቺ ለምን አሁን አትቀበይም ነይ አብረን እንግባ እእ..>> ማሂ።
<<አይ ቀስ ብዬ እቀበላለው እስቲ የአቤላንም ልየው። ያው አንዳይነት ነገር ነው እኮ ውጤታችን የሚሆነው...>>
<<በናትሽ ነይ አብረሽኝ ..እንደውም የቅድሙን አሁን እናውራና በኃላ አብረን እንቀበላለን እእ..>>
<<ኧረ አያሣስብክ እሱ ይደርሳል ..>>
<<እኔ ግን አሁን ብናወራ ይሻለኝ ነበር..ደግሞ አሁንም ስልክ የለሽማ?>>
<<አዎ ምነው? ልትገዛልኝ ነው? ሃሃሃሃ>>
<<የኔን ውሰጂው እኔ ኮ ሌላም አለኝ እቤት ...ሲሙን ላውጣውና ስልኩን ይዘሽው ትሄጃለሽ በቃ እሺ..>>
<<አንተ ደግሞ አታምርራ .. እኔ እኮ ቀፎ ስለሌለኝ አይደለም እቤት አይፈቀድልኝም። ገና በስምንተኛ ክፍል ነው የምባለው..>>
<<እንዳዛ ከሆነ እሺ፤ ግን እኮ ቁጥሬ ራሱ የለሽማ? ነይ ልፃፍልሽ ..>>
<<በኃላ ትሰጠኛለህ ኧረ ግባ እነ ባቢ አስጠበካቸው እኮ..>> እሺ ብሎ ወደ በሩ አመራ። በሩ ጋር ሲደርስ ዞር ብሎ አየኝ፤ በጣም ፈርቷል። አስተያየቱ አሁንም አይኔ ላይ አለ። ርቆ እንደሚሄድ ሰው ፍዝዝ ብሎ ነበር፤ እንዲገባ በአይኔ ምልክት ስሰጠው ገባ።
*
ከነ ራቢ ጋር ባቢ ማሂ ና አቤላ ስንት እንደሚያመጡ እየገመትን፤ የሶስቱንም ግምት ያገኘ ሎሊፖፕ እንደሚገዛለት ተስማምተን እስኪወጡ ዛፍ ስር ቁጭ ብለን መጠበቅ ጀመርን። ከደቂቃዎች ነኃላ የሆነች ልጅ እያለቀሰች ስትወጣ ደንግጠን ወደ በሩ ሄድን። ወደ ዘጠነኛ ክፍል ስላላለፈች ወደ አንዱ ጥግ ሄዳ ማልቀሷን ቀጠለች። ፍርሃታችን ይባሱኑ ጨመረ፤ ራቢ እጄን ጭምድድ አድርጋ <<ኧረ ፈራሁ እኛስ እናልፋለን ወይይ?>> አለች።
<<እንጃ አላውቅም። ራቢ እነ ማሂ ለምን ቆዩ?>> ዩሲ ነበረች በር በሩን እያየች። ወዲያው ማሂ እየሮጠ ወጣ ከተቀመጥኩበት ብድግ ብዬ በፍጥነት ወደሱ ስሄድ እነ አቤላም ከኃላው እየሮጡ መጡ። እሱ ጋር ከመድረሴ በፊት ወደ ጊቢው መውጫ እየፈጠነ መራመዱን ቀጠለ ከኃላ ባቢ ቢጠራውም ሊቆም አልቻለም።
እንደምንም ልደርስበፍት ሁለት እርምጃ ያህል ሲቀረኝ የጊቢውን በር በእግሩ ጠልዞ ወዲያው ወጣ። ተከትዬው ብወጣም እሱ ላይ መድረስ አልቻልኩም። ብጠራውም እጁን እያወናጨፈ ርቆ ሄደ። እኔም ባለሁበት ከአይኔ እስኪጠፋ ተከተልኩት። እነ ዩሲ መጥተው ወደ ውስጥ ገባን አቤላና ባቢ ተመልሰው መጡ።
<<በናትሽ ማሄሬ ኮ ወደቀ በአንድ ነጥብ ቲሽሽሽ ብሽቅ ነው ያኩት>> አቤላ ተናዶ ያወራል፤ ሌላው ዝም ብሎ ቁጭ ቁጭ ብሏል። ዛሬም ያልሆነ ስህተት ሰራሁ፤ ምን አለ መጀመሪያ ብናወራ እሱም እናውራ ሲለኝ እሺ ብለውስ? በቃ ሁሌ የራሴን ሃሳብ ብቻ ነው የምፈፅመው። ለዛሬ እንኳን እሱን ብሰማውስ እንዴት ከስህተቴ አልማርም? እሺ ካሁን ቡኃላ የት ነው የማገኘው? ጭራሽ ስልኩ ቁጥሩን ሲሰጠኝም አልተቀበልኩትም! ኧረ ኢብቲሣም ምንድነው ያደረግሽው? የነበረኝን አንድ እድል ባልሆነ መንገድ አጣሁ እኮ። ሁለት ወር ሙሉ ስጠብቀው የነበረው ቀን በአንዴ እንዲህ ምንም ሳላደርግ ሊያልፈኝ ነው እንዴ? እነዚያ የባከኑ ቀናቶችን በዛሬ አስተካክላው ብዬ ምንም ሳላደርግ እንዲሁ ባክነው ቀሩ ማለት ነው?

BY Habiba Calligraphy


Share with your friend now:
tgoop.com/Habibacalligraphy/1951

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

Matt Hussey, editorial director at NEAR Protocol also responded to this news with “#meIRL”. Just as you search “Bear Market Screaming” in Telegram, you will see a Pepe frog yelling as the group’s featured image. So far, more than a dozen different members have contributed to the group, posting voice notes of themselves screaming, yelling, groaning, and wailing in various pitches and rhythms. The Channel name and bio must be no more than 255 characters long The Standard Channel To edit your name or bio, click the Menu icon and select “Manage Channel.”
from us


Telegram Habiba Calligraphy
FROM American