tgoop.com/Habibacalligraphy/1952
Last Update:
.
<<ኢብቲ ተማሪው እኮ ተቀበለ እኛ ብቻ ቀረን እእ እንቀበል በቃ ቁርጣችንን እንወቀው>> ራቢ ከገባሁበት ሃሳብ መለሰችኝ እሺ ተባብለን ለመቀበል ተስማምተን ወደ በሩ ጋ ስንደርስ አቤላ እየወጣ ተገጣጠምን የውጤቱን ካርድ ሳይ ልቤ ምቱን ጨመረብኝ።
<<እእ አቤላ እ.ን.ዴ.ት ነው..>>
<<አቦ ተይኝ እኔ ደግሞ አልፋለው ማለቴ ድሮም ካንቺ ሰርቼ>>
<<ማለት?>> ዩሲ ደንገጥ ብላ ወረቀቱን ለማየት ስትጠጋው።
<<ቲ! ያው ናችሁ። ምን የወደኩበትን ለማየት ምን አስቸኮለሽ ዞርበይ ከዚህ ሲያስጠሉ>> ሶስታችንንም ገልመጥ አድርጎ አየን።
<<በናትህ አቤላ ንገረኝ ወደቅን ነው የምትለኝ? ድምፄ ከፍ እያለ መጣ።>>
<<አቤላ አትበይኝ ዱዝ! አቤል ነው ስሜ። አው እንኳን ደስ አለሽ እኔ ወደኩኝ ከሌላው ብሰራስ አንቺን አምኜ ሙሉ ካንቺ መስራቴ..>> ከዚህ በላይ አልሰማሁትም፤ እየተቻኮልኩ ወደ ቢሮው ገባሁ
<<ይቅርታ የኔን ወረቀት ..>>
<<እንዴ ኢብቲሳም የት ጠፍተሽ ነው እስካሁን?>> ባይሎጂ አስተማሪያችን ስሜን እየፈለገ። <<እሲቲ ቁጭ በይ እስከዛው>> እንድቀመጥ ጋበዘኝ። ቢለኝም እዛው መቆምን መረጥኩ... እስኪያገኘው ጨነቀኝ። አንድ ወረቀት ነጥሎ እንደያዘ።
<<ምን ነክቶሽ ነው ግን ምን ሁነሽ ነበር?>>
<<ማለት ቲቸር? መቼ?>> ግራ እየተጋባሁ ጠየኩት ...
<<መቼ? ለፈተናው ነዋ። ጥሩ ጎበዝ ልጅ አልበርሽ እንዴ? በአንዴ ምንድነው እንደዚህ የቀየረሽ>> አስተማሪው አፈጠጠብኝ <ምነው ባልገባሁ> አልኩኝ በውስጤ።
<<ቲቸር ም.ን.ድ.ነው እ ውጤቴ?>> የሞት ሞቴን ጠየኩት።
<<እኛማ ብዙ ተስፋ የጣልንብሽ ልጅ ነበርሽ፤ የትምህርት ቤቱንም ስም ታስጠሪያለሽ ብለን ጠብቀን ነበር አዝናለሁ ኢብቲሳም። አሉኝ ከምላቸው ዋነኛዋ ተማሪ እንዲህ አልጠበኩም ነበር አፍሬብሻለው...>> አይኖቼ በዕንባ እየተሞሉ ልቤ ምቱን ላይ በላይ ሲደጋግመው በሰማሁት ነገር ልዘረር ምንም አልቀረኝም።
<<እና ወ.ድ.ቀ.ሻ.ል ነው..>>
<<በሚያሳዝን ሁኔታ አዎ>> በተቀመጠበት ወንበር ወደ ኃላ ለጠጥ ብሎ እየተቀመጠ የምሆነውን ያያል።
በምን ሃይል እንደሆነ ባይገባኝም ወረቀቴን ስጠኝ ብዬ ጮኽኩበት። በር አካባቢ የነበሩት ዩሲና ራቢ ገቡ። እሱ ከቦታው ሳይንቀሳቀስ..
<<ብሰጥሽስ ምን ያደርግልሻል>> ብሎ የሹፈት ፈገግ አለ። እነ ራቢ ደንግጠው እርስ በርሳቸው ይተያያሉ። ይባሱኑ ብሽቅ አልኩና <<ወረቀቴን ስጠኝ ብወድቅስ ምን አገባህ>> ብዬ ከእጁ ላይ መንትፌው ወደ ውጪ ወጣሁ። ራቢ ተከትላኝ ወረቀቱን ተቀበለችኝ፤ ራቢ ለዩሲ <<ነይ! ነይ!ቶሎ በይ>> ስትል ዩሲ ምንድነው ብላ ራቢ ጋር መጣች። እኔ መቆም አቅቶኝ ከዚህ ወደዚያ እሽከረከራለሁ፤ በመሃል ራቢ <<የስሥሥሥሥሥሥሥሥ>> ብላ ስትቀውጠው ከዩሲ ጋር ተቃቀፉ።
<<ኢብቲ ነይማ አፍጥኝው>> ብላ ወደኔ መጣች። እጇን ወረቀቱ ላይ እየጠቆመችኝ ትስቃለች፤ 96 ይላል ፁሁፉ።
<<እእ.. ደስ ይላል ራቢ። ያንቺ ነው የዩሲ?>> ብዬ ሁለቱንም አፍራርቄ ሳይ ይስቃሉ አብራቼው ፈገግ ለማለት ስሞክር
<<ኢብቲ እይማ>> ብላ ድጋማ ከወረቀቱ ላይ ሌላ ነገር አስነበበችኝ። <ኢብቲሳም ማህሙድ> ይላል።
<<ማለት?>> ሁለቱም ላይ አፈጠጥኩባቸው።
<<ያንቺ ኮ ነው 96 የኔ ውድ ነቀነቅሽው ኮ!>> ብላ ጥምጥም ስትልብኝ ደግሜ አየሁት ዩሲም ተጨመረች። በመሃል <ሰርፕራይዝ> ሚል ድምፅ ሰማን። ዞር ስል አቤላ እየሳቀ ነበር፤ እኔ አልፌ እሱ መውደቁ ትዝ ሲለኝ ወረቀቱን ለራቢ ሰጥቻት ወደሱ ሄድኩ፤ <አቤላ..> ስለው ምንም ሣይመልስልኝ ወረቀቱን ሰጠኝ የማየውን ማመን ስላቻልኩ እሱን አየሁት <<አዎ ነቀነቅነው 92>> ብሎ ሳቀ
<<ውይኔ ደስ ሲል>> ብዬ ስጮኽ <<ተጫወትንብሻ ከቲቸር ጋ!>> ብሎ ከት ብሎ ሳቀብኝ። ብሽቅ አልኩና ልመታው ማሯሯጥ ጀመርኩ።
.
.
ይቀጥላል...
www.tgoop.com/Habibacalligraphy
BY Habiba Calligraphy
Share with your friend now:
tgoop.com/Habibacalligraphy/1952