HABIBACALLIGRAPHY Telegram 1953
የባከኑ ቀናት
ክፍል አስራ ሁለት
(ሂባ ሁዳ)
.
.
ከአቤላ ጋር ቁጭ ካልን በኃላ ..ምን አለ የማሂም እንዲሁ ቀልድ ነው ብላችሁኝ ደስታዬ ሙሉ ቢሆን እያልኩ አስባለሁ። እነ ዩሲም ምርጥ ውጤት ስላመጡ በጣም ደስ ብሏቸዋል። ሶስታችንም የትምህርት ቤቱ ሰቃይ ሆነናል። እኔ ግን ልቤ ላይ ሌላ ጭንቀት አለ እሱም ማሂር ነው። በቃ በአንድ አጋጣሚ ተገናኝተን በሌላ አጋጣሚ ተለያየን ማለት ነው? እኔ ግን እጣፈንታን ተቀየምኳት.. ራሷ አገናኝታን ራሷው አለያየችን። አሁን ማሂር ምን ይሁን የሚሆነው..
<<ኢብቲ ማሂ ስለወደቀ ከፋሽ አ? እኔም ደብሮኛል የሌለ አብሬው ብወድቅ ነው ያልኩት>> አቤላ እንዲህ ሲለኝ ስለ ማሂ እያሰብኩ ስለነበረ ደነገጥኩ።
<<አዎ አቤላ አሳዘነኝ.. ሁኔታውን አይተኸዋ። እኔ ምልህ እስቲ ስለ እሱ ንገረኝ... ፋሚሊዮቹ ምን አይነት ናቸው?>>
<<አይ ስለወደቀ እንኳን አይቆጡትም አያሣስብሽ..>> የጠየኩት ጥያቄ የገባው አልመሰለኝም።
<<ሣይሆን አላይደል እምነታቸው ላይ...>>
<<እእ እሱን ነበር እንዴ የጠየቅሽኝ... አንድም እኮ የጓዳው እሱ ነው። ለዛ ነው ቶሎ ሆድ የሚብሰው፤ ሰውም ብዙ የማይቀርበው እንዳያጣ ስለሚፈራ ነው። ኡፍፍ ብራዘር ምርጥ ልጅ ኮ ነበረ>>
<<ማለት አቤላ ቤተሰቦቹ ላይ ችግር አለ? ማለቴ አይስማሙ?>>
<<ሣይሆን እናቱ ከሞተች ቆየት ብሏል። ያኔ ጩጬ ነበር፤ ፈታ ብሎ ነበር የሚያድገው። እናቱ ከሞተች በኃላ ነገራቶች ተቀየሩ ፋዘሩም ሌላ ሚስት አገባና ከአዲሱ ሚስቱ ጋር እምነቱን ቀየረ፤ በፊት ኮ ምርጥ ሼኪ ነበር ይባላል። በቃ ማሂሬም ትምህርት ቤት ብቻ አስገብተው ላሽ አሉት፤ ግን ፋዙካው የሌለ ነው የሚወደው። እንዲከፋው ምናምን አይፈልጉም ግን የሚፈልገውን አላሟሉለትም። አለ አይደል ከመሰረታዊ ነገር ውጪ እሱ በጣም የሚያስጨንቀው እምነቱ ነበር። በፊት ብዙም አያርፍም ነበር ሲቆይ ሲቆይ ግን የሌለ ይሸምመው ጀመረ። አብሶ ሙስሊሞችን ሲያይ ሽምቅቅ ነው የሚለው፤ አንዳንዴ ምን እንደሚሉት አይገባውም። ከነርሱ ጋር እንደፈለገ ፈታ ብሎ አያወራም፤
ምክንያቱም እነሱ ከሚያውቁት ምንም የሚያውቀው ነገር የለም። ሲጠይቃቸው ደግሞ <እንዴት አታውቅም ለስሙ ሙስሊም ነህ> ብለው ሙድ መያዣ ያደርጉታል። ለዛም ነው ከኔና ከባቢ ጋር ብቻ የምታይው፤ እኛ ከድሮም አብረን ስለተማርን ሁሉንም ነገር እናውቃለን። ምንም አንደባበቅም.. በቃ እኔ ማሂሮ የመጭ ነው የሚያሳዝነኝ፤ የሌለ ምርጥ ልጅ እኮ ነው በናትሽ። አንድ ጥሩ ሰው ቢገጥመው እኮ የሌለ ደስተኛ መሆን ይችላል።>>
<<አቤላ እኔ ግን ምን አይነት ሰው ነኝ? እንዴት ምንም ማድረግ ያቅተኛል..>>
<<ኢብቲሣም ምንአልባት ከዛሬ ቡኃላ አንገናኝም ይሆናል ከመለያየታችን በፊት ግን ልነግርሽ የምፈልገው ነገር አለ ...>> አቤላ እጁ ላይ ያለውን ክር እያሽከረከረ ንግግሩን ቀጠለ።
<<ኢብቲ በመጀመሪያ ያሳለፍነው ጊዜ መቼም ልረሳው አልችልም። ለኔ ሁላችሁም ምርጥ ነበራችሁ፤ ትለዩብኛላችሁ። ሁሌ አብረን ብንሆን ምነኛ ደስ ባለኝ ግን መለያየት ልክ እንደመገናኘት ነው ፈልገሽ ሣይሆን መሆን ስላለበት ብቻ የሚሆን። እና ደግሞ ኢብቲ ሁላችንም እናከብርሽ ነበር ባቢም ማሂሮም ስለሌሉ እነሱንም ሁኜ ነው የምነግርሽ። በተለይ ለኔና ለባቢ በጣም ለውጠሽና፤ ብዙ ነገሮችን እንድናይ ረድተሽናል። የሰው ክብር ከምንም በላይ አሳውቀሽናል። ብቻ ብዙ ነገር.. ታዲያ ግን ይሄን ለኛ ባደረግሽ ጊዜ ካንቺ ሌላ ነገርን ጠብቀን ነበር። መጠበቅ ብቻ ሣይሆን ታደርጊዋለሽ ብለን ነበር..ግን ምን ያደርጋል፤ አንዳችን አርፍደናል አልያም ዘግይተናል። መቼስ ገብቶሻል አይደል? ስለ ማሂር ነው። በጣም እንድትቀራረቡ ከባቢ ጋር ብዙ ነገር ፈጣጥረን ነበር። እንድታወሩ ብዙ አጋጣሚ መሳይ ነገሮችን ስንፈጣጥር ነበር። የኛ ልፋት ውጤቱ ላይ ሳይደረስ ቀረ። ለምን? አንድም ማሂር ፈሪ ስለሆነ፤ ከዛሬ ነገ አወራታለሁ ሲል። ሌላው ደግሞ ያንቺ ትኩረት አለመስጠት ነው። እንዴ ኢብቲ ብዙ አጋጣሚዎች ላይ እኮ ማሂ ስለእምነቱ እንደማያውቅ ካንቺ መማር እንደሚፈልግ ነግሮሽ ነበር። ግን አንቺ ሁሌ ቀልድ እየመሰለሽ ታልፊዋለሽ። ከዛሬ ነገ ቀኑ እየሄደ ሲመጣ ማሂር ሁሉንም እንዲነግርሽ በግድ አሳምነን ላክነው። ግ'ና ምን ያደርጋል..እቸኩላለው ብለሽ ልታዳምጭው ፍቃደኛ አነበርሽም፤ ሌላ ስብራት ፈጠርሽበት። ትዝ ይልሻል አይደለ? ከቀናት በአንዱ ቅዳሜ ቀን ነበር። የዛኔ ያየሁትን የማሂን ተስፋ ማጣት ምንም ላይ ደግሜ የማየው አይመስለኝም። ሁላችንም ባንቺ እምነት ነበረን፤ ነገራቶችን ታስተካኪያለሽ ብለን... ደግሞ እኔ ወይ ባቢ ከምንነግርሽ ራሱ ቢነግርሽ እንደሚሻል አስበን ነው። ብቻ ኢብቲ አውቃለሁ፤ በጣም ጎበዝ ልጅ ነሽ፤ በትምህርትም በእምነታችሁም። እኔ በአስራ አራት አመቷ ወንድ አልጨብጥም የምትል ሴት ካንቺ ውጪ አላውቅም። በዛ ላይ በጣም ተግባቢም ልጅ ነሽ። ግን አንድ ነገር ይጎልሻል፤ ሰዎችን ማድመጥ፣ በዙሪያሽ ላሉት ትኩረት መስጠት.. ይሄን ባህሪሽ በናትሽ እንደምንም አስተካኪው። ድጋሚ የማሂን አይነት ሰው ትኩረት እንዳትነፍጊ። ኢብቲ የምር በጣም አመሰግናለሁ። ያው እኔ ከባቢ ና ማሂሮ ተለይቼ ያለፍኩት ካንቺ ስለሰራሁ ነው። የዛሬውን ቀን እንዲ አልጠበቅናትም ነበር። ከነ ማሂሮ ጋር ፈታ እንላለን ብለን ነበር አልሆነም። የስምንተኛ ክፍል ላይፍ ለኔ ከየትኛውም የትምህርት ቤት ላይፍ በላይ ነው። ፈጣሪ መልካሙን ያድርግልን፤ ምን አልባት በሆነ አጋጣሚ እንገናኝ ይሆናል።>> ከተቀመጠበት ተነሳ። እኔ ምን አይነት ስሜት ውስጥ እንደሆንኩ አላውቅም... አቤላ እንዲህ ቁም ነገራቶችን ያወራል ብዬ አልጠበኩም ነበር። እኔም ተነሳሁ።
<<ቻው ኢብቲ በቃ>>
<<አቤላ..>>
<<ወዬ>> ፊቱን ሙሉ ለሙሉ ወደኔ አዞረ።
<<በጣም ይቅርታ ስለሁሉም..>> ታምቆ የተያዘው ዕንባዬ ቀደመኝ። እኔ ከዕንባዬ ጋር ስታገል አቤላ እየሮጠ ወደ በሩ ሸሸ። ከአቤላ መሸሽ ጋር የኔም ህልምና ተስፋ ላይመለስ አብሮ ሸሸ፤ ፀፀቱ እኔው ጋር ቀረ።
.
አንድ አመት ሙሉ ከኔው ጋር እየዋለ ለሚሄድ፤ በየቀኑ ከጎኔ ለማገኘው.... ተስፋውን በኔ ላይ ጥሎ መሰበሩን ለሚያሳየኝ ሰው.... መጠገን ትቼ ተስፋውን ገደል መክተቴ... ምን ያህል የባከኑ ቀኖች.... ከኔ ጋር እንደነበሩ አሁን ገባኝ ....ቢገባኝስ ምን ሊፈይድ... ከነስብራቱ ተስፋውን ጥሎ... ማሂሬ ሄደ እኮ!..
.
.
ይቀጥላል...

www.tgoop.com/Habibacalligraphy



tgoop.com/Habibacalligraphy/1953
Create:
Last Update:

የባከኑ ቀናት
ክፍል አስራ ሁለት
(ሂባ ሁዳ)
.
.
ከአቤላ ጋር ቁጭ ካልን በኃላ ..ምን አለ የማሂም እንዲሁ ቀልድ ነው ብላችሁኝ ደስታዬ ሙሉ ቢሆን እያልኩ አስባለሁ። እነ ዩሲም ምርጥ ውጤት ስላመጡ በጣም ደስ ብሏቸዋል። ሶስታችንም የትምህርት ቤቱ ሰቃይ ሆነናል። እኔ ግን ልቤ ላይ ሌላ ጭንቀት አለ እሱም ማሂር ነው። በቃ በአንድ አጋጣሚ ተገናኝተን በሌላ አጋጣሚ ተለያየን ማለት ነው? እኔ ግን እጣፈንታን ተቀየምኳት.. ራሷ አገናኝታን ራሷው አለያየችን። አሁን ማሂር ምን ይሁን የሚሆነው..
<<ኢብቲ ማሂ ስለወደቀ ከፋሽ አ? እኔም ደብሮኛል የሌለ አብሬው ብወድቅ ነው ያልኩት>> አቤላ እንዲህ ሲለኝ ስለ ማሂ እያሰብኩ ስለነበረ ደነገጥኩ።
<<አዎ አቤላ አሳዘነኝ.. ሁኔታውን አይተኸዋ። እኔ ምልህ እስቲ ስለ እሱ ንገረኝ... ፋሚሊዮቹ ምን አይነት ናቸው?>>
<<አይ ስለወደቀ እንኳን አይቆጡትም አያሣስብሽ..>> የጠየኩት ጥያቄ የገባው አልመሰለኝም።
<<ሣይሆን አላይደል እምነታቸው ላይ...>>
<<እእ እሱን ነበር እንዴ የጠየቅሽኝ... አንድም እኮ የጓዳው እሱ ነው። ለዛ ነው ቶሎ ሆድ የሚብሰው፤ ሰውም ብዙ የማይቀርበው እንዳያጣ ስለሚፈራ ነው። ኡፍፍ ብራዘር ምርጥ ልጅ ኮ ነበረ>>
<<ማለት አቤላ ቤተሰቦቹ ላይ ችግር አለ? ማለቴ አይስማሙ?>>
<<ሣይሆን እናቱ ከሞተች ቆየት ብሏል። ያኔ ጩጬ ነበር፤ ፈታ ብሎ ነበር የሚያድገው። እናቱ ከሞተች በኃላ ነገራቶች ተቀየሩ ፋዘሩም ሌላ ሚስት አገባና ከአዲሱ ሚስቱ ጋር እምነቱን ቀየረ፤ በፊት ኮ ምርጥ ሼኪ ነበር ይባላል። በቃ ማሂሬም ትምህርት ቤት ብቻ አስገብተው ላሽ አሉት፤ ግን ፋዙካው የሌለ ነው የሚወደው። እንዲከፋው ምናምን አይፈልጉም ግን የሚፈልገውን አላሟሉለትም። አለ አይደል ከመሰረታዊ ነገር ውጪ እሱ በጣም የሚያስጨንቀው እምነቱ ነበር። በፊት ብዙም አያርፍም ነበር ሲቆይ ሲቆይ ግን የሌለ ይሸምመው ጀመረ። አብሶ ሙስሊሞችን ሲያይ ሽምቅቅ ነው የሚለው፤ አንዳንዴ ምን እንደሚሉት አይገባውም። ከነርሱ ጋር እንደፈለገ ፈታ ብሎ አያወራም፤
ምክንያቱም እነሱ ከሚያውቁት ምንም የሚያውቀው ነገር የለም። ሲጠይቃቸው ደግሞ <እንዴት አታውቅም ለስሙ ሙስሊም ነህ> ብለው ሙድ መያዣ ያደርጉታል። ለዛም ነው ከኔና ከባቢ ጋር ብቻ የምታይው፤ እኛ ከድሮም አብረን ስለተማርን ሁሉንም ነገር እናውቃለን። ምንም አንደባበቅም.. በቃ እኔ ማሂሮ የመጭ ነው የሚያሳዝነኝ፤ የሌለ ምርጥ ልጅ እኮ ነው በናትሽ። አንድ ጥሩ ሰው ቢገጥመው እኮ የሌለ ደስተኛ መሆን ይችላል።>>
<<አቤላ እኔ ግን ምን አይነት ሰው ነኝ? እንዴት ምንም ማድረግ ያቅተኛል..>>
<<ኢብቲሣም ምንአልባት ከዛሬ ቡኃላ አንገናኝም ይሆናል ከመለያየታችን በፊት ግን ልነግርሽ የምፈልገው ነገር አለ ...>> አቤላ እጁ ላይ ያለውን ክር እያሽከረከረ ንግግሩን ቀጠለ።
<<ኢብቲ በመጀመሪያ ያሳለፍነው ጊዜ መቼም ልረሳው አልችልም። ለኔ ሁላችሁም ምርጥ ነበራችሁ፤ ትለዩብኛላችሁ። ሁሌ አብረን ብንሆን ምነኛ ደስ ባለኝ ግን መለያየት ልክ እንደመገናኘት ነው ፈልገሽ ሣይሆን መሆን ስላለበት ብቻ የሚሆን። እና ደግሞ ኢብቲ ሁላችንም እናከብርሽ ነበር ባቢም ማሂሮም ስለሌሉ እነሱንም ሁኜ ነው የምነግርሽ። በተለይ ለኔና ለባቢ በጣም ለውጠሽና፤ ብዙ ነገሮችን እንድናይ ረድተሽናል። የሰው ክብር ከምንም በላይ አሳውቀሽናል። ብቻ ብዙ ነገር.. ታዲያ ግን ይሄን ለኛ ባደረግሽ ጊዜ ካንቺ ሌላ ነገርን ጠብቀን ነበር። መጠበቅ ብቻ ሣይሆን ታደርጊዋለሽ ብለን ነበር..ግን ምን ያደርጋል፤ አንዳችን አርፍደናል አልያም ዘግይተናል። መቼስ ገብቶሻል አይደል? ስለ ማሂር ነው። በጣም እንድትቀራረቡ ከባቢ ጋር ብዙ ነገር ፈጣጥረን ነበር። እንድታወሩ ብዙ አጋጣሚ መሳይ ነገሮችን ስንፈጣጥር ነበር። የኛ ልፋት ውጤቱ ላይ ሳይደረስ ቀረ። ለምን? አንድም ማሂር ፈሪ ስለሆነ፤ ከዛሬ ነገ አወራታለሁ ሲል። ሌላው ደግሞ ያንቺ ትኩረት አለመስጠት ነው። እንዴ ኢብቲ ብዙ አጋጣሚዎች ላይ እኮ ማሂ ስለእምነቱ እንደማያውቅ ካንቺ መማር እንደሚፈልግ ነግሮሽ ነበር። ግን አንቺ ሁሌ ቀልድ እየመሰለሽ ታልፊዋለሽ። ከዛሬ ነገ ቀኑ እየሄደ ሲመጣ ማሂር ሁሉንም እንዲነግርሽ በግድ አሳምነን ላክነው። ግ'ና ምን ያደርጋል..እቸኩላለው ብለሽ ልታዳምጭው ፍቃደኛ አነበርሽም፤ ሌላ ስብራት ፈጠርሽበት። ትዝ ይልሻል አይደለ? ከቀናት በአንዱ ቅዳሜ ቀን ነበር። የዛኔ ያየሁትን የማሂን ተስፋ ማጣት ምንም ላይ ደግሜ የማየው አይመስለኝም። ሁላችንም ባንቺ እምነት ነበረን፤ ነገራቶችን ታስተካኪያለሽ ብለን... ደግሞ እኔ ወይ ባቢ ከምንነግርሽ ራሱ ቢነግርሽ እንደሚሻል አስበን ነው። ብቻ ኢብቲ አውቃለሁ፤ በጣም ጎበዝ ልጅ ነሽ፤ በትምህርትም በእምነታችሁም። እኔ በአስራ አራት አመቷ ወንድ አልጨብጥም የምትል ሴት ካንቺ ውጪ አላውቅም። በዛ ላይ በጣም ተግባቢም ልጅ ነሽ። ግን አንድ ነገር ይጎልሻል፤ ሰዎችን ማድመጥ፣ በዙሪያሽ ላሉት ትኩረት መስጠት.. ይሄን ባህሪሽ በናትሽ እንደምንም አስተካኪው። ድጋሚ የማሂን አይነት ሰው ትኩረት እንዳትነፍጊ። ኢብቲ የምር በጣም አመሰግናለሁ። ያው እኔ ከባቢ ና ማሂሮ ተለይቼ ያለፍኩት ካንቺ ስለሰራሁ ነው። የዛሬውን ቀን እንዲ አልጠበቅናትም ነበር። ከነ ማሂሮ ጋር ፈታ እንላለን ብለን ነበር አልሆነም። የስምንተኛ ክፍል ላይፍ ለኔ ከየትኛውም የትምህርት ቤት ላይፍ በላይ ነው። ፈጣሪ መልካሙን ያድርግልን፤ ምን አልባት በሆነ አጋጣሚ እንገናኝ ይሆናል።>> ከተቀመጠበት ተነሳ። እኔ ምን አይነት ስሜት ውስጥ እንደሆንኩ አላውቅም... አቤላ እንዲህ ቁም ነገራቶችን ያወራል ብዬ አልጠበኩም ነበር። እኔም ተነሳሁ።
<<ቻው ኢብቲ በቃ>>
<<አቤላ..>>
<<ወዬ>> ፊቱን ሙሉ ለሙሉ ወደኔ አዞረ።
<<በጣም ይቅርታ ስለሁሉም..>> ታምቆ የተያዘው ዕንባዬ ቀደመኝ። እኔ ከዕንባዬ ጋር ስታገል አቤላ እየሮጠ ወደ በሩ ሸሸ። ከአቤላ መሸሽ ጋር የኔም ህልምና ተስፋ ላይመለስ አብሮ ሸሸ፤ ፀፀቱ እኔው ጋር ቀረ።
.
አንድ አመት ሙሉ ከኔው ጋር እየዋለ ለሚሄድ፤ በየቀኑ ከጎኔ ለማገኘው.... ተስፋውን በኔ ላይ ጥሎ መሰበሩን ለሚያሳየኝ ሰው.... መጠገን ትቼ ተስፋውን ገደል መክተቴ... ምን ያህል የባከኑ ቀኖች.... ከኔ ጋር እንደነበሩ አሁን ገባኝ ....ቢገባኝስ ምን ሊፈይድ... ከነስብራቱ ተስፋውን ጥሎ... ማሂሬ ሄደ እኮ!..
.
.
ይቀጥላል...

www.tgoop.com/Habibacalligraphy

BY Habiba Calligraphy




Share with your friend now:
tgoop.com/Habibacalligraphy/1953

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

4How to customize a Telegram channel? Telegram message that reads: "Bear Market Screaming Therapy Group. You are only allowed to send screaming voice notes. Everything else = BAN. Text pics, videos, stickers, gif = BAN. Anything other than screaming = BAN. You think you are smart = BAN. Hui said the time period and nature of some offences “overlapped” and thus their prison terms could be served concurrently. The judge ordered Ng to be jailed for a total of six years and six months. “[The defendant] could not shift his criminal liability,” Hui said. Select “New Channel”
from us


Telegram Habiba Calligraphy
FROM American