HABIBACALLIGRAPHY Telegram 1960
የባከኑ ቀናት
ክፍል አስራ አምስት
(የመጨረሻው ክፍል)
(ሂባ ሁዳ)
.
.
ዝምታው ያስፈራል፤ ረጅም ደቂቃ ዝም አለ።
<<ማሂ እሺ አሁንስ?>>
<<አሁንማ... አሁንማ ኢብቲ...ተስፋ የቆረጠ ሰው አታውቂም?...ራሱን የጠላ ሰው?... መኖር የሰለቸው? ....እየኖረ የሞተ?.... ህልሙን ቅዠት የሆነበት?... ከራሱ ርቆ በሌሎች የተደበቀ.... ልቡን ላለማድመጥ ጩኸት የሚፈጥር?... ከኑሮ ለመሸሽ በጪስ የተወሸቀ?...ኢብቲ ከፊትሽ ያለው ለሴቶች ክብር ብሎ የሚጣላው ማሂር እኮ አይደለም። የሴቶችን ክብር የሚወስድ እንጂ..>> ድምፁ በሲቃ ታፈነ አይኖቹ መሸከም ያልቻሉትን ዕንባዎች ሲለቋቸው ቁልቁል ፈሰሱ። ከዚህ በላይ ራሴን መቆጣጠር አልቻልኩም። ድንዝዝ ያሉት እጆቼ ዕንባዬን መጥረግ ተሳናቸው። ምንም ቃል መናገር አልቻልኩም የማሂ ዕንባ እያይሁ ከማንባት ውጪ።
እንደምንም ራሱን አረጋግቶ ግንባሩን በሁለት እጆቹ ደጋፍ አደረገ
<<ኢ.ብ..ቲ>> ድምፁ መቆራረጥ ጀመረ። <<አ.ል.ች.ል.ም እንዲህ መኖር አህ.ህ.ህ>> እጆቹ እንደመንቀጥቀጥ አደረጋቸው።
<<ማሂሬ ደና ነህ?>> በጣም ደንግጫለው አይኑን ይጨፍናል መልሶ ይገልጣል ..
<<ማሂ ማሂሬ?>>ድምፁ ጠፋብኝ
<<ትንሽ ደቂቃ ብቻ... ይ.ተ.ወ.ኛ.ል ..>>
.
<<ኢብቲ አየሽ አይደል እዚህ ድረስ ነኝ.. በሰዐቱ ካልተጠቀምኩ እንዲህ ነው የሚያደርገኝ መውጣት ማልችለው ሱስ ውስጥ ወድቄያለሁ። ኢብቲ ከዚህ ቡኃላ የኔ የምለው ምንም አይነት ነገር የለኝም፤ የኔ ቀርቶ እኔም አልኖርም። እኔ እኮ አሁን አንቺን ማግኘቴ ደስ ብሎኛል። ቢያንስ እንደኔ ሌላ ሰው ሰው በማጣት የህልሙ ብርሃን ጭላንጭል ሲሆን... ጭላንጭሉን ወደ ብርሃን እንዲቀየር እንደምታግዥው ለራሴ ቃል ትገቢልኛለሽ። ከአሁን በኃላ ሰሚ ላጡ አባሽ ለሚፈልጉ ዕንባዎች እንደ አሁኑ አብረሻቸው ከማልቀስ ይልቅ መፍትሄ እንደምታመጪላቸው እንድትነግሪኝ እፈልጋለሁ። ኢብቲ ያለፈው ፀፅቶሻል? ጎድቶሻል አይደል? በሌሌች አስተካኪው። ከመስማት ማድመጥን ልመጂ። ማየት ብቻ ሣይሆን በመመልከት አስተውዪ ...>>
<<ማሂሬ እንዴት ልቻለው? ይሄን ሁሉ ከመሆኑ በፊት እኮ..ማሂ ይሄ ሁሉ በኔ እኮ ነው! ራሴን ምን ብዬ ላሳምነው?>> ከዚህ በላይ ማውራት አልቻልኩም ስቅስቅ ብዬ ከማልቀስ ውጪ።
<<ኢብቲ ነገርኩሽ እኮ... በቃ ያለፈ ታሪክ ነው። ያገኘሁሽ ሁላ በኔ ምክንያት መጨነቅሽን ትተሽ ሰላምሽን እንድታገኚ ነው።>>
<<ማሂ ለዚህ ሁሉ ስህተት ምንድነው ይቅርታው?>>
<<ኢብቲዬ ማርፈድ ከትምህርት ቤት ይልቅ ህይወት ላይ ዋጋ ያስከፍላል። በኔ ህይወት አንቺ አልዘገየሽም፤ እኔ ቸኮልኩ እንጂ.. እኔን እርሺኝ ከአሁን በኃላ የሚመጡትን ማሂሮችን እርጂያቸው። ከዚህ በላይ ስታለቅሺ የማየት አቅሙ የለኝም። ማንም አንቺን ባያስከፋሽ ምኞቴ ነው። በኔ ምክንያት እንድታለቅሺ ከቶ አይቻለኝም። ቃል እንድትሰጭኝ ፈልጋለሁ ማሂን በድዬዋለሁ ብለሽ እንደማታለቅሽ..>>
<<ማሂ ጭራሽ ከአዕምሮዬ በላይ ሆንክብኝ እኮ። ያልከኝን ሁሉ አደርጋለሁ ግን በጣም ይ.ቅ.ር.ታ...ስለሁሉም>> ድምፄ ታፈነ ማውራት እየፈለኩ ግን አንደበቴ ተሳሰረ። ከሚቆራረጠው ትንፋሼ በቀር ..
<<ማ.ማማ..ሂ.እኔ... >> ወደኔ ተጠጋ ሊያባብለኝ ሞከረ፤ ግን አልሆነለትም። ዕንባዎቹ እየተሽቀዳደሙ መሰለኝ። ለመጥረግ ብሞክርም እንደ አዲስ የሚፈሱት እጄን አረጠቡት። እንደ ትኩስ ውሃ ቢያቃጥለኝ፤ ልቤ ከሚለበልበው ህመሜ በላይ የሱ ሲቃ ገዘፈብኝ። እጄን ከፊቱ ላይ አወረዳቸው ወደ ጆሮዬ ተጠጋ።
<<ኢብቲ እኔ ከአሁን በኃላ የለሁም። ስለኔ ብለሽ ሌሎች ማሂሮችን እርጂያቸው ስለኔ ስታለቅሺ ከዚህ በላይ ማየት አልችልም>> ለመጨረሻ ጊዜ ከማሂ የወጡ ቃላት ነበሩ። ማሂ እያየሁት በምን ፍጥነት በር ጋር እንደ ደረሰ እኔንጃ ብቻ በር ጋር ሲደርስ አንዴ ዞር ብሎ አይቶኝ ከአይኔ ሸሸ።
.
ከደቂቃዎች ቡኃላ ተረጋጋሁና አካባቢዬን አስተዋልኩ፤ ጠረዼዛው ላይ ማሂ ሂሳብ አስቀምጧል በኩባያ ሙሉ ወተት አለ። ማሂ ከተቀመጠበት ወንበር ላይ ውሃ ሰማያዊ ጂንስ ጃኬት አለ አንስቼ ያዝኩት፤ የማሂሬ ነበር። ለትናንቱ ህመሜ ዛሬ ማስታገሻ አጊቻለሁ...ትናንት ላይ የባከኑት ቀናት ዛሬ ላይ ዋጋ አስከፍለውኛል ያውም በማሂሬ!
.
ሁላችንም ውስጥ ትላንት አለ፤ ትናንታችን ውስጥ ደግሞ ስህተቶች አሉ፡፡ ምናልባት የኛ ምናልባትም ደግሞ በህይወታችን ዉስጥ የገባ የሌላ ሰው ስህተት አለ፡፡ ከትላንት ስህተታችን ለመታረም መቁረጥ አለብን፡፡ እኛ ህይወት ውስጥ ስህተት የሚፈጠረው በአንድም ይሁን በሌላ መልኩ በእኛ ምክንያት ነው፡፡ ባለማወቅ ሰዎችን ብዙ ጎድተና፤ እንዲያዝኑ አድርገናል፤ በእርግጥ ሰዎችን ከልክ በላይ የሆነ ቦታ እንዲሰጡን የሚያደርጉ ነገሮች አሉ፡፡ ግና ትክክል ነው ብለው አውቀውም ሆነ ሳያውቁ የነሱን የህይወት ፈተና ማለፊያ ያደርጉናል... አልያም እናደርጋቸዋለን፡፡ ይሁና.......! ሁሉም በየራሱ መንገድ ትክክል ነው፡፡ በቃ...አሁን ዛሬ ላይ ነን። ምናልባት ነገ ብለን ትናንት ተስፋ ያደረግነው ነገር ዛሬ ላይ ፀፀት ሆኖ ይሆናል፤ ግን አልፎዋል አራት ነጥብ፡፡ ያ ሁሉ ተስፋ፣ ፍቅር፣ እምነት፣ ስህተት ....በቃ ሁሉም ትላንት ነው፡፡ ዛሬ ሌላ ቀን ነው! አዲስ ከስህተት ተምረን የምንለወጥበት ባለፉ ስህተቶች ድጋሚ የማናልፍበት። ሌላ ከኖርነው እድሜ ላይ የተጨመረችልን ልዩ ቀን። ያለፈው ይሁና.......! ይሄን ሁሉ አልፈን እንድንቆም ለረዳን አላህ ምስጋና አቅርበን ነጋችንን የምንስልባት ባለ ፀሀይ ቀን፡፡ እርግጠኛ ነኝ ነገ ከትላንት ይሻላል፡፡ የሄደው ነገር ሁሉ ለመልካም ነው፡፡ ዛሬዬን ያዘጋጀልኝ ጌታዬ ነገዬን የተሻለ እንደሚያደርግልኝ አምናለው፡፡ ምናልባት አልሄድንም ይሆናል ፤ አልመጣንም ይሆናል ፤ ግን ፈቀቅ ብለናል ፡፡
ቅድም ማሂ በሰጠኝ ወረቀት ጀርባ መሞነጫጨር ጀመርኩ... ምን አልባትም ለማሂ የፃፍኩት የመጨረሻ ቃላቶቼ ናቸው።

#ግራጫ_ቀናቶች
~~~~
ጣዕም የለሽ ህይወት
ትርጉም አልባ ኑሮ ፤
ቀንም ሆነ ምሽት
የሳግ እንጉርጉሮ ፡፡
በጥቁር ደመና
እንባን ያቀረሩ ፤
በሳቅ በትወና
ባዷቸውን የቀሩ ፤
ወይ ከነጭ አልሆኑ
ወይ ደግሞ ከጥቁሩ ፤
ብዙ ቀኖች አሉኝ
በመሃል የቀሩ ፡፡

የፃፍኩትን ወረቀት ሳጣጥፍ ከጀርባው ሌላ ፁሁፍ በትናንሹ ተፅፎ አይሁ ለማንበብ ወረቀቱን ዘረጋሁትና ማሂ እንዳለኝ በአትኩሮት ለማንበብ ራሴን አብሰብ አደረኩ።
❝ግን በመሄድና በመምጣት የጊዜ ርዝማኔ ውስጥ የተስፋ ስብራቶች፣የልብ ቁስሎች ፣ የአእምሮ መላሸቆች ስንት ይሆኑ...? ባለመኖር እውነታ ውስጥ ስንት የመኖር ህልም ይሞት ይሆን.....? በትናንት ህመም ውስጥ ስንት ዛሬዎች ባከኑ፤ የነገ ህልሞች ደቀቁ............❞
አንብቤ ስጨርስ እንደ ጀት ቅርፅ ሰራሁበት ከካፌው እንደወጣሁ ወደ ሰማዩ ለቀኩት..በአንዱ መስመር ሲሄድ እኔ በሌላኛው መስመር ሄድኩ ....

ተፈፀመ
••••••
www.tgoop.com/Habibacalligraphy



tgoop.com/Habibacalligraphy/1960
Create:
Last Update:

የባከኑ ቀናት
ክፍል አስራ አምስት
(የመጨረሻው ክፍል)
(ሂባ ሁዳ)
.
.
ዝምታው ያስፈራል፤ ረጅም ደቂቃ ዝም አለ።
<<ማሂ እሺ አሁንስ?>>
<<አሁንማ... አሁንማ ኢብቲ...ተስፋ የቆረጠ ሰው አታውቂም?...ራሱን የጠላ ሰው?... መኖር የሰለቸው? ....እየኖረ የሞተ?.... ህልሙን ቅዠት የሆነበት?... ከራሱ ርቆ በሌሎች የተደበቀ.... ልቡን ላለማድመጥ ጩኸት የሚፈጥር?... ከኑሮ ለመሸሽ በጪስ የተወሸቀ?...ኢብቲ ከፊትሽ ያለው ለሴቶች ክብር ብሎ የሚጣላው ማሂር እኮ አይደለም። የሴቶችን ክብር የሚወስድ እንጂ..>> ድምፁ በሲቃ ታፈነ አይኖቹ መሸከም ያልቻሉትን ዕንባዎች ሲለቋቸው ቁልቁል ፈሰሱ። ከዚህ በላይ ራሴን መቆጣጠር አልቻልኩም። ድንዝዝ ያሉት እጆቼ ዕንባዬን መጥረግ ተሳናቸው። ምንም ቃል መናገር አልቻልኩም የማሂ ዕንባ እያይሁ ከማንባት ውጪ።
እንደምንም ራሱን አረጋግቶ ግንባሩን በሁለት እጆቹ ደጋፍ አደረገ
<<ኢ.ብ..ቲ>> ድምፁ መቆራረጥ ጀመረ። <<አ.ል.ች.ል.ም እንዲህ መኖር አህ.ህ.ህ>> እጆቹ እንደመንቀጥቀጥ አደረጋቸው።
<<ማሂሬ ደና ነህ?>> በጣም ደንግጫለው አይኑን ይጨፍናል መልሶ ይገልጣል ..
<<ማሂ ማሂሬ?>>ድምፁ ጠፋብኝ
<<ትንሽ ደቂቃ ብቻ... ይ.ተ.ወ.ኛ.ል ..>>
.
<<ኢብቲ አየሽ አይደል እዚህ ድረስ ነኝ.. በሰዐቱ ካልተጠቀምኩ እንዲህ ነው የሚያደርገኝ መውጣት ማልችለው ሱስ ውስጥ ወድቄያለሁ። ኢብቲ ከዚህ ቡኃላ የኔ የምለው ምንም አይነት ነገር የለኝም፤ የኔ ቀርቶ እኔም አልኖርም። እኔ እኮ አሁን አንቺን ማግኘቴ ደስ ብሎኛል። ቢያንስ እንደኔ ሌላ ሰው ሰው በማጣት የህልሙ ብርሃን ጭላንጭል ሲሆን... ጭላንጭሉን ወደ ብርሃን እንዲቀየር እንደምታግዥው ለራሴ ቃል ትገቢልኛለሽ። ከአሁን በኃላ ሰሚ ላጡ አባሽ ለሚፈልጉ ዕንባዎች እንደ አሁኑ አብረሻቸው ከማልቀስ ይልቅ መፍትሄ እንደምታመጪላቸው እንድትነግሪኝ እፈልጋለሁ። ኢብቲ ያለፈው ፀፅቶሻል? ጎድቶሻል አይደል? በሌሌች አስተካኪው። ከመስማት ማድመጥን ልመጂ። ማየት ብቻ ሣይሆን በመመልከት አስተውዪ ...>>
<<ማሂሬ እንዴት ልቻለው? ይሄን ሁሉ ከመሆኑ በፊት እኮ..ማሂ ይሄ ሁሉ በኔ እኮ ነው! ራሴን ምን ብዬ ላሳምነው?>> ከዚህ በላይ ማውራት አልቻልኩም ስቅስቅ ብዬ ከማልቀስ ውጪ።
<<ኢብቲ ነገርኩሽ እኮ... በቃ ያለፈ ታሪክ ነው። ያገኘሁሽ ሁላ በኔ ምክንያት መጨነቅሽን ትተሽ ሰላምሽን እንድታገኚ ነው።>>
<<ማሂ ለዚህ ሁሉ ስህተት ምንድነው ይቅርታው?>>
<<ኢብቲዬ ማርፈድ ከትምህርት ቤት ይልቅ ህይወት ላይ ዋጋ ያስከፍላል። በኔ ህይወት አንቺ አልዘገየሽም፤ እኔ ቸኮልኩ እንጂ.. እኔን እርሺኝ ከአሁን በኃላ የሚመጡትን ማሂሮችን እርጂያቸው። ከዚህ በላይ ስታለቅሺ የማየት አቅሙ የለኝም። ማንም አንቺን ባያስከፋሽ ምኞቴ ነው። በኔ ምክንያት እንድታለቅሺ ከቶ አይቻለኝም። ቃል እንድትሰጭኝ ፈልጋለሁ ማሂን በድዬዋለሁ ብለሽ እንደማታለቅሽ..>>
<<ማሂ ጭራሽ ከአዕምሮዬ በላይ ሆንክብኝ እኮ። ያልከኝን ሁሉ አደርጋለሁ ግን በጣም ይ.ቅ.ር.ታ...ስለሁሉም>> ድምፄ ታፈነ ማውራት እየፈለኩ ግን አንደበቴ ተሳሰረ። ከሚቆራረጠው ትንፋሼ በቀር ..
<<ማ.ማማ..ሂ.እኔ... >> ወደኔ ተጠጋ ሊያባብለኝ ሞከረ፤ ግን አልሆነለትም። ዕንባዎቹ እየተሽቀዳደሙ መሰለኝ። ለመጥረግ ብሞክርም እንደ አዲስ የሚፈሱት እጄን አረጠቡት። እንደ ትኩስ ውሃ ቢያቃጥለኝ፤ ልቤ ከሚለበልበው ህመሜ በላይ የሱ ሲቃ ገዘፈብኝ። እጄን ከፊቱ ላይ አወረዳቸው ወደ ጆሮዬ ተጠጋ።
<<ኢብቲ እኔ ከአሁን በኃላ የለሁም። ስለኔ ብለሽ ሌሎች ማሂሮችን እርጂያቸው ስለኔ ስታለቅሺ ከዚህ በላይ ማየት አልችልም>> ለመጨረሻ ጊዜ ከማሂ የወጡ ቃላት ነበሩ። ማሂ እያየሁት በምን ፍጥነት በር ጋር እንደ ደረሰ እኔንጃ ብቻ በር ጋር ሲደርስ አንዴ ዞር ብሎ አይቶኝ ከአይኔ ሸሸ።
.
ከደቂቃዎች ቡኃላ ተረጋጋሁና አካባቢዬን አስተዋልኩ፤ ጠረዼዛው ላይ ማሂ ሂሳብ አስቀምጧል በኩባያ ሙሉ ወተት አለ። ማሂ ከተቀመጠበት ወንበር ላይ ውሃ ሰማያዊ ጂንስ ጃኬት አለ አንስቼ ያዝኩት፤ የማሂሬ ነበር። ለትናንቱ ህመሜ ዛሬ ማስታገሻ አጊቻለሁ...ትናንት ላይ የባከኑት ቀናት ዛሬ ላይ ዋጋ አስከፍለውኛል ያውም በማሂሬ!
.
ሁላችንም ውስጥ ትላንት አለ፤ ትናንታችን ውስጥ ደግሞ ስህተቶች አሉ፡፡ ምናልባት የኛ ምናልባትም ደግሞ በህይወታችን ዉስጥ የገባ የሌላ ሰው ስህተት አለ፡፡ ከትላንት ስህተታችን ለመታረም መቁረጥ አለብን፡፡ እኛ ህይወት ውስጥ ስህተት የሚፈጠረው በአንድም ይሁን በሌላ መልኩ በእኛ ምክንያት ነው፡፡ ባለማወቅ ሰዎችን ብዙ ጎድተና፤ እንዲያዝኑ አድርገናል፤ በእርግጥ ሰዎችን ከልክ በላይ የሆነ ቦታ እንዲሰጡን የሚያደርጉ ነገሮች አሉ፡፡ ግና ትክክል ነው ብለው አውቀውም ሆነ ሳያውቁ የነሱን የህይወት ፈተና ማለፊያ ያደርጉናል... አልያም እናደርጋቸዋለን፡፡ ይሁና.......! ሁሉም በየራሱ መንገድ ትክክል ነው፡፡ በቃ...አሁን ዛሬ ላይ ነን። ምናልባት ነገ ብለን ትናንት ተስፋ ያደረግነው ነገር ዛሬ ላይ ፀፀት ሆኖ ይሆናል፤ ግን አልፎዋል አራት ነጥብ፡፡ ያ ሁሉ ተስፋ፣ ፍቅር፣ እምነት፣ ስህተት ....በቃ ሁሉም ትላንት ነው፡፡ ዛሬ ሌላ ቀን ነው! አዲስ ከስህተት ተምረን የምንለወጥበት ባለፉ ስህተቶች ድጋሚ የማናልፍበት። ሌላ ከኖርነው እድሜ ላይ የተጨመረችልን ልዩ ቀን። ያለፈው ይሁና.......! ይሄን ሁሉ አልፈን እንድንቆም ለረዳን አላህ ምስጋና አቅርበን ነጋችንን የምንስልባት ባለ ፀሀይ ቀን፡፡ እርግጠኛ ነኝ ነገ ከትላንት ይሻላል፡፡ የሄደው ነገር ሁሉ ለመልካም ነው፡፡ ዛሬዬን ያዘጋጀልኝ ጌታዬ ነገዬን የተሻለ እንደሚያደርግልኝ አምናለው፡፡ ምናልባት አልሄድንም ይሆናል ፤ አልመጣንም ይሆናል ፤ ግን ፈቀቅ ብለናል ፡፡
ቅድም ማሂ በሰጠኝ ወረቀት ጀርባ መሞነጫጨር ጀመርኩ... ምን አልባትም ለማሂ የፃፍኩት የመጨረሻ ቃላቶቼ ናቸው።

#ግራጫ_ቀናቶች
~~~~
ጣዕም የለሽ ህይወት
ትርጉም አልባ ኑሮ ፤
ቀንም ሆነ ምሽት
የሳግ እንጉርጉሮ ፡፡
በጥቁር ደመና
እንባን ያቀረሩ ፤
በሳቅ በትወና
ባዷቸውን የቀሩ ፤
ወይ ከነጭ አልሆኑ
ወይ ደግሞ ከጥቁሩ ፤
ብዙ ቀኖች አሉኝ
በመሃል የቀሩ ፡፡

የፃፍኩትን ወረቀት ሳጣጥፍ ከጀርባው ሌላ ፁሁፍ በትናንሹ ተፅፎ አይሁ ለማንበብ ወረቀቱን ዘረጋሁትና ማሂ እንዳለኝ በአትኩሮት ለማንበብ ራሴን አብሰብ አደረኩ።
❝ግን በመሄድና በመምጣት የጊዜ ርዝማኔ ውስጥ የተስፋ ስብራቶች፣የልብ ቁስሎች ፣ የአእምሮ መላሸቆች ስንት ይሆኑ...? ባለመኖር እውነታ ውስጥ ስንት የመኖር ህልም ይሞት ይሆን.....? በትናንት ህመም ውስጥ ስንት ዛሬዎች ባከኑ፤ የነገ ህልሞች ደቀቁ............❞
አንብቤ ስጨርስ እንደ ጀት ቅርፅ ሰራሁበት ከካፌው እንደወጣሁ ወደ ሰማዩ ለቀኩት..በአንዱ መስመር ሲሄድ እኔ በሌላኛው መስመር ሄድኩ ....

ተፈፀመ
••••••
www.tgoop.com/Habibacalligraphy

BY Habiba Calligraphy




Share with your friend now:
tgoop.com/Habibacalligraphy/1960

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

To edit your name or bio, click the Menu icon and select “Manage Channel.” Telegram is a leading cloud-based instant messages platform. It became popular in recent years for its privacy, speed, voice and video quality, and other unmatched features over its main competitor Whatsapp. With Bitcoin down 30% in the past week, some crypto traders have taken to Telegram to “voice” their feelings. How to Create a Private or Public Channel on Telegram? Concise
from us


Telegram Habiba Calligraphy
FROM American