tgoop.com/Hulaadiss/38485
Last Update:
በኢትዮጵያ ታዳጊ ሴቶች የመጀመሪያ የግብረ ስጋ ግንኙነት በ17 ዓመት የእድሜ ክልል ውስጥ እንደሚፈፅሙ ተነገረ
በኢትዮጵያ የመጀመሪያ የግብረ ስጋ ግንኙነት አማካይ እድሜ ላይ መሻሻሎች ቢኖሩም በአሁኑ ሰአት በ17 አመት እድሜ ውስጥ ያሉ ኢትዮጵያውያን ሴቶች የመጀመሪያ የግብረ ስጋ ግንኙነትን እንደሚፈፅሙ ተነግሯል።
በአዲስ አበባ ዮኒቨርሲቲ የስኩል ኦፍ ፐብሊክ ሄልዝ መምህር አቶ አሰፋ ስሜ ለብስራት ሬዲዮና ቴሌቪዥን እንደተናገሩት ጉዳዮን አስመልክቶ በፈረንጆቹ አቅጣጠር 2021 ላይ በፒ.ኤም.ኤ ኢትዮጵያ አማካኝነት የዳሰሳ ጥናት ተደርጓል።
ጥናቱ በገጠርና በከተማ መካሄዱን የገለፁት አቶ አሰፋ ከ25 እስከ 29 ፣ ከ30 እስከ 34 እንዲሁም ከ35 እስከ 39 የእድሜ ክልል ውስጥ ያሉ ሴቶች ላይ ትኩረት በማድረግ ተጠንቷል ብለዋል።
በጥናቱ መሰረት ከከተማ ይልቅ የገጠር ሴቶች የመጀመሪያ ወሲብ የመፈፀሚያ እድሜ እንደሚቀንስ የተገለፀ ሲሆን እድሜያቸው ከ35 እስከ 39 ያሉ እናቶች ቀደም ብለው የመጀመሪያ የወሲብ ግንኙነትን ስለመፈፀማቸው ተገልጻል።የግዳጅ ጋብቻ መኖር በገጠር የሚኖሩ ሴቶች ቀድመው የመጀመሪያ ወሲብን እንዲፈፅሙ ያደረገ ዋነኛው ምክንያት እንደሆነ ተነግሯል።
ቀደም ባሉት ጊዜያት የነበሩ እናቶች በ16 አመት እድሜ ላይ እያሉ ይህንን ተግባራዊ ያደርጉ እንደነበር አቶ አሰፋ የገለፁ ሲሆን በአሁኑ ወቅት ግን በ17 አመት እድሜ ክልል ውስጥ የመጀመሪያ ጊዜ የወሲብ ግንኙነትን ይፈፅማሉ ብለዋል።
ይህም የመጀመሪያ ጊዜ ወሲብ መዘግየትን ያሳያል በማለት ተናግረው፤ ሴቶች በበሰለ እድሜ ላይ ሆነው ከጋብቻና ከልጆች ፍላጎት ጋር በተገናኘ መወሰን እንዲችሉ ጠቀሜታው የጎላ ነው ሲሉ አስረድተዋል።
የቤተሰብ እቅድ ምጣኔን አስመልክቶ እድሜዋ ከ35 እስከ 39 ያለች አንዲት የገጠር ሴት በ 26 አመት እድሜ እያለች ትጠቀም እንደነበር በማስታወስ አሁን ላይ በ20ዎቹ እድሜ ውስጥ ተግባራዊ እያደረገች እንደምትገኝ ተጠቅሷል።ይህም ለውጥ የመጣው በሴቶች ዘንድ ያለው ግንዛቤ በማደጉ እና የእርግዝና መከላከያ አቅርቦት በመሻሻሉ ነው ተብሏል።
በቅድስት ደጀኔ
BY Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)
Share with your friend now:
tgoop.com/Hulaadiss/38485