tgoop.com/Hulaadiss/38491
Last Update:
‹‹አቡበከር ናስር የት እንዳለ አላውቅም›› ሲሉ የክለቡ አሰልጣኝ ተናገሩ፡፡ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን አጥቂ የነበረው አቡበከር ናስር የዛሬ ሶስት አመት ከኢትዮጵያ ቡና ወደደቡብ አፍሪካው ማሜሎዲ ሰንዳውንስ ክለብ መዘዋወሩ ይታወሳል፡፡
ይህ የሀያ አራት አመቱ ተጨዋች ለአዲሱ ክለቡ አስራ ዘጠኝ ጊዜ ከተሰለፈና አራት ጎሎችን ካስቆጠረ በኋላ ባጋጠመው ጉዳት የተነሳ ለበርካታ ጊዜያት ተቀያሪ ወንበር ላይ ለመቀመጥ ተገዷል፡፡ ይሁንና ከወራት በፊት ሰንዳውንስ በዚያው ደቡብ አፍሪካ ለሚገኝ ክለብ ለአንድ አመት በውሰት ሰጥቶት ነበር፡፡
አቡበከር ናስርም ሱፐርስፖርትስ ለተሰኘው ክለብ ለመጫወት በጥቅምት ወር የፈረመ ሲሆን በጉዳቱ በማገገሙ ለአዲሱ ክለቡ ጥሩ አስተዋፅኦ እንደሚያደርግ ተስፋ ተጥሎበት እንደነበር ጎል ዶት ኮም ገልጿል፡፡ ይሁንና ተጨዋቹ አሁን በክለቡ ውስጥ ሲሰለፍ አለመታየቱን ተከትሎ ጎል ዶት ኮም አሰልጣኙን ጠይቋል፡፡
የሱፐር ስፖርት አሰልጣኝ የሆኑት ጋቪን ሀንት ሲመልሱም ‹‹አቡበከር አሁን የት እንዳለ አላውቅም፡፡ ላለፉት ሁለት ሳምንታት አይቼው አላውቅም›› ካሉ በኋላ የልምምድ ቦታ ላይ መገኘት ማቆሙን አስረድተዋል፡፡ ተጨዋቹ ክለቡን በተቀላቀለባቸው አራት ወራት ውስጥ ያለፈቃድ ጥሎ እየጠፋ በተደጋጋሚ እንዳስቸገራቸውም ገልፀዋል፡፡ እንደጎል ዶት ኮም ዘገባ አሰልጣኙ በዚህ የተነሳ አቡበከርን ወደቀድሞ ክለቡ ማሜሎዲ ሰንዳውንስ የመመለስ ሀሳብ አላቸው፡፡
አቡበከር በጉዳዩ ላይ የሰጠው አስተያየት የለም።
BY Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)
Share with your friend now:
tgoop.com/Hulaadiss/38491