HULAADISS Telegram 38575
ኬንያ በኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ላይ ያነጣጠረ ወታደራዊ ዘመቻ መጀመሯን አስታወቀች!

ኬንያ ከኢትዮጵያ ጋር በምትዋሰንበት የድንበር ግዛቶቿ ላይ ባሉ የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ላይ ያነጣጠረ ወታደራዊ ዘመቻ መጀመሯን አስታወቀች።የኬንያ መንግሥት የጦሩ አባላት ተደብቀውባቸዋል ባላቸው የማርሳቤት እና ኢሲዮሎ ግዛቶች ላይ "ወንጀለኞችን የማስወገድ" የተሰኘ ከፍተኛ የጸጥታ ዘመቻ ባለፈው ወር ጥር፣ 25/ 2017 ዓ.ም መጀመሩን ገልጿል።

እነዚህ ግዛቶችን "ድንበር ዘለል የወንጀል ድርጊቶችን ለማሳለጥ የሚጠቀምባቸው ናቸው" ሲል የኬንያ መንግሥት ብሔራዊ የፖሊስ አገልግሎት ሰኞ ጥር፣ 26/ 2017 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ ቡድኑን ወንጅሎታል።የኢትዮጵያ መንግሥት በተለያዩ ጥሰቶች የሚወነጅለው "ሸኔ" እያለ የሚጠራው የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት በኬንያ ግዛቶች ውስጥም ህገወጥ የማዕድን ማውጣትን ጨምሮ ሌሎች ጥሰቶች እየፈጸመ ነው ኬንያ ወንጅላለች።

የኬንያ ብሔራዊ ፖሊስ ቡድኑ "በተለያዩ ህገወጥ የጦር መሳሪያ፣ አደንዛዥ ዕጾች ዝውውር፣ ህገወጥ የማዕድን ማውጣት ህገወጥ የሰዎች ዝውውር ንግድ ተሰማርቶ ይገኛል" ብሎታል በመግለጫው።የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት "ለገንዘብ ሲል እገታዎችን በመፈጸም እንዲሁም ድንበር ዘለል ወረራዎችን በማካሄድ እና በጎሳዎች መካከል ግጭቶች እንዲቀሰቀሱ በማድረግ ለኬንያ የብሔራዊ ደህንነት ከፍተኛ ስጋት" ሆኗል ሲል መግለጫው አስፍሯል።

የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት በበኩሉ ቡድኑን መወንጀል አዲስ ነገር እንዳልሆነ ጠቅሶ በዘረፋዎችም ሆነ በህገወጥ ተግባራት እንዳልተሳተፈ እና "ለፍትህ" የሚታገል ድርጅት መሆኑን ለቢቢሲ ገልጿል።"እንዲህ አይነት ጥሰቶችን የሚፈጽሙ አካላትን ከኬንያ መንግሥት ጋር በመተባባር እንደሚዋጉ" የጦሩ ዋና አዛዥ አማካሪ ጂሬኛ ጉዴታ ለቢቢሲ ተናግረዋል።

ኬንያ በታጣቂዎቹ ላይ የጀመረችው ዘመቻ ባለፈው ወር የኢትዮጵያ ብሔራዊ መረጃ እና ደኅንነት አገልግሎት ዳይሬክተር ጄኔራል አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ወደ ኬንያ ተጉዘው ከአገሪቱ ፕሬዚዳንት ዊልያም ሩቶ ጋር ከተነጋገሩ በኋላ ነው።በውይይቱ ላይ የኬንያው የብሔራዊ መረጃ አገልግሎት ዳይሬክተር ጄኔራል ኑረዲን ሐጂ ተገኝተው ነበር።

ታጣቂው ቡድን "በኬንያ ቦረና እና በኢትዮጵያ ኦሮሞ መካከል ያለውን የባህል ትስስር እንዲሁም ቅርብ ዝምድና በመጠቀም በማርሳቤት እና ኢሶዮሎ ግዛቶች ውስጥ ባሉ ህዝቦች መካከል ሰርጎ በመግባት በድንበር አካባቢ በሚኖሩ ማህበረሰቦች ላይ ጥሰቶችን" እየፈጸመ ይገኛል ብሎታል የኬንያ ፖሊስ መግለጫ።

መግለጫው አክሎም "ቡድኑ በሴቶች እና በታዳጊዎች ላይ ወሲባዊ ጥቃቶችን ጨምሮ ማስፈራራት፣ በኃይል ንብረትን መውሰድ በአካባቢው በመፈጸሙ ማህበረሰቡን ለሰቆቃ ዳርጎታል" ብሏል።

ህይወትን፣ ንብረትን እንዲሁም ሰላምን ለማስጠበቅ በግዛቲቱ ተደብቀው የሚገኙ "የኦሮሞ ነጻነት ወንጀለኞችን ለማስወገድ" የኬንያ ብሔራዊ የፖሊስ አገልግሎት የወታደራዊ የመጀመሪያ ምዕራፍ ዘመቻ በይፋ መጀመሩን የአገሪቱ ፖሊስ ምክትል ዋና አዛዥ ጊልበርት ማንጊሲ እንዲሁም የወንጀል ምርመራ አገልግሎት ዳይሬክተር መሀመድ አሚን በትናንትናው ዕለት ገልጸዋል።

Via BBC



tgoop.com/Hulaadiss/38575
Create:
Last Update:

ኬንያ በኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ላይ ያነጣጠረ ወታደራዊ ዘመቻ መጀመሯን አስታወቀች!

ኬንያ ከኢትዮጵያ ጋር በምትዋሰንበት የድንበር ግዛቶቿ ላይ ባሉ የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ላይ ያነጣጠረ ወታደራዊ ዘመቻ መጀመሯን አስታወቀች።የኬንያ መንግሥት የጦሩ አባላት ተደብቀውባቸዋል ባላቸው የማርሳቤት እና ኢሲዮሎ ግዛቶች ላይ "ወንጀለኞችን የማስወገድ" የተሰኘ ከፍተኛ የጸጥታ ዘመቻ ባለፈው ወር ጥር፣ 25/ 2017 ዓ.ም መጀመሩን ገልጿል።

እነዚህ ግዛቶችን "ድንበር ዘለል የወንጀል ድርጊቶችን ለማሳለጥ የሚጠቀምባቸው ናቸው" ሲል የኬንያ መንግሥት ብሔራዊ የፖሊስ አገልግሎት ሰኞ ጥር፣ 26/ 2017 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ ቡድኑን ወንጅሎታል።የኢትዮጵያ መንግሥት በተለያዩ ጥሰቶች የሚወነጅለው "ሸኔ" እያለ የሚጠራው የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት በኬንያ ግዛቶች ውስጥም ህገወጥ የማዕድን ማውጣትን ጨምሮ ሌሎች ጥሰቶች እየፈጸመ ነው ኬንያ ወንጅላለች።

የኬንያ ብሔራዊ ፖሊስ ቡድኑ "በተለያዩ ህገወጥ የጦር መሳሪያ፣ አደንዛዥ ዕጾች ዝውውር፣ ህገወጥ የማዕድን ማውጣት ህገወጥ የሰዎች ዝውውር ንግድ ተሰማርቶ ይገኛል" ብሎታል በመግለጫው።የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት "ለገንዘብ ሲል እገታዎችን በመፈጸም እንዲሁም ድንበር ዘለል ወረራዎችን በማካሄድ እና በጎሳዎች መካከል ግጭቶች እንዲቀሰቀሱ በማድረግ ለኬንያ የብሔራዊ ደህንነት ከፍተኛ ስጋት" ሆኗል ሲል መግለጫው አስፍሯል።

የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት በበኩሉ ቡድኑን መወንጀል አዲስ ነገር እንዳልሆነ ጠቅሶ በዘረፋዎችም ሆነ በህገወጥ ተግባራት እንዳልተሳተፈ እና "ለፍትህ" የሚታገል ድርጅት መሆኑን ለቢቢሲ ገልጿል።"እንዲህ አይነት ጥሰቶችን የሚፈጽሙ አካላትን ከኬንያ መንግሥት ጋር በመተባባር እንደሚዋጉ" የጦሩ ዋና አዛዥ አማካሪ ጂሬኛ ጉዴታ ለቢቢሲ ተናግረዋል።

ኬንያ በታጣቂዎቹ ላይ የጀመረችው ዘመቻ ባለፈው ወር የኢትዮጵያ ብሔራዊ መረጃ እና ደኅንነት አገልግሎት ዳይሬክተር ጄኔራል አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ወደ ኬንያ ተጉዘው ከአገሪቱ ፕሬዚዳንት ዊልያም ሩቶ ጋር ከተነጋገሩ በኋላ ነው።በውይይቱ ላይ የኬንያው የብሔራዊ መረጃ አገልግሎት ዳይሬክተር ጄኔራል ኑረዲን ሐጂ ተገኝተው ነበር።

ታጣቂው ቡድን "በኬንያ ቦረና እና በኢትዮጵያ ኦሮሞ መካከል ያለውን የባህል ትስስር እንዲሁም ቅርብ ዝምድና በመጠቀም በማርሳቤት እና ኢሶዮሎ ግዛቶች ውስጥ ባሉ ህዝቦች መካከል ሰርጎ በመግባት በድንበር አካባቢ በሚኖሩ ማህበረሰቦች ላይ ጥሰቶችን" እየፈጸመ ይገኛል ብሎታል የኬንያ ፖሊስ መግለጫ።

መግለጫው አክሎም "ቡድኑ በሴቶች እና በታዳጊዎች ላይ ወሲባዊ ጥቃቶችን ጨምሮ ማስፈራራት፣ በኃይል ንብረትን መውሰድ በአካባቢው በመፈጸሙ ማህበረሰቡን ለሰቆቃ ዳርጎታል" ብሏል።

ህይወትን፣ ንብረትን እንዲሁም ሰላምን ለማስጠበቅ በግዛቲቱ ተደብቀው የሚገኙ "የኦሮሞ ነጻነት ወንጀለኞችን ለማስወገድ" የኬንያ ብሔራዊ የፖሊስ አገልግሎት የወታደራዊ የመጀመሪያ ምዕራፍ ዘመቻ በይፋ መጀመሩን የአገሪቱ ፖሊስ ምክትል ዋና አዛዥ ጊልበርት ማንጊሲ እንዲሁም የወንጀል ምርመራ አገልግሎት ዳይሬክተር መሀመድ አሚን በትናንትናው ዕለት ገልጸዋል።

Via BBC

BY Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)


Share with your friend now:
tgoop.com/Hulaadiss/38575

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

During the meeting with TSE Minister Edson Fachin, Perekopsky also mentioned the TSE channel on the platform as one of the firm's key success stories. Launched as part of the company's commitments to tackle the spread of fake news in Brazil, the verified channel has attracted more than 184,000 members in less than a month. Telegram Android app: Open the chats list, click the menu icon and select “New Channel.” With the administration mulling over limiting access to doxxing groups, a prominent Telegram doxxing group apparently went on a "revenge spree." As of Thursday, the SUCK Channel had 34,146 subscribers, with only one message dated August 28, 2020. It was an announcement stating that police had removed all posts on the channel because its content “contravenes the laws of Hong Kong.” According to media reports, the privacy watchdog was considering “blacklisting” some online platforms that have repeatedly posted doxxing information, with sources saying most messages were shared on Telegram.
from us


Telegram Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)
FROM American