KALTUBE Telegram 11380
በክርስቶስ IN CHRIST
ክፍል 40

        የወንጌል ኃይል
የተበተኑትም ቃሉን እየሰበኩ ዞሩ።ፊልጶስም ወደ ሰማርያ ከተማ ወርዶ ክርስቶስን ሰበከላቸው። ሕዝቡም የፊልጶስን ቃል በሰሙ ጊዜ ያደርጋት የነበረውንም ምልክት ባዩ ጊዜ፥ የተናገረውን በአንድ ልብ አደመጡ። ርኵሳን መናፍስት በታላቅ ድምፅ እየጮኹ ከብዙ ሰዎች ይወጡ ነበርና፤ ብዙም ሽባዎችና አንካሶች ተፈወሱ፤ በዚያችም ከተማ ታላቅ ደስታ ሆነ። ሲሞን የሚሉት አንድ ሰው ግን፦ “እኔ ታላቅ ነኝ፡” ብሎ፡ እየጠነቈለ የሰማርያንም ወገን እያስገረመ ቀድሞ በከተማ ነበረ። ከታናናሾችም ጀምሮ እስከ ታላላቆቹ ድረስ፦ “ታላቁ የእግዚአብሔር ኃይል ይህ ነው፡” እያሉ ሁሉ ያደምጡት ነበር። ከብዙ ዘመንም ጀምሮ በጥንቈላ ስላስገረማቸው ያደምጡት ነበር። ነገር ግን ስለ እግዚአብሔር መንግሥትና ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ ስም እየሰበከላቸው ፊልጶስን ባመኑት ጊዜ፥ ወንዶችም ሴቶችም ተጠመቁ። ሲሞንም ደግሞ ራሱ አመነ፤ ተጠምቆም ከፊልጶስ ጋር ይተባበር ነበር፤ የሚደረገውንም ምልክትና ታላቅ ተአምራት ባየ ጊዜ ተገረመ። ሐዋር 8:4-13

➢በሐዋርያት ዘመን ከእስጢፋኖስ ሞት በኋላ ቤተክርስቲያን በታላቅ ስደት ላይ ነበረች። ምንም እንኳን ሰደት ላይ ቢሆኑም ተሰደው በሄዱበት ሰማርያ ወንጌልን ይሰብኩ ነበር።

➢ከላይ በመግቢያ ጥቅሳችን ላይ እንዳነበብነው እውነተኛ ወንጌል በሚሰበክበት በየትኛውም ጊዜና ቦታ የእግዚአብሔር ኃይል ይገለጣል። ወንጌል ኃይል የታጠቀ የእግዚአብሔር መልእክት ነው።

➢ወንጌል ወደ ሰማርያ እስከደረሰበት ጊዜ ድረስ ሕዝቡ የእግዚአብሔር ኃይል እያለ አምኖ የተቀበለው የጥንቆላን ኃይል ነበር።ሲሞን የተባለው ጠንቋይ የሰማርያን ነዋሪዎች ከማስደነቅ አልፎ ታላቁ የእግዚአብሔር ኃይል ተብሎ ታምኖ ነበር።

ነገር ግን ፊልጶስ ወንጌል እየሰበከ ሲመጣ የእግዚአብሔር እውነተኛ ኃይል መገለጥ ጀመረ፣ የጥንቋላ አሰራር መፍረስ ጀመረ፣
ህዝቡን በተአምራት ሲያስደንቅ የነበረው ጠንቋይ ሲሞን እራሱ በእግዚአብሔር ኃይልና በፊልጶስ በሚደረገው ተአምራት መደመም ጀመረ። ይህ ብቻ አይደለም ደስታ ያጣችው   ሰማርያ ታላቅ ደስታ ሆነላት።

➢ወንጌል የትኛውንም ኃይል የሚሽር ፣የትኛውም ኃይል የማይቋቋመው የመለኮት ኃይል ነው።
➢የኛ የአማኞች ድርሻ ወንጌል መስበክ ነው።
ወንጌል መስበክ የሰይጣንን ስራ ያፈራርሳል የእግዚአብሔርን መንግስት ደግሞ ያስፋፋል።

➢ቤተክርስቲያን ምስባክ ላይ ሆነ በየትኛውም አጋጣሚ የቆጥ የባጡን ሳይሆን ወንጌል መስበክ አለባት።ወንጌል ኃይል አለው። ወንጌል ሲሰበክ ተአምራት በራሱ ጊዜ መከሰት ይጀምራል። ወንጌል ጠንካራና ድንጋይ ልቦችን  ያቀልጣል። ወንጌል በየትኛውም አመክንዮ የተወጠሩ ጭንቅላቶችን አሳምኖ ማሸነፍ ይችላል። ወንጌል ከተማን ይፈውሳል፣ወንጌል ማህበረሰብን ይለውጣል፣ ወንጌል ትውልድን ይባርካል።
ወንጌልን በቤተሰብ፣ በትምህርት ቤት፣በስራ ቦታ፣በየመንገዱ፣ በከተማ ፣በገጠር ባገኘነው አጋጣሚ ሁሉ  እንስበክ። በዚህ አጋጣሚ ወንጌል በመስበክ ላይ የተጠመዳችሁ ውድ የጌታ ልጆች ፀጋ ይብዛላችሁ።ተባረኩ!!

መሳይ አለማየሁ (ነቢይ)

ክፍል 41 ይቀጥላል

👇💐👇💐👇💐👇💐👇💐
            @KALTUBE
            @KALTUBE
            @KALTUBE



tgoop.com/KALTUBE/11380
Create:
Last Update:

በክርስቶስ IN CHRIST
ክፍል 40

        የወንጌል ኃይል
የተበተኑትም ቃሉን እየሰበኩ ዞሩ።ፊልጶስም ወደ ሰማርያ ከተማ ወርዶ ክርስቶስን ሰበከላቸው። ሕዝቡም የፊልጶስን ቃል በሰሙ ጊዜ ያደርጋት የነበረውንም ምልክት ባዩ ጊዜ፥ የተናገረውን በአንድ ልብ አደመጡ። ርኵሳን መናፍስት በታላቅ ድምፅ እየጮኹ ከብዙ ሰዎች ይወጡ ነበርና፤ ብዙም ሽባዎችና አንካሶች ተፈወሱ፤ በዚያችም ከተማ ታላቅ ደስታ ሆነ። ሲሞን የሚሉት አንድ ሰው ግን፦ “እኔ ታላቅ ነኝ፡” ብሎ፡ እየጠነቈለ የሰማርያንም ወገን እያስገረመ ቀድሞ በከተማ ነበረ። ከታናናሾችም ጀምሮ እስከ ታላላቆቹ ድረስ፦ “ታላቁ የእግዚአብሔር ኃይል ይህ ነው፡” እያሉ ሁሉ ያደምጡት ነበር። ከብዙ ዘመንም ጀምሮ በጥንቈላ ስላስገረማቸው ያደምጡት ነበር። ነገር ግን ስለ እግዚአብሔር መንግሥትና ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ ስም እየሰበከላቸው ፊልጶስን ባመኑት ጊዜ፥ ወንዶችም ሴቶችም ተጠመቁ። ሲሞንም ደግሞ ራሱ አመነ፤ ተጠምቆም ከፊልጶስ ጋር ይተባበር ነበር፤ የሚደረገውንም ምልክትና ታላቅ ተአምራት ባየ ጊዜ ተገረመ። ሐዋር 8:4-13

➢በሐዋርያት ዘመን ከእስጢፋኖስ ሞት በኋላ ቤተክርስቲያን በታላቅ ስደት ላይ ነበረች። ምንም እንኳን ሰደት ላይ ቢሆኑም ተሰደው በሄዱበት ሰማርያ ወንጌልን ይሰብኩ ነበር።

➢ከላይ በመግቢያ ጥቅሳችን ላይ እንዳነበብነው እውነተኛ ወንጌል በሚሰበክበት በየትኛውም ጊዜና ቦታ የእግዚአብሔር ኃይል ይገለጣል። ወንጌል ኃይል የታጠቀ የእግዚአብሔር መልእክት ነው።

➢ወንጌል ወደ ሰማርያ እስከደረሰበት ጊዜ ድረስ ሕዝቡ የእግዚአብሔር ኃይል እያለ አምኖ የተቀበለው የጥንቆላን ኃይል ነበር።ሲሞን የተባለው ጠንቋይ የሰማርያን ነዋሪዎች ከማስደነቅ አልፎ ታላቁ የእግዚአብሔር ኃይል ተብሎ ታምኖ ነበር።

ነገር ግን ፊልጶስ ወንጌል እየሰበከ ሲመጣ የእግዚአብሔር እውነተኛ ኃይል መገለጥ ጀመረ፣ የጥንቋላ አሰራር መፍረስ ጀመረ፣
ህዝቡን በተአምራት ሲያስደንቅ የነበረው ጠንቋይ ሲሞን እራሱ በእግዚአብሔር ኃይልና በፊልጶስ በሚደረገው ተአምራት መደመም ጀመረ። ይህ ብቻ አይደለም ደስታ ያጣችው   ሰማርያ ታላቅ ደስታ ሆነላት።

➢ወንጌል የትኛውንም ኃይል የሚሽር ፣የትኛውም ኃይል የማይቋቋመው የመለኮት ኃይል ነው።
➢የኛ የአማኞች ድርሻ ወንጌል መስበክ ነው።
ወንጌል መስበክ የሰይጣንን ስራ ያፈራርሳል የእግዚአብሔርን መንግስት ደግሞ ያስፋፋል።

➢ቤተክርስቲያን ምስባክ ላይ ሆነ በየትኛውም አጋጣሚ የቆጥ የባጡን ሳይሆን ወንጌል መስበክ አለባት።ወንጌል ኃይል አለው። ወንጌል ሲሰበክ ተአምራት በራሱ ጊዜ መከሰት ይጀምራል። ወንጌል ጠንካራና ድንጋይ ልቦችን  ያቀልጣል። ወንጌል በየትኛውም አመክንዮ የተወጠሩ ጭንቅላቶችን አሳምኖ ማሸነፍ ይችላል። ወንጌል ከተማን ይፈውሳል፣ወንጌል ማህበረሰብን ይለውጣል፣ ወንጌል ትውልድን ይባርካል።
ወንጌልን በቤተሰብ፣ በትምህርት ቤት፣በስራ ቦታ፣በየመንገዱ፣ በከተማ ፣በገጠር ባገኘነው አጋጣሚ ሁሉ  እንስበክ። በዚህ አጋጣሚ ወንጌል በመስበክ ላይ የተጠመዳችሁ ውድ የጌታ ልጆች ፀጋ ይብዛላችሁ።ተባረኩ!!

መሳይ አለማየሁ (ነቢይ)

ክፍል 41 ይቀጥላል

👇💐👇💐👇💐👇💐👇💐
            @KALTUBE
            @KALTUBE
            @KALTUBE

BY #KALTUBE


Share with your friend now:
tgoop.com/KALTUBE/11380

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

The initiatives announced by Perekopsky include monitoring the content in groups. According to the executive, posts identified as lacking context or as containing false information will be flagged as a potential source of disinformation. The content is then forwarded to Telegram's fact-checking channels for analysis and subsequent publication of verified information. The administrator of a telegram group, "Suck Channel," was sentenced to six years and six months in prison for seven counts of incitement yesterday. Telegram channels fall into two types: 3How to create a Telegram channel? 4How to customize a Telegram channel?
from us


Telegram #KALTUBE
FROM American