ZEPHILOSOPHY Telegram 1036
ቡድናዊነት በድናዊነት?
ብርሀን ደርበው

የምንከተለው ፋሽን፣ የሚያስቁን ቀልዶች የምንወዳቸው ሙዚቃዎች ወዘተ ወዘተ... እውን የወደድነው የምንወደውን ነው? የምናደርገው ሁሉ በራሳችን ውሳኔ እና ፍላጎት የተደረገ ወይስ ቀልብያችን የሚለን ሌላ ሆኖ አንዳች ኃይል አስገድዶን?

አንዳንዴ እራሴን እንዲህ ብዬ ጠይቃለሁ የምትከተለው ፋሽን የሚያስቁህ ቀልዶች የምትወዳቸው ሙዚቃዎች ወዘተ ወዘተ... ያንተ ምርጫ ወይስ አንዳች ኃይል አስገድዶህ ምትመርጠው? እውን የወደድከው ሁሉ የምትወደውን ነው? የምታደርጋቸው ውሳኔዎች ባንተ ፍላጎት በቀልብያህ ፍቃድ ወይስ ሌሎች ስለወደዱት ላለመነጠል በዓለም ውስጥ
መናኒ ላለመሆን?

Solomon Asch የተባለ ሳይኮሎጂስት Confirmity Line Experiment የምትባል የሰውን ልጅ ውሳኔ አሰጣጥ የምትገመግም አንዲት የምትገርም ጥናት አለችው። እነሆ ጥናቱ A,B,C ሲል የሰየማቸውን ሦስት የተለያየ ቁመት ያላቸው መስመሮች አዘጋጀ።

ተሳታፊዎች በተዘጋጀላቸው ክፍል ውስጥ ሁሉም በየተራ የትኛው መስመር ረዥም እንደሆነ ጮክ ብለው ይናገራሉ። ታድያ ይሄ ሁሉ ሲሆን ክፍሉ ውስጥ በየዙሩ ከሚገኙት ተሳታፊዎች ከአንዱ ወይ ከሁለቱ በቀር ሁሉም ተዋናያን(ሆን ብለው ስህተት የሆነውን እንዲመርጡ) ይሆኑና በመጨረሻ የተቀረው መልሱን እንዲመልስ ይደረጋል።

ታድያ ውጤቱም ከቅጥረኛ ተዋናያን ጋር ከነበሩት ውስጥ በአማካይ 75% ተሳታፊዎች ቢያንስ አንዴ ስህተት የሆነ መልስ ሰጥተዋል። በአንጻሩ ያላንዳች ተጽእኖ ለብቻቸውን (control group) የመለሱ ተሳታፊዎች ሙሉ ለሙሉ በሚባል ደረጃ ትክክለኛውን መልስ መልሰዋል።

በጥቅሉ የጥናቱ ውጤት እንደሚያሳየው እውነታው ግልጽ እና እርግጥ ሆኖ ሳለ ከሌሎች ላለመነጠል ሲል እያወቀው አልያም ብዙ ሰው ካለውማ ልክ ነው (ሞት ከአገር ጋር እንቅልፍ ነው እንዲሉ አበው) በማለት ካለው እውነት የብዙኃኑን ስህተት ይቀላቀላል።

ግላዊነት በሚንቆለጳጰስበት በዚህ በዘመነ ሉላዊነት ምንበላውን ምግብ ፣የት መብላት እንዳለብን፣ ምንለብሰውን ልብስ፣ ማንን መጥላት፣ ማንን መደገፍ እንዳለብን ሁሉ ባንድም ይሁን በሌላ መንገድ የሚወስንልን ማህበራዊ ሚድያው ሆኗል። ፍቅራችን አድናቆታችን ጥላቻችን የኛ አይደለም። ከየትኛውም ጊዜ በላቀ የመንጋነት ስነልቡና በዓለም ላይ ተንሰራፍቷል። ሌሎችን ቀድሞ መከተል ሌሎችን እንደመምራት የሚቆጠርበት ዘመን ላይ ነን።

ቡድናዊ አስተሳሰብ የተለየ ሃሳብ ማመንጨትን ፣ በተለየ መንገድ ነገሮችን ተረድቶ የተለየ
መፍትሔ መስጠትን ፣ አዲስ እይታን፣ ልዩ ምልከታን በጥቅሉ በራስ መቆምን የሚገድል
ከቡድን ውጭ ያለን ሁሉ በድን የሚል ምልከታ ነው።

Hannah Arendt የተባለች ፖለቲካል ፊሎሶፊስት Adolf Eichman ስለሚባል የናዚ መኮነን የፍርድ ሂደት ላይ በጻፈችው Eichman in Jerusalem በተባለ መጽሐፏ እንዲህ ትለናለች ‘’The sad truth is that most evil is done by people who had never made up their minds to be good or evil. ‘’

የሚያሳዝነው ብዙ ክፋቶችና ጥፋቶች የተሠሩት ክፉና ደጉን ለይተው ክፋትን በሚፈጽሙ ክፉ ሰዎች እና አረመኔዎች ሳይሆን ኢየሱስ “የሚያደርጉትን አያውቁምና ይቅር በላቸው።” እንዳለው የሚያደርጉትን ሁሉ አስበውበት ሳይሆን አሳስበዋቸው በፈጸሙ ፤ ስማ በለው በሚመራቸው ጆሯቸው የአእምሮዋቸውን ቦታ በተካባቸው ብኩኖች ነው።

ከሶቅራጥስ ግድያ እስከ ክርስቶስ ስቅላት፣ከጆርዳኖ ቡሩኖ ቃጠሎ እስከ ስልሣዎቹ መረሸን፤ ከናዚ የዘር ፍጅት እስከ አገራችን ፍጅት በፍራቻ በጥላቻ ና በስጋት
ቡድኖች በባህል በፖለቲካ እና በሃይማኖት ስም የመንጋ ውሳኔዎችን በማስተላለፍ ታላቅ ጥፋት
አድርሰዋል እያደረሱም ነው።

ብዙኃንን መከተል ለምን?

የሰው ልጅ ተፈጥሮ(Human natures need to belong) Aristotile(አርስጣጣሊስ) Man is by nature a social animal ሰው በተፈጥሮው ማህበራዊ እንስሣ ነው ይለናል።

በሰው ልጅ ዝግመተ ለውጥ ውስጥ ለአደን ለመሄድም ሆነ ከአራዊት ጥቃት እራስን ለማዳን የሰው ልጅ ሕይወቱን ለማስቀጠል የሄደበት መንገድ በቡድን መሆንን ነው። ታድያ በስነ ተረክ እና በባህል ተጠቅሞ ኃይልን ለማንበር ፣ ሰላምን ለማስፈን እና ነውጥን ለመግራት የሚያደርገው ትግል በ DNAያችን እና በ ንቃት ህሊናችን ውስጥ ስለሚታተም ከመንጋው መነጠል ወደ ሞት መጓዝ ነው ብሎ እንዲያስብ እና እንዲደምድም ያደርዋል።

ታድያ እርግጠኛ ባለመሆን ፤ተቀባይነትን ለማግኘት፤ መጣልን/መገለልን ፍራቻ በጥቅሉ ክብርን ለማግዘፍና ህላዌን ለማስቀጠል ሲል ብዙኃኑን ይከተላል።
የማህበራዊ ሚዲያን መስፋፋት ተከትሎ የዲጂታል መንጋነትም ለመቆጣጠር በማያስችል ሁኔታ እየተስፋፋ ነው። ጭብጨባችን እንኳ የራሳችን አይደለም። የገደል ማሚቶዎች ሆነናል ፤ በቀቀናዊ ማንነትን ተላብሰናል። ነገሩን ተረዱትም አልተረዱትም ሃሳብን በሃሳብ ከመሞገት ይልቅ በስድብ፣በዛቻ እና በማስፈራራት የሚመልሱ ከልቡናቸው/በጣታቸው በኩልም ይሁን በአፋቸው/ ከጸያፍ ነገር በቀር የሌለ የሚመስል ባለማእረግ ተራጋሚዎችን እያፈራን ነው።

ዲጂታል መንጋዎች ተከታዮቻቸው እንዲነኩባቸው አስተያየት እንዲሰጥባቸው አንዳች ትችት እንዲደርስባቸው አይፈልጉም። የሚከተሉትን ሰዎች ከፈጣሪያችው እኩል አንዳንዴም በላይ እንከን የለሽ አድርገው ስለሳሏቸው እነሱን ለነካባቸው እንጦሮንጦስ ድረስ ወርደው በቀል የመሰላቸውን ነገር ለማድረግ ሁሌም ዝግጁ ናቸው።

ኒቼ Beyond Good and Evil መጽሐፉ ላይ እንዲህ ይላል “Insanity in individuals is something rare - but in groups, parties, nations and epochs, it is the rule.” ቡድኖች እብደታቸውን ሕግ ያደርጉታል።

በማህበር ሲታበድ፤ በጎራ ሲወፈፍ፣ በወል ሲነሆለል፤ ስሜት ይነግሣል ምክንያት ቦታ ያጣል። መቃወም ያስወግራል ፣ መለየት ያስቀጣል ፣መሞገት ያሠድዳል፣ መመርመር ያስቀስፋል ። ከኛ ወዲያ ክንደብርቱ ከኛ ወድያ ኃያል ርቱዕ ከኛ ወድያ ጎራሽ... ፣ ከኛ ወዲያ ላሳር ከኛ ወድያ... ። የሁሉ ነገር መለኪያ ፣ የሁሉ ነገር መተኪያ፣ እና ሁሉ ነገር በራሱ እኛ ነን የሚል የተደፈነ አስተሳሰብን ያጸናል።

እኛ ደሞ(የመተርጎም ነጻነቱን ላንባቢው ትተን) መኖርን የሚያክል ጥናት የለምና ኖረን ካየነው እንዲህ እንላለን Even a pacifist in a mob could become a warmonger.
ቡድናዊነት/የመንጋ እሳቤ በግለሰቦች ውስጥ ያለን እውነት፣ ለውጥ ፣ሂደትና ፈጠራ ወደ በድንነት በመለወጥ በራስ መቆምን የሚያሽመደምድ ነው። መንጋነት ሲነግሥ ሰውነት ይረክሳል፣ ፍትሕ ትንጋደዳለች፣ ስልጣኔ አፈር ይበላዋል።የወል እሳቤ ማጤን መመርመርን በጥቅሉ ሰው መሆንን የሚገድል ነቀርሳ ነው።

በጅምላ ማሰብ፤ የሰው ልጅ የመጀመርያው ሞቱ ነው። ቆም ብለህ አስብ።ከእሳቱ ከልለው ከጨለማው የዶሉህን ትተህ የራስህን ሻማ ለኩሰህ ብርሃንህን አብራ።ሰው ሆነህ ሳለህ እራስህን ስለምን ታሳንሳለህ? ራስህን ችለህ አስብ! በራስህ ተጠራ! ሰው ሁን!

ብዙኃን በመንጋ ፣በቡድን፣ በጎራ ሲያስቡና ሲወስኑ ብቻቸውን መቆም የቻሉ ምንኛ የታደሉ ናቸው። የሰውነት ምልአት የመሻገር ከፍታ እነርሱ ጋር ናትና።

ቸር ያቆየን!

Credit to ባይራ ዲጂታል መፅሄት

@Bayradigital
@Zephilosophy



tgoop.com/Zephilosophy/1036
Create:
Last Update:

ቡድናዊነት በድናዊነት?
ብርሀን ደርበው

የምንከተለው ፋሽን፣ የሚያስቁን ቀልዶች የምንወዳቸው ሙዚቃዎች ወዘተ ወዘተ... እውን የወደድነው የምንወደውን ነው? የምናደርገው ሁሉ በራሳችን ውሳኔ እና ፍላጎት የተደረገ ወይስ ቀልብያችን የሚለን ሌላ ሆኖ አንዳች ኃይል አስገድዶን?

አንዳንዴ እራሴን እንዲህ ብዬ ጠይቃለሁ የምትከተለው ፋሽን የሚያስቁህ ቀልዶች የምትወዳቸው ሙዚቃዎች ወዘተ ወዘተ... ያንተ ምርጫ ወይስ አንዳች ኃይል አስገድዶህ ምትመርጠው? እውን የወደድከው ሁሉ የምትወደውን ነው? የምታደርጋቸው ውሳኔዎች ባንተ ፍላጎት በቀልብያህ ፍቃድ ወይስ ሌሎች ስለወደዱት ላለመነጠል በዓለም ውስጥ
መናኒ ላለመሆን?

Solomon Asch የተባለ ሳይኮሎጂስት Confirmity Line Experiment የምትባል የሰውን ልጅ ውሳኔ አሰጣጥ የምትገመግም አንዲት የምትገርም ጥናት አለችው። እነሆ ጥናቱ A,B,C ሲል የሰየማቸውን ሦስት የተለያየ ቁመት ያላቸው መስመሮች አዘጋጀ።

ተሳታፊዎች በተዘጋጀላቸው ክፍል ውስጥ ሁሉም በየተራ የትኛው መስመር ረዥም እንደሆነ ጮክ ብለው ይናገራሉ። ታድያ ይሄ ሁሉ ሲሆን ክፍሉ ውስጥ በየዙሩ ከሚገኙት ተሳታፊዎች ከአንዱ ወይ ከሁለቱ በቀር ሁሉም ተዋናያን(ሆን ብለው ስህተት የሆነውን እንዲመርጡ) ይሆኑና በመጨረሻ የተቀረው መልሱን እንዲመልስ ይደረጋል።

ታድያ ውጤቱም ከቅጥረኛ ተዋናያን ጋር ከነበሩት ውስጥ በአማካይ 75% ተሳታፊዎች ቢያንስ አንዴ ስህተት የሆነ መልስ ሰጥተዋል። በአንጻሩ ያላንዳች ተጽእኖ ለብቻቸውን (control group) የመለሱ ተሳታፊዎች ሙሉ ለሙሉ በሚባል ደረጃ ትክክለኛውን መልስ መልሰዋል።

በጥቅሉ የጥናቱ ውጤት እንደሚያሳየው እውነታው ግልጽ እና እርግጥ ሆኖ ሳለ ከሌሎች ላለመነጠል ሲል እያወቀው አልያም ብዙ ሰው ካለውማ ልክ ነው (ሞት ከአገር ጋር እንቅልፍ ነው እንዲሉ አበው) በማለት ካለው እውነት የብዙኃኑን ስህተት ይቀላቀላል።

ግላዊነት በሚንቆለጳጰስበት በዚህ በዘመነ ሉላዊነት ምንበላውን ምግብ ፣የት መብላት እንዳለብን፣ ምንለብሰውን ልብስ፣ ማንን መጥላት፣ ማንን መደገፍ እንዳለብን ሁሉ ባንድም ይሁን በሌላ መንገድ የሚወስንልን ማህበራዊ ሚድያው ሆኗል። ፍቅራችን አድናቆታችን ጥላቻችን የኛ አይደለም። ከየትኛውም ጊዜ በላቀ የመንጋነት ስነልቡና በዓለም ላይ ተንሰራፍቷል። ሌሎችን ቀድሞ መከተል ሌሎችን እንደመምራት የሚቆጠርበት ዘመን ላይ ነን።

ቡድናዊ አስተሳሰብ የተለየ ሃሳብ ማመንጨትን ፣ በተለየ መንገድ ነገሮችን ተረድቶ የተለየ
መፍትሔ መስጠትን ፣ አዲስ እይታን፣ ልዩ ምልከታን በጥቅሉ በራስ መቆምን የሚገድል
ከቡድን ውጭ ያለን ሁሉ በድን የሚል ምልከታ ነው።

Hannah Arendt የተባለች ፖለቲካል ፊሎሶፊስት Adolf Eichman ስለሚባል የናዚ መኮነን የፍርድ ሂደት ላይ በጻፈችው Eichman in Jerusalem በተባለ መጽሐፏ እንዲህ ትለናለች ‘’The sad truth is that most evil is done by people who had never made up their minds to be good or evil. ‘’

የሚያሳዝነው ብዙ ክፋቶችና ጥፋቶች የተሠሩት ክፉና ደጉን ለይተው ክፋትን በሚፈጽሙ ክፉ ሰዎች እና አረመኔዎች ሳይሆን ኢየሱስ “የሚያደርጉትን አያውቁምና ይቅር በላቸው።” እንዳለው የሚያደርጉትን ሁሉ አስበውበት ሳይሆን አሳስበዋቸው በፈጸሙ ፤ ስማ በለው በሚመራቸው ጆሯቸው የአእምሮዋቸውን ቦታ በተካባቸው ብኩኖች ነው።

ከሶቅራጥስ ግድያ እስከ ክርስቶስ ስቅላት፣ከጆርዳኖ ቡሩኖ ቃጠሎ እስከ ስልሣዎቹ መረሸን፤ ከናዚ የዘር ፍጅት እስከ አገራችን ፍጅት በፍራቻ በጥላቻ ና በስጋት
ቡድኖች በባህል በፖለቲካ እና በሃይማኖት ስም የመንጋ ውሳኔዎችን በማስተላለፍ ታላቅ ጥፋት
አድርሰዋል እያደረሱም ነው።

ብዙኃንን መከተል ለምን?

የሰው ልጅ ተፈጥሮ(Human natures need to belong) Aristotile(አርስጣጣሊስ) Man is by nature a social animal ሰው በተፈጥሮው ማህበራዊ እንስሣ ነው ይለናል።

በሰው ልጅ ዝግመተ ለውጥ ውስጥ ለአደን ለመሄድም ሆነ ከአራዊት ጥቃት እራስን ለማዳን የሰው ልጅ ሕይወቱን ለማስቀጠል የሄደበት መንገድ በቡድን መሆንን ነው። ታድያ በስነ ተረክ እና በባህል ተጠቅሞ ኃይልን ለማንበር ፣ ሰላምን ለማስፈን እና ነውጥን ለመግራት የሚያደርገው ትግል በ DNAያችን እና በ ንቃት ህሊናችን ውስጥ ስለሚታተም ከመንጋው መነጠል ወደ ሞት መጓዝ ነው ብሎ እንዲያስብ እና እንዲደምድም ያደርዋል።

ታድያ እርግጠኛ ባለመሆን ፤ተቀባይነትን ለማግኘት፤ መጣልን/መገለልን ፍራቻ በጥቅሉ ክብርን ለማግዘፍና ህላዌን ለማስቀጠል ሲል ብዙኃኑን ይከተላል።
የማህበራዊ ሚዲያን መስፋፋት ተከትሎ የዲጂታል መንጋነትም ለመቆጣጠር በማያስችል ሁኔታ እየተስፋፋ ነው። ጭብጨባችን እንኳ የራሳችን አይደለም። የገደል ማሚቶዎች ሆነናል ፤ በቀቀናዊ ማንነትን ተላብሰናል። ነገሩን ተረዱትም አልተረዱትም ሃሳብን በሃሳብ ከመሞገት ይልቅ በስድብ፣በዛቻ እና በማስፈራራት የሚመልሱ ከልቡናቸው/በጣታቸው በኩልም ይሁን በአፋቸው/ ከጸያፍ ነገር በቀር የሌለ የሚመስል ባለማእረግ ተራጋሚዎችን እያፈራን ነው።

ዲጂታል መንጋዎች ተከታዮቻቸው እንዲነኩባቸው አስተያየት እንዲሰጥባቸው አንዳች ትችት እንዲደርስባቸው አይፈልጉም። የሚከተሉትን ሰዎች ከፈጣሪያችው እኩል አንዳንዴም በላይ እንከን የለሽ አድርገው ስለሳሏቸው እነሱን ለነካባቸው እንጦሮንጦስ ድረስ ወርደው በቀል የመሰላቸውን ነገር ለማድረግ ሁሌም ዝግጁ ናቸው።

ኒቼ Beyond Good and Evil መጽሐፉ ላይ እንዲህ ይላል “Insanity in individuals is something rare - but in groups, parties, nations and epochs, it is the rule.” ቡድኖች እብደታቸውን ሕግ ያደርጉታል።

በማህበር ሲታበድ፤ በጎራ ሲወፈፍ፣ በወል ሲነሆለል፤ ስሜት ይነግሣል ምክንያት ቦታ ያጣል። መቃወም ያስወግራል ፣ መለየት ያስቀጣል ፣መሞገት ያሠድዳል፣ መመርመር ያስቀስፋል ። ከኛ ወዲያ ክንደብርቱ ከኛ ወድያ ኃያል ርቱዕ ከኛ ወድያ ጎራሽ... ፣ ከኛ ወዲያ ላሳር ከኛ ወድያ... ። የሁሉ ነገር መለኪያ ፣ የሁሉ ነገር መተኪያ፣ እና ሁሉ ነገር በራሱ እኛ ነን የሚል የተደፈነ አስተሳሰብን ያጸናል።

እኛ ደሞ(የመተርጎም ነጻነቱን ላንባቢው ትተን) መኖርን የሚያክል ጥናት የለምና ኖረን ካየነው እንዲህ እንላለን Even a pacifist in a mob could become a warmonger.
ቡድናዊነት/የመንጋ እሳቤ በግለሰቦች ውስጥ ያለን እውነት፣ ለውጥ ፣ሂደትና ፈጠራ ወደ በድንነት በመለወጥ በራስ መቆምን የሚያሽመደምድ ነው። መንጋነት ሲነግሥ ሰውነት ይረክሳል፣ ፍትሕ ትንጋደዳለች፣ ስልጣኔ አፈር ይበላዋል።የወል እሳቤ ማጤን መመርመርን በጥቅሉ ሰው መሆንን የሚገድል ነቀርሳ ነው።

በጅምላ ማሰብ፤ የሰው ልጅ የመጀመርያው ሞቱ ነው። ቆም ብለህ አስብ።ከእሳቱ ከልለው ከጨለማው የዶሉህን ትተህ የራስህን ሻማ ለኩሰህ ብርሃንህን አብራ።ሰው ሆነህ ሳለህ እራስህን ስለምን ታሳንሳለህ? ራስህን ችለህ አስብ! በራስህ ተጠራ! ሰው ሁን!

ብዙኃን በመንጋ ፣በቡድን፣ በጎራ ሲያስቡና ሲወስኑ ብቻቸውን መቆም የቻሉ ምንኛ የታደሉ ናቸው። የሰውነት ምልአት የመሻገር ከፍታ እነርሱ ጋር ናትና።

ቸር ያቆየን!

Credit to ባይራ ዲጂታል መፅሄት

@Bayradigital
@Zephilosophy

BY ፍልስፍና ለላቀ አስተሳሰብ Philosophy


Share with your friend now:
tgoop.com/Zephilosophy/1036

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

The public channel had more than 109,000 subscribers, Judge Hui said. Ng had the power to remove or amend the messages in the channel, but he “allowed them to exist.” With the sharp downturn in the crypto market, yelling has become a coping mechanism for many crypto traders. This screaming therapy became popular after the surge of Goblintown Ethereum NFTs at the end of May or early June. Here, holders made incoherent groaning sounds in late-night Twitter spaces. They also role-played as urine-loving Goblin creatures. So far, more than a dozen different members have contributed to the group, posting voice notes of themselves screaming, yelling, groaning, and wailing in various pitches and rhythms. Public channels are public to the internet, regardless of whether or not they are subscribed. A public channel is displayed in search results and has a short address (link). Select: Settings – Manage Channel – Administrators – Add administrator. From your list of subscribers, select the correct user. A new window will appear on the screen. Check the rights you’re willing to give to your administrator.
from us


Telegram ፍልስፍና ለላቀ አስተሳሰብ Philosophy
FROM American