BUTAJIRA_QIRAT_DAEWA_GROUP Telegram 1482
ረመዷን እና ተውበት

እንደሚታወቀው ታላቁ የረመዷን ወር ሊገባ የተወሰኑ ቀናት ብቻ ቀርተውታል።እናም መቃረቡን አስመልክቶ በተለያዩ አጋጣሚዎች ይህንን ወር ካጠፋናቸው ጥፋቶች ወደ አሏህ በፀፀት ተመልሰን በንፁህ ልብ መቀበል እንዳለብን በሰፊው ትምህቶች ሲሰጡ ይስተዋላል።ይሁን እንጂ እነዚህን ትምህርቶች በቅጡ ያልተረዱ ወንድሞችና እህቶች ስህተቶችን ሲፈፅሙ ይታያል።ከነዚህ ስህተቶች መካከል አንዱን ብቻ ለማሳያነት ልጥቀስ

\\  ረመዷን ሲመጣ ሁሉም በሚባል ያህል ሙስሊሙ ኡማ ባለቺው እውቀት ልክ ይዘጋጃል።ከነዚህ ዝግጅቶች መካከል በተውበት ወደ አሏህ መመለስ አንደኛውና ዋንኛው ነው።ነገር ግን ተውበታችን ተውበታችንን በሚያበላሽ እሳቤ( ኒያ) ላይ ተመስርቶ ይታያል።ይህ እሳቤ ምንድነው ካላቹህ ? መልካም !! ነገሩ ወዲህ ነው, ገና ተውበት ስናደርግ ለተውበታችን የመነሻና የመድረሻ ጊዜ ገደብ እናበጅለታለን።

ለምሳሌ፦ አንድ ሶላት የማይሰግድ ሰው ረመዷንን ከዚህ ጥፋቱ ተመልሶ መቀበል ይፈልጋል።ነገር ግን ሶላቱን የሚጀምረው የረመዷን የመጀመሪያው ቀን  ወይም ከሱ አንድ ቀን ቀደም ብሎ ይሆናል፤ይህም ብቻ አይደለም ረመዷን መጨረሻ አካባቢም በነሻጣ የጀመረውን ሶላት አቋርጦ ፆሙን ብቻ ያስቀጥላል። የዚህን ሰው ተውበት ስናይ የተውበትን መስፈርት ያሟላ አይደለም።ምክንያቱም ተቀባይነት ያለው ተውበት በጥቂቱ ሶስት መስፈርቶችን ያሟላ መሆን አለበት።እነርሱም

➊ ተውበት ለማድረግ ከወሰነበት ሰዓት ጀምሮ ከወንጀሉ ተነቅሎ መውጣት

➋ በሰራው ወንጀል መፀፀት

➌ ዳግም ወደዛ ወንጀል ላለመመለስ ቁር፞ጥ ያለ ውሳኔ መወሰን

★ ከላይ ለምሳሌነት ያነሳነው ሰውዬ ግልፅ በሆነ መልኩ የመጀመሪያውንና የመጨረሻውን መስፈርት ያሟላ አይደለም።ምክንያቱም ተውበት ለማድረግ የወሰነው ምናልባት ረመዷን ሳምንት ሲቀረው ይሆናል ነገር ግን ሶላቱን የሚጀምረው ረመዷን ሲገባ ነው።ይህም ማለት ተውበት ለማድረግ ከወሰነበት ሰዓት ጀምሮ ከወንጀሉ ( ሶላቱን ከመተው) አልወጣም ማለት ነው።በዚህ መሰረት የመጀመሪያውን መስፈርት አጓድሏል።ሌላኛው ደሞ ረመዷን ሲወጣ አብሮ ሶላቱንም ይተዋል።ይህ ከሆነ  ደሞ ተውበት ስናደርግ ዳግም ወደዛ ጥፋት ላለመመለስ ቁር፞ጥ ያለ ውሳኔ መወሰን አለበት ብለን ሶስተኛ ላይ ያሰቀመጥነውን መስፈርት ያላሟላ ሆኖ ይገኛል ማለት ነው።ተውበታችን ደሞ ተቀባይነት የሚኖረው ሁሉንም መስፈርት ስናሟላ ነው።ያለበለዚያ ተውበታችን አሁን አፏን ጠርጋ ምንም ሳትቆይ ዳግም ቆሻሻ ለመልቀም እንደመትመለሰው ዶሮ ነውና የሚሆነው ልንጠነቀቅ ይገባል።ሶላቱን ካሁኗ ሰዓት ጀምረን ላለማቋረጥ ወስነን መጀመር አለብን። ለምሳሌ ብለን ሶላትን መተው አነሳን እንጂ ከሌሎችም ጥፋቶቻችን ስንመለስ በዚህ መልኩ መሆን ይኖርበታል።

እናስተዉል!!

ተውበት ማለት ካሳለፍናቸው የወንጀል ቆሻሾቻችን የምንፀዳበት የአዛኙ ጌታችን ትልቅ ስጦታ መሆኑን ማስተዋል ይጠበቅብናል።ተውበት ማድረግ ባይኖር እና በእያንዳንዱ ወንጀላችን አሏህ ቢተሳሰበን  ምን ይውጠን ነበር!? የትስ እናመልጥ ነበር? ስለዚህ ወንድም እና እህቶች የተውበትን ፀጋነት አስተውለን ይህንን ድንቅ የአሏህ ስጦታ እሱ ባዘዘን እንዲሁም መልዕክተኛው ( አለይሂ ሶላቱ ወሰላም) ባሳዩን መልኩ ልንጠቀምበት ይገባል እንጂ እንደ ቀልድ የምናስመልጠው እድል መሆን የለበትም።ከዚህ በተጨማሪ ተውበት ማለት ልክ እንደ ሶላት ፣ ፆም ፣ ዘካና መሰል የሆኑ ኢባዳዎች እራሱን የቻለ ዒባዳ መሆኑን ጠንቅቀን አውቀን በተገቢው መልኩ ልንፈፅመው ይገባል።

በመጨረሻም አሏህ

َّ (وَتُوبُوا إِلَى اللَّهِ جَمِيعًا أَيُّهَ الْمُؤْمِنُونَ لَعَلَّكُمْ تُفْلِحُونَ)

(ምእመናኖች ሆይ! ትድኑ ዘንድ ሁላችሁም ወደ አላህ (በመመለስ) ተጸጸቱ ።)
【አል—ኑር 31】

ብሏልና  ይህንን የተከበረውን እንግዳ  አድርሶን ፤ እሱ በሚፈልገው መልኩ ወደሱ በፀፀት ተመልሰው ይህንን ታላቅ ወር የሚቀበሉ እና በውስጡም መልካሙን ሁሉ ገጥሟቸው የውመል ቂያማ በፆማቸው አጅር ምክንያት ከሚደሰቱት ያድርገን ።


                   አሏሁመ አሚን!!



tgoop.com/butajira_Qirat_daewa_group/1482
Create:
Last Update:

ረመዷን እና ተውበት

እንደሚታወቀው ታላቁ የረመዷን ወር ሊገባ የተወሰኑ ቀናት ብቻ ቀርተውታል።እናም መቃረቡን አስመልክቶ በተለያዩ አጋጣሚዎች ይህንን ወር ካጠፋናቸው ጥፋቶች ወደ አሏህ በፀፀት ተመልሰን በንፁህ ልብ መቀበል እንዳለብን በሰፊው ትምህቶች ሲሰጡ ይስተዋላል።ይሁን እንጂ እነዚህን ትምህርቶች በቅጡ ያልተረዱ ወንድሞችና እህቶች ስህተቶችን ሲፈፅሙ ይታያል።ከነዚህ ስህተቶች መካከል አንዱን ብቻ ለማሳያነት ልጥቀስ

\\  ረመዷን ሲመጣ ሁሉም በሚባል ያህል ሙስሊሙ ኡማ ባለቺው እውቀት ልክ ይዘጋጃል።ከነዚህ ዝግጅቶች መካከል በተውበት ወደ አሏህ መመለስ አንደኛውና ዋንኛው ነው።ነገር ግን ተውበታችን ተውበታችንን በሚያበላሽ እሳቤ( ኒያ) ላይ ተመስርቶ ይታያል።ይህ እሳቤ ምንድነው ካላቹህ ? መልካም !! ነገሩ ወዲህ ነው, ገና ተውበት ስናደርግ ለተውበታችን የመነሻና የመድረሻ ጊዜ ገደብ እናበጅለታለን።

ለምሳሌ፦ አንድ ሶላት የማይሰግድ ሰው ረመዷንን ከዚህ ጥፋቱ ተመልሶ መቀበል ይፈልጋል።ነገር ግን ሶላቱን የሚጀምረው የረመዷን የመጀመሪያው ቀን  ወይም ከሱ አንድ ቀን ቀደም ብሎ ይሆናል፤ይህም ብቻ አይደለም ረመዷን መጨረሻ አካባቢም በነሻጣ የጀመረውን ሶላት አቋርጦ ፆሙን ብቻ ያስቀጥላል። የዚህን ሰው ተውበት ስናይ የተውበትን መስፈርት ያሟላ አይደለም።ምክንያቱም ተቀባይነት ያለው ተውበት በጥቂቱ ሶስት መስፈርቶችን ያሟላ መሆን አለበት።እነርሱም

➊ ተውበት ለማድረግ ከወሰነበት ሰዓት ጀምሮ ከወንጀሉ ተነቅሎ መውጣት

➋ በሰራው ወንጀል መፀፀት

➌ ዳግም ወደዛ ወንጀል ላለመመለስ ቁር፞ጥ ያለ ውሳኔ መወሰን

★ ከላይ ለምሳሌነት ያነሳነው ሰውዬ ግልፅ በሆነ መልኩ የመጀመሪያውንና የመጨረሻውን መስፈርት ያሟላ አይደለም።ምክንያቱም ተውበት ለማድረግ የወሰነው ምናልባት ረመዷን ሳምንት ሲቀረው ይሆናል ነገር ግን ሶላቱን የሚጀምረው ረመዷን ሲገባ ነው።ይህም ማለት ተውበት ለማድረግ ከወሰነበት ሰዓት ጀምሮ ከወንጀሉ ( ሶላቱን ከመተው) አልወጣም ማለት ነው።በዚህ መሰረት የመጀመሪያውን መስፈርት አጓድሏል።ሌላኛው ደሞ ረመዷን ሲወጣ አብሮ ሶላቱንም ይተዋል።ይህ ከሆነ  ደሞ ተውበት ስናደርግ ዳግም ወደዛ ጥፋት ላለመመለስ ቁር፞ጥ ያለ ውሳኔ መወሰን አለበት ብለን ሶስተኛ ላይ ያሰቀመጥነውን መስፈርት ያላሟላ ሆኖ ይገኛል ማለት ነው።ተውበታችን ደሞ ተቀባይነት የሚኖረው ሁሉንም መስፈርት ስናሟላ ነው።ያለበለዚያ ተውበታችን አሁን አፏን ጠርጋ ምንም ሳትቆይ ዳግም ቆሻሻ ለመልቀም እንደመትመለሰው ዶሮ ነውና የሚሆነው ልንጠነቀቅ ይገባል።ሶላቱን ካሁኗ ሰዓት ጀምረን ላለማቋረጥ ወስነን መጀመር አለብን። ለምሳሌ ብለን ሶላትን መተው አነሳን እንጂ ከሌሎችም ጥፋቶቻችን ስንመለስ በዚህ መልኩ መሆን ይኖርበታል።

እናስተዉል!!

ተውበት ማለት ካሳለፍናቸው የወንጀል ቆሻሾቻችን የምንፀዳበት የአዛኙ ጌታችን ትልቅ ስጦታ መሆኑን ማስተዋል ይጠበቅብናል።ተውበት ማድረግ ባይኖር እና በእያንዳንዱ ወንጀላችን አሏህ ቢተሳሰበን  ምን ይውጠን ነበር!? የትስ እናመልጥ ነበር? ስለዚህ ወንድም እና እህቶች የተውበትን ፀጋነት አስተውለን ይህንን ድንቅ የአሏህ ስጦታ እሱ ባዘዘን እንዲሁም መልዕክተኛው ( አለይሂ ሶላቱ ወሰላም) ባሳዩን መልኩ ልንጠቀምበት ይገባል እንጂ እንደ ቀልድ የምናስመልጠው እድል መሆን የለበትም።ከዚህ በተጨማሪ ተውበት ማለት ልክ እንደ ሶላት ፣ ፆም ፣ ዘካና መሰል የሆኑ ኢባዳዎች እራሱን የቻለ ዒባዳ መሆኑን ጠንቅቀን አውቀን በተገቢው መልኩ ልንፈፅመው ይገባል።

በመጨረሻም አሏህ

َّ (وَتُوبُوا إِلَى اللَّهِ جَمِيعًا أَيُّهَ الْمُؤْمِنُونَ لَعَلَّكُمْ تُفْلِحُونَ)

(ምእመናኖች ሆይ! ትድኑ ዘንድ ሁላችሁም ወደ አላህ (በመመለስ) ተጸጸቱ ።)
【አል—ኑር 31】

ብሏልና  ይህንን የተከበረውን እንግዳ  አድርሶን ፤ እሱ በሚፈልገው መልኩ ወደሱ በፀፀት ተመልሰው ይህንን ታላቅ ወር የሚቀበሉ እና በውስጡም መልካሙን ሁሉ ገጥሟቸው የውመል ቂያማ በፆማቸው አጅር ምክንያት ከሚደሰቱት ያድርገን ።


                   አሏሁመ አሚን!!

BY የቡታጅራ አህለሱና ቂራኣትና ዳዕዋ ቻናል


Share with your friend now:
tgoop.com/butajira_Qirat_daewa_group/1482

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

A few years ago, you had to use a special bot to run a poll on Telegram. Now you can easily do that yourself in two clicks. Hit the Menu icon and select “Create Poll.” Write your question and add up to 10 options. Running polls is a powerful strategy for getting feedback from your audience. If you’re considering the possibility of modifying your channel in any way, be sure to ask your subscribers’ opinions first. How to Create a Private or Public Channel on Telegram? In 2018, Telegram’s audience reached 200 million people, with 500,000 new users joining the messenger every day. It was launched for iOS on 14 August 2013 and Android on 20 October 2013. Your posting frequency depends on the topic of your channel. If you have a news channel, it’s OK to publish new content every day (or even every hour). For other industries, stick with 2-3 large posts a week. Done! Now you’re the proud owner of a Telegram channel. The next step is to set up and customize your channel.
from us


Telegram የቡታጅራ አህለሱና ቂራኣትና ዳዕዋ ቻናል
FROM American