tgoop.com/christsbelievers/4198
Last Update:
. #አእምሮን_ማንቃት
👇
ከልጅነታችሁ ጀምራችሁ #ያጎለበታችሁት ፤ በፍጹም #የማትጠራጠሩት ፤ በዚህ በፍጹም ሰይጣንም ይሁን ሁኔታ #ፈጽሞ_ሊያስተኝ አይችልም ያላችሁት ፤ ለሰዎች በኩራት #የምታወሩት ፤ ሰዎች እናንተን በዚህ አቋሟችሁ ጠንካራ እንደሆናችሁ #የሚመሰክሩሏችሁ ፤ በሰውና በእግዚአብሔር ፊት ያለኝ #ጠንካራ_ጎኔ ይህ ነው ብላችሁ #የምትናገሩት ፤ በልበ ሙሉነት ከአቋሜ ለአንዲት #ሰከንድ_ሸርተት አልልም ፥ የምትሉት ነገር አላችሁ?
#እኔ_ነበረኝ ግን ያ ሁሉ ነገር #እኔ ስለራሴ የማስበውና የምናገረው ውሸት ነበር😭
#እውነቱ_ይህ_ብቻ_ነበር👉 "ሰው በኃይሉ አይበረታምና።”— 1ኛ ሳሙኤል 2፥9
#ሃይሌ ባልኩት ነገር #ደከምኩ ፤ #ጉልበቴ ባልኩት ነገሬ #ደከምኩ ፤ #ብርታቴ ብዬ በማስበው ባሕሪይ #ዛልኩ😭
#ግን_እውነቱ_ይሄ_ነበር👉 “በገዛ ልቡ የሚታመን ሰው ሰነፍ ነው፤ በጥበብ የሚሄድ ግን ይድናል።”— ምሳሌ 28፥26
#ሰዎች ሲወድቁ እንዴት ይወድቃሉ ባልኩት ፤ #ሰዎች ሲደክሙ እንዴት ይደክማሉ ባልኩት ፤ #ሰዎች ሲያቅታቸው ባንጓጠጥኩበት ነገር ፤ #ሰዎች ሲሰበሩ በሳኩበት ነገር ፤ በዚህ #እኔ ከነሱ የተሻልኩ እንደሆንኩ #ባፏጨውበት ነገር ፤
#እኔ ወደኩ ፣ #እኔ ደከምኩ ፣ #እኔ አቃተኝ ፣ #እኔ ተሰበርኩ ፣ #እኔ ከነሱ በብዙ አንሼ ተገኘው 😭😭😭
#ግን_እውነቱ_ይሄ_ነበር 👉 “አንተ በሌላው ሎሌ የምትፈርድ ማን ነህ? እርሱ ቢቆም ወይም ቢወድቅ ለገዛ ጌታው ነው፤ ነገር ግን እግዚአብሔር ሊያቆመው ይችላልና ይቆማል።” — ሮሜ 14፥4
#አሁን_ይሄንን_ተረድቻለሁ “ልጆቼ ሆይ፥ ኃጢአትን እንዳታደርጉ ይህን እጽፍላችኋለሁ። ማንም ኃጢአትን ቢያደርግ ከአብ ዘንድ ጠበቃ አለን እርሱም ጻድቅ የሆነ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።”— 1ኛ ዮሐንስ 2፥1
✍ @Ye_Fikr_Tebib
Channel @Christsbelievers
@Christsbelievers
@Christsbelievers
🔺ይ🀄️ላ🀄️ሉን🔺
BY Christsbelievers
Share with your friend now:
tgoop.com/christsbelievers/4198