COFFEEANDSCRIBBLINGS Telegram 626
ይህች ተራራማ ከተማ... ይህች ተራራማ ሀገር... ምስጢሯን መጠበቅ አታውቅበትም። ህንጻዎቿ ከዋክብት መስለው መብራታቸውን ያንቦገቡጋሉ። በተራ የተሰደሩ መዐት ከዋክብት። መኪኖቿ በተራሮቿ መቀነት ሽር እያሉ ከአይን ሲጠፉ እዚሁ ቁጭ ባልኹበት ይታየኛል።

ከላይ ከሚንቦገቦጉት ከተሞች ስር ጭል ጭል የሚሉ ኮሳሳ ቤቶች አሉ። ቡናማ ጣሪያቸው ቀለሙ ከማይለይ ግድግዳ ጋር። ነጭ ቲሸርት የለበሱ ባለነጫጭ ጸጉር አባወራዎች በዱካ የሚቀመጡባቸው። ትናንሽ ልጆች ፀጉራቸው እንደተንጨባረረ ቂጣቸውን ጥለው የሚሮጡባቸው። ሴቶች በሚዶ ጸጉራቸውን መንጨር መንጨር የሚያደርጉባቸው። ሳፋ፣ መዘፍዘፊያ፣ ጀሪካን፣ ሙቀጫ ደግሞ ሌላም ሌላም ዝርግፍግፍ ያለባቸው። ቢጫማ አፈራቸውን የለበሱ ግቢዎች። የተደጋገፉ ቤቶች። ጩኸት፣ ጫጫታ፣ እንቅስቃሴ የማይጠፋባቸው።

የአክስቴን ቤት ያስታውሱኛል። ወይም የሌላዋን። ወይም የእከሌን።

የሚብለጨለጩት መብራቶች ትናንሾቹን እንደሚውጧቸው አውቃለሁ። ፊት ለፊቴ የተዘረጋው የበቆሎ እርሻ አስፋልት እንደሚሆን አውቃለሁ።

አይቼዋለሁ። ስም ይቀየራል። ቦታ ይቀየራል እንጂ ታሪክ አይቀየርም።

ድህነት ሲያበሩት ወዴት ነው የሚሄደው? ክፉ ጥላውን ይዞ ፈንጠር ይላል እንጂ ይጠፋል?

ከአይን ቢርቅ ከልብ ይርቃል ድህነት?

የህጻናቱን ጩኸት እየሰማሁ አስባለሁ። የምብለጨለጨው የማንን ፋኖስ አጥፍቼ ነው?

@coffeeandscribblings



tgoop.com/coffeeandscribblings/626
Create:
Last Update:

ይህች ተራራማ ከተማ... ይህች ተራራማ ሀገር... ምስጢሯን መጠበቅ አታውቅበትም። ህንጻዎቿ ከዋክብት መስለው መብራታቸውን ያንቦገቡጋሉ። በተራ የተሰደሩ መዐት ከዋክብት። መኪኖቿ በተራሮቿ መቀነት ሽር እያሉ ከአይን ሲጠፉ እዚሁ ቁጭ ባልኹበት ይታየኛል።

ከላይ ከሚንቦገቦጉት ከተሞች ስር ጭል ጭል የሚሉ ኮሳሳ ቤቶች አሉ። ቡናማ ጣሪያቸው ቀለሙ ከማይለይ ግድግዳ ጋር። ነጭ ቲሸርት የለበሱ ባለነጫጭ ጸጉር አባወራዎች በዱካ የሚቀመጡባቸው። ትናንሽ ልጆች ፀጉራቸው እንደተንጨባረረ ቂጣቸውን ጥለው የሚሮጡባቸው። ሴቶች በሚዶ ጸጉራቸውን መንጨር መንጨር የሚያደርጉባቸው። ሳፋ፣ መዘፍዘፊያ፣ ጀሪካን፣ ሙቀጫ ደግሞ ሌላም ሌላም ዝርግፍግፍ ያለባቸው። ቢጫማ አፈራቸውን የለበሱ ግቢዎች። የተደጋገፉ ቤቶች። ጩኸት፣ ጫጫታ፣ እንቅስቃሴ የማይጠፋባቸው።

የአክስቴን ቤት ያስታውሱኛል። ወይም የሌላዋን። ወይም የእከሌን።

የሚብለጨለጩት መብራቶች ትናንሾቹን እንደሚውጧቸው አውቃለሁ። ፊት ለፊቴ የተዘረጋው የበቆሎ እርሻ አስፋልት እንደሚሆን አውቃለሁ።

አይቼዋለሁ። ስም ይቀየራል። ቦታ ይቀየራል እንጂ ታሪክ አይቀየርም።

ድህነት ሲያበሩት ወዴት ነው የሚሄደው? ክፉ ጥላውን ይዞ ፈንጠር ይላል እንጂ ይጠፋል?

ከአይን ቢርቅ ከልብ ይርቃል ድህነት?

የህጻናቱን ጩኸት እየሰማሁ አስባለሁ። የምብለጨለጨው የማንን ፋኖስ አጥፍቼ ነው?

@coffeeandscribblings

BY Coffee and Scribblings


Share with your friend now:
tgoop.com/coffeeandscribblings/626

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

Administrators The Channel name and bio must be no more than 255 characters long So far, more than a dozen different members have contributed to the group, posting voice notes of themselves screaming, yelling, groaning, and wailing in various pitches and rhythms. Those being doxxed include outgoing Chief Executive Carrie Lam Cheng Yuet-ngor, Chung and police assistant commissioner Joe Chan Tung, who heads police's cyber security and technology crime bureau. Done! Now you’re the proud owner of a Telegram channel. The next step is to set up and customize your channel.
from us


Telegram Coffee and Scribblings
FROM American