DMTSE_TEWAEDO Telegram 10399
ጾም በእግዚአብሔር ታዟል፤ተፈቅዷልም ።
++++++++++++++++++++++++++
ጌታችን አምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ጾምን እንድንጾም ባርኮ የሰጠን እሱ ነው ።ለዚህም ማረጋገጫ ፦
"ኢየሱስም እንዲህ አላቸው፦ሚዜዎች ሙሽራው ከእነርሱ ጋር ሳለ ሊያዝኑ ይችላሉን? ነገር ግን ሙሽራው ከእነርሱ የሚወሰድበት ወራት ይመጣል፥ በዚያ ጊዜም ይጦማሉ።"
ማቴ 9:15
በዚህ መሰረት ፦
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የራሷ የሆነ የጾም ህግና ስርዓት አላት ።
"ነገር ግን ሁሉ በአግባብና በሥርዓት ይሁን ።"እንዲል
1ኛ ቆሮ 14፥40
በቤተክርስቲያናችን ህግና ሥርዓት ተሰርቶላቸው
ከሚጾሙ 7 የአዋጅ አጽዋማት መካከል አንዱ ጾመ ነብያት ይባላል ።የጾሙ ጊዜ ከህዳር 15-እስከ ጌታ ልደት ታህሳስ 28 ድረስ ያለው ነው ።ይህን ጾም የምንጾመው ነቢያት በየዘመናቸው ስለክርስቶስ መምጣት ንጽህት ከምትሆን ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም መወለዱን በናፍቆት ይጾሙና ይጸልዩ ስለነበር የእነርሱን አርአያ ተከትለን የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስን ልደት ከማክበራችን ቀደም ብለን ይህን ጾም እንድንጾም በሐዋርያዊት ቤተክርስቲያን ሥርዓት ተሰርቷል። (ፍት.መ.ን.አንቀጽ 15)
ስለሆነም እኛም ክርስቲያኖች ይህን ተከትለን ብልቶቻችንን ሁሉ(አይን ይጹም ፤እጅ ይጹም፤ እግር ይጹም ፤አንደበት ይጹመ...እንዳለ ቅዱስ ያሬድ) ከኃጢአት ጠብቀን፤እግዚአብሔርን ከማያስደስቱ ማናቸውም ነገሮች ራሳችንን አርቀንና ፤በወንድሞቻችን በማናቸውም ላይ ቂም በቀልን በማስወገድ ይቅርም በመባባል ፤ጸሎትን ስግደትን ምጽዋትንም በመጨመር በንጹህ ልቦና መጾም ይገባናል።ይህን ካደረግን ዘወትር የሚዋጉንና የሚፈታተኑን የአጋንንት ሰራዊት በሙሉ ይደመሰሳሉ፤ኃይላቸውም ይደክማል ።ከእግዚአብሔር ከአምላካችን ፍቅርን ሰላምና በረከትንም እንቀበላለን ።
"የጌታ ቃል የታመነ ነውና።"ቲቶ 3:8
".....ይህ ዓይነት ግን ከጸሎትና ከጦም በቀር አይወጣም አላቸው።"
ማቴ 17:21

#ድምፀ_ተዋህዶ

        📹📹📹📹
   ፊላታዎስ ሚዲያ
               👇👇
https://youtu.be/PYhgHxupzLI?si=pQaqogjyj_DUcNXW
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM



tgoop.com/dmtse_tewaedo/10399
Create:
Last Update:

ጾም በእግዚአብሔር ታዟል፤ተፈቅዷልም ።
++++++++++++++++++++++++++
ጌታችን አምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ጾምን እንድንጾም ባርኮ የሰጠን እሱ ነው ።ለዚህም ማረጋገጫ ፦
"ኢየሱስም እንዲህ አላቸው፦ሚዜዎች ሙሽራው ከእነርሱ ጋር ሳለ ሊያዝኑ ይችላሉን? ነገር ግን ሙሽራው ከእነርሱ የሚወሰድበት ወራት ይመጣል፥ በዚያ ጊዜም ይጦማሉ።"
ማቴ 9:15
በዚህ መሰረት ፦
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የራሷ የሆነ የጾም ህግና ስርዓት አላት ።
"ነገር ግን ሁሉ በአግባብና በሥርዓት ይሁን ።"እንዲል
1ኛ ቆሮ 14፥40
በቤተክርስቲያናችን ህግና ሥርዓት ተሰርቶላቸው
ከሚጾሙ 7 የአዋጅ አጽዋማት መካከል አንዱ ጾመ ነብያት ይባላል ።የጾሙ ጊዜ ከህዳር 15-እስከ ጌታ ልደት ታህሳስ 28 ድረስ ያለው ነው ።ይህን ጾም የምንጾመው ነቢያት በየዘመናቸው ስለክርስቶስ መምጣት ንጽህት ከምትሆን ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም መወለዱን በናፍቆት ይጾሙና ይጸልዩ ስለነበር የእነርሱን አርአያ ተከትለን የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስን ልደት ከማክበራችን ቀደም ብለን ይህን ጾም እንድንጾም በሐዋርያዊት ቤተክርስቲያን ሥርዓት ተሰርቷል። (ፍት.መ.ን.አንቀጽ 15)
ስለሆነም እኛም ክርስቲያኖች ይህን ተከትለን ብልቶቻችንን ሁሉ(አይን ይጹም ፤እጅ ይጹም፤ እግር ይጹም ፤አንደበት ይጹመ...እንዳለ ቅዱስ ያሬድ) ከኃጢአት ጠብቀን፤እግዚአብሔርን ከማያስደስቱ ማናቸውም ነገሮች ራሳችንን አርቀንና ፤በወንድሞቻችን በማናቸውም ላይ ቂም በቀልን በማስወገድ ይቅርም በመባባል ፤ጸሎትን ስግደትን ምጽዋትንም በመጨመር በንጹህ ልቦና መጾም ይገባናል።ይህን ካደረግን ዘወትር የሚዋጉንና የሚፈታተኑን የአጋንንት ሰራዊት በሙሉ ይደመሰሳሉ፤ኃይላቸውም ይደክማል ።ከእግዚአብሔር ከአምላካችን ፍቅርን ሰላምና በረከትንም እንቀበላለን ።
"የጌታ ቃል የታመነ ነውና።"ቲቶ 3:8
".....ይህ ዓይነት ግን ከጸሎትና ከጦም በቀር አይወጣም አላቸው።"
ማቴ 17:21

#ድምፀ_ተዋህዶ

        📹📹📹📹
   ፊላታዎስ ሚዲያ
               👇👇
https://youtu.be/PYhgHxupzLI?si=pQaqogjyj_DUcNXW

BY 🎤✨ድምፀ ተዋህዶ✨🎤


Share with your friend now:
tgoop.com/dmtse_tewaedo/10399

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

The best encrypted messaging apps 3How to create a Telegram channel? Telegram offers a powerful toolset that allows businesses to create and manage channels, groups, and bots to broadcast messages, engage in conversations, and offer reliable customer support via bots. It’s yet another bloodbath on Satoshi Street. As of press time, Bitcoin (BTC) and the broader cryptocurrency market have corrected another 10 percent amid a massive sell-off. Ethereum (EHT) is down a staggering 15 percent moving close to $1,000, down more than 42 percent on the weekly chart. Hui said the messages, which included urging the disruption of airport operations, were attempts to incite followers to make use of poisonous, corrosive or flammable substances to vandalize police vehicles, and also called on others to make weapons to harm police.
from us


Telegram 🎤✨ድምፀ ተዋህዶ✨🎤
FROM American