Telegram Web
🙊🙊ስድብ በቀጠሮ🙊🙊
▪️▫️▪️▫️▪️▫️▪️▫️▪️

🗣ሴትየዋ በሰፈሩ ውስጥ የታወቀች ተሳዳቢና ተንኳሽ ናት። ወቅቱ የአቢይ ጾም መግቢያ አካባቢ ነው "አሁንስ በጾም በጸሎት ተወስኜ መኖር አለብኝ" ብላ ለራሷ ቃል ትገባና የንስሐ አባቷን ታማክራለች።

🕯 የንስሐ አባቷም በውሳኔዋ ተደስተው መልካም ማድረጓን ገልጸው እንዲህ ሲል ይመክሯታል። "ልጄ አደራሽን ይህ የሱባዔ ወቅት ሁላችን በጾምና በጸሎት ወደ ፈጣሪያችን የምንመለስበትና ስለ ኃጥያታችን የምናለቅስበት ነው እኛ ክርስትያኖች በይኽ ጊዜ እንኳንስ እርስ በእርስ ልንጣላ ይቅርና ጠላታችንን የምንወድበት፣ ስንበድል ይቅርታን የምንልበት የንስሐ ጊዜ ነው።ስለይኽ እንኳን አንቺ ቀድመሽ ልትናገሪ ቢናገሩሽም እንኳን በትእግስት ማለፍ ይኖርብሻል። አደራ ልጄ በርቺ እግዚአብሔር ከአንቺ ጋር ይሁን። ብለው ባርከው ያሰናብቷቷል።

💎ጾሙ ተጀመረና በሦስተኛው ቀን ሴትየዋ የከሰዓቱን ቅዳሴ አስቀድሳ ወደ ቤቷ ስትገባ "አንዴ ሌባ ካሏት ብትቆርብም አያምኗት" እንደተባለው የመንደሩ ሴት በነገር ጠመዳት። እስኪ ተመልከቷት አሁን ላያት ሰው እውነተኛ ክርስቲያን አትመስልም?? ወገኛ......እያሉ ዘለፏት እሷ ግን የንስሐ አባቷ የመከሯትን አስታውሳ እንዳትሳደብም ጾም በመሆኑ እንዲህ አለች "እሺ አሁን ስደቡኝ ግድ የለም ይኽ ጾም ይፈታና እያንዳንድሽን ልክ አስገባሻለሁ። .......

😊😊😊😊😊😊😊😊😊😊😊😊
ሁሌም ቢሆን ተናግሮ አናጋሪውን ያዝልኝ ማለት ደግ ነው ቢሆንም ግን የብዙዎች ክርስትና እንደ ፋብሪካ ሠራተኛ በሺፍት(በፈረቃ) ነው። በጾም ጊዜ ወደ ቤተክርስቲያን ይገሰግሳሉ ለፋሲካ ግን የመጠጥና ጭፈራ ቤቱን ያጨናንቁታል።

👉👉የሁዳዴ ክርስቲያን የፋሲካ ዘፋኝ መሆን አይገባንም ።
     "በጊዜውም አለጊዜውም ጽና "
"...........እነሆ፥ የተወደደው ሰዓት አሁን ነው፤ የመዳን ቀን አሁን ነው"
--2ኛ ቆሮ 6፥2
ኪዳነ_ምሕረት

ስላንቺ ላወራ ስል እንባዬ ይቀድመኛል😥
ፍቅርሽን ውለታሽን ምገልጽበት ቃላት ያጥረኛል ከደጅሽ መጥቼ አለቀስኩ አቀረቀርኩም ግን አንቺ የልጅሽ ሀዘን አቶጂምና ቀና አረክሽ ችግሬን ላይመለስ ከእኔ አራቅሽው ታድያ በየትኛው አንደበትና ቃል አንቺን ላመሥግንሽ🙏
አንቺን ለምኜ የአጣሁት የለም

እናቴ

እኔማ አሁንም ደግሜ ደጋግሜ ኅጥያት መስራት አላቆምኩም፤ አንቺንም ማፍቀሬን አላቆምኩም
ይገርመኛል የአንቺ ትሕትና እደዚ ኅጥያተኛ ሆኜ ከኔ አትለይኚም እንዴት አይነት ፍቅር ❤️ ቢሆን ነው እንዴትስ ያለ መውደድ ነው፤ እንዴትስ ብዬ ላውራው ምንስ ቃል ተጠቅሜ ስላንቺ ፍቅር ልናገር እመቤቴ፤ ያንቺስ ደግነት በዛብኝ ከአይምሮ በላይ ሆነብኝ እናቴ አንቺን ሳመሰግን ነፍሴ ከሥጋዬ ልትለይ ትደርሳለች ገና ለማመስገን ስምሽን ስጠራው እንባዬ ይመጣል😢 የፍቅርሽ ኃይሉ በጣም ከባድ ነው። ሊመጠን፤ ሊለካ፤ ሊመዘን...ጭራሽ አይቻልም እና አንቺ ለኔ ያለሽ ፍቅር ልዩ ነው ኪዳነ_ምህረት እናቴ

👉 እናቴ በስንፍናዬ ላላመሰግንሽ እችላለሁ በስምሽ ላልጸልይ እችላለሁ መቼም ግን ስምሽን ሳልጠራ አልውልም

እ_ወ_ድ_ሻ_ለ_ሁ

꧁  ይ🀄🀄ሉ ꧂

https://www.tgoop.com/eotcy
https://www.tgoop.com/eotcy
https://www.tgoop.com/eotcy
ኃጢአቷን የምትጽፈዉ ሴት

አንዲት ሴት ነበረች ኃጢአቷን የምትጽፍ
ልቧ በኃጢአት የሰከረ ለኃጢአትም ተገዥ የሆነች ይች ሴት የተለያየ ኃጢያት የምትሰራ ናት ትዘሙታለች፣ ትዋሻለች፣ ታማለች፣ ተሰርቃለች፣ ትገድላለች፣ በአል ትሽራለች፣ በትእቢት የተሞላች ሴት ናት ልቧ ኃጢአት ነበር። ነገር ግን የምትሰራዉን ኃጢአቷን ሁሉ እየጻፈች ታስቀምጥ ነበር።

ከእለታት አንድ ቀን የጻፈችዉን ኃጢአቷን ብታየዉ ስንክሳር አክሎ ተመለከተችዉ ስንክሳር ማለት በ365 ቀኖች የሚለዉ የቅዱሳን ታሪክ ሰብስቦ የያዘ ትልቅ መጽሐፍ ነዉ። የዚች ሴትም ኃጢአትም ይህን አክሎ ነበር እንዳየችዉ ደነገጠችና ኃጢአቷን ተሸክማ አባት ወደ አለበት ወደ አንጾኪያ ሄደች አባ ባስልዮስን አገኘችዉ አባቴ በዚህ ያለዉ ኃጢአትሽ ይፋቅልሽ በለኝ አለችዉ።

አባ ባስልዮስም ይፋቅልሽ አላት ገልጣ ብታሳየዉ ሁሉ ተፍቆ አንዲት ኃጢአት ብቻ ቀርታ አየቻት። በጣም ከባድ ኃጢአት ነበረች ሊፈሩዋት የምትከብድ ሊነግሯት የምታሳፍር ነበረች አባቴ ይችሳ አለችዉ አባ ባስልዮስም ይችን ኃጢአትሽንስ ማስተሰረይ የሚችል ልጄ ቅዱስ ኤፍሬም ነዉ ሂደሽ ለእርሱ ንገሪዉ አላት።
አባ ባስልዮስ ይሄን ያላት ኃጢአቷን መፋቅ አቅቶት አይደለም የራሱ ክብር ከሚገልጥ የቅዱስ ኤፍሬም ክብር እንዲገለጥ ፈልጎ ነዉ። ደግሞም ስትመላለስ ንስሐ እንዲሆናት ጭምር ነዉ።
እሷም አባ ባሰስልዮስ እንዳላት ቅዱስ ኤፍሬም ወዳለበት ወደ ሶሪያ ሄደች በባዶ እግሯ እንቅፋቱ እየመታት እሾሁ እየወጋት እግሯ ሲደማ ልብሷን ቀዳ እየጠመጠመች ተጉዛ ከቅዱስ ኤፍርም ደረሰች።

አባቴ በዚህ ያለዉ ኃጢአትሽ ይፋቅልሽ በለኝ አለችዉ ቅዱስ ኤፍሬም ግን ይሄ ለኔ አይቻለኝም ለአባቴ ለአባ ባስለዮስ እንጂ አላት ቅዱስ ኤፍሬም ግን ኃጢአቷን መደምሰስ አቅቶት አይደለም በፈሊጥ ቀኖና ሲሰጣት እንጂ ስትመላለስ ኃጢአቷ እንዲቀልላትም ነዉ። ሂደሽ ለአባ ባስለዮስ ንገሪዉ ይደመስስልሻል አላት እሷም አግኝቸዉ እኮ አይሆንልኝም ብሎ ወደ አንተ ልኮኛል ሳትል እሽ ብላ መንገድ ስትጀምር እንደ ቀድሞዉ በህይወት አታገኝዉም ሙቶ ካህናት ሊቀብሩት ወደ ቤተ ክርስቲያን ይዘዉት ሲሄዱ ታገኝዋለሽ ሳትጠራሪ የተጻፈዉ ኃጢአትሽን ከአስክሬኑ ላይ ጣይዉ አላት እሷም እሽ ብላ ሄደች የቀኑ ሙቀት የሌሊቱ ብርድ እያሰቃያት ደረሰች ሙቶ ካህናት ፍትሀት እየፈቱት አየች።

የእግዚአብሔር አገልጋይ ባስልዮስ ሆይ የባሪያህን ኃጢአት ደምስስልኝ ብላ ከአስክሬኑ ላይ ጣለችዉ አስክሬኑም ድምጽ ወጥቶ ኃጢአትሽ ተደምስሶልሻል አላት ገልጣ ብታይ ተደምስሶላታል። አምላኳን አመሰገነች በደስታ ዘመረች በዚህ በኋላ ዓለምን ንቃ ገዳም ገብታ መኖር ጀመረች።

እንደዚች ሴት ኃጢአቱን የሚያስታዉስ ማነዉ?
ወደ ካህን ሂዶ ንስሐ የገባስ ስንቱ ነዉ?
ስለ ኃጢአቱ በረሃ የተከራተተ ማን ይሆን?

የዚችን ሴት መጨረሻ ያሳመረ የሁላችንም መጨረሻ ያሳምርልን ኃጢአቷን የደመሠሠ የሁላችንም ኃጢአት ይደምስስልን!

ለንስሐ የሚሆን ፍሬ አድርጉ

የዉዳሴ ማርያም አንድምታ ትርጓሜ

"...........እነሆ፥ የተወደደው ሰዓት አሁን ነው፤ የመዳን ቀን አሁን ነው"
--2ኛ ቆሮ 6፥2

🟢 @eotcy 🟢
🟡 @eotcy 🟡
🔴 @eotcy 🔴
እስኪ ልጠይቃችሁ

አንድ ሰው የተጣራ ወርቅ ልሰጣችሁ እመጣለሁና የሆነ ቦታ [ ለምሳሌ ተራራው ሥር ] ጠብቁኝ ቢላችሁ ምን ታደርጋላችሁ ? ወደዚያ ቦታ [ ወደ ታራራው ለመውጣት ] ለመሔድ አስፋላጊ ነው የምትሉትን [ ቅድመ ዝግጅት ] ሁሉ አታደርጉምን ? [ እንዳያመልጣችሁ በጊዜ ሔዳችሁ ]  ቀኑን ሙሉም ቢሆን ቁጭ ብላችሁ አትጠብቁትምን ? 

እግዚአብሔር እሰጣቹዃለሁ ያለው አንድ ሺህ ቅንጣት ወርቅ አይደለም ወይም ምድርን ሁሉ አይደለም።  ከእነዚህ ሁሉ የምትበልጠዋን መንግስተ ሠማያትን ነው እንጂ ...

ታድያ ከዚያ የሚበልጥ ስጦታ ምን አለ ? 🤷🏾‍♂
[ ምንም የለም ]  ይሕን ስጦታ ለማግኘት የማይደክሙ [ ወደ ተራራው የማይወጡ ] ሰዎች እንደምን ያሉ ምስኪኖች ናቸው
| ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ

"...........እነሆ፥ የተወደደው ሰዓት አሁን ነው፤ የመዳን ቀን አሁን ነው"
--2ኛ ቆሮ 6፥2
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
ክርስቶስን ያከበሩ ፣ መንገዱን የተከተሉ ብዙ ሴቶች አሉ፣ እውነትን የመሠከሩ ፣ስለ ቃሉ የኖሩ ብዙ ሴቶች አሉ፣ መስዋዕትነትን የከፈሉ በሰማዕትነት ያለፉ ብዙ ሴቶች አሉ ፣ ታላላቅ የምድር ነገስታትን፣ ታላላቅ ነቢያትን የወለዱ ብዙ ሴቶች አሉ፣ ከዚህ ሁሉ ግን አንቺ ትበልጫለሽ።

ቅድስት ሆይ አንች እኮ:- ሰማይ ዙፋኑ ምድር መረገጫው የሆነ፣ ዓለምን ሁሉ ከሞት ወደ ሕይወት የመለሰ፣ መንበሩን የሚሸከሙ ኪሩቤልና ሱራፌል የሚንቀጠቀጡለት ፣ የሁሉ ፈጣሪ የሁሉ አምላክ እናት ነሽ። በፊትም አሁንም ወደፊትም ካንቺ በቀር ፈጣሪዋን ልጄ ብላ የምትጠራ ሴት አልነበረችም  የለችም አትኖርምም ክርስቶስም እናቴ ብሎ የሚጠራት ብቸኛዋ ሴት አንቺ ነሽ በእውነት ከሁሉ ትበልጫለሽ።

እናት ስትሆኝ ድንግል ድንግል ስትሆኝ እናት በእውነት ከሁሉ ትበልጫለሽ። ትውልድ ሁሉ ብጽዕት ብሎ የሚጠራሽ ብቸኛዋ ሴት በእውነት ከሁሉ ትበልጫለሽ። እግዚአብሔር መርጦና ጠብቆ ያስቀረሽ ዘር በእውነት ከሁሉ ትበልጫለሽ።
ለዓለም ሁሉ ድህነት ምልክት የሆንሽ በእውነት ከሁሉ ትበልጫለሽ።

እናቴ እንግዲህ እኔ ምን ልናገር ሺህ ቃላትን ብደረድር ያንቺን ክብር ልገልፀውስ እንደምን እችላለሁ አዎ አሁንም እላለሁ መልካም ያደረገ ብዙ ሴቶች አሉ አንቺ ግን ከሁሉ ትበልጫለሽ። ምሳ.31:29

የቃልኪዳኗ እመቤት ምልጃዋ አይለየን

https://www.tgoop.com/eotcy
ግንቦት 21 #ደብረ_ምጥማቅ
@eotcy
👉አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም
ግንቦት ሃያ አንድ በዚች ዕለት አምላክን የወለደች እመቤታችን #ቅድስት_ድንግል_ማርያም በደብረ ምጥማቅ የተገለጠችበት ዓመታዊ ክብረ በዓል ነዉ

👉ግንቦት ሃያ አንድ በዚች ዕለት አምላክን የወለደች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በደብረ ምጥማቅ በስሟ በተሠራች ቤተ ክርስቲያን ጉልላት ላይ በብርሃን መርከብ ተቀምጣ ፊቷ በግልጥ ስለመታየቱ የክርስቲያን ወገኖች ሁሉም ታላቅ በዓልን ያደርጋሉ
@eotcy
👉 እርሷም በልጅዋ የመለኮት ብርሃን የተጐናጸፈች ናት በዙሪያዋም የመላእክት ሠራዊት የመላእክት አለቆችም በየማዕረጋቸው ክንፋቸውን ዘርግተው ይቆሙ ነበር ይጋርዷታልም ሱራፌልም ማዕጠንታቸውን ይዘው ለንግሥዋ ገናናነት ይሰግዳሉ በየስግደታቸውም እንዲህ እያሉ ያመሰግኗታል አብ በሰማይ ሁኖ ተመለከተ እንደ አንቺ ያለ አላገኘም አንድ ልጁንም ልኮ ከአንቺ ሰው ሆነ

👉ሁለተኛ ሰማዕታትም በየማዕርጋቸው ረቂቃን በሆኑ ፈረሶቻቸው ተቀምጠው እየመጡ መጀመሪያ ቅዱስ ጊዮርጊስ ከአምባላይ ፈረሱ ወርዶ ይሰግድላታል እንዲሁም ባልንጀሮቹ ሰማዕታት መጥተው ይሰግዱላታል
@eotcy
👉ከእርሱ በኋላ የሚመጣው በዱሪ ፈረስ የሚቀመጥ ይህ መርቆሬዎስ ነው ከዚህም በኋላ ሰማዕታት ሁሉ በመከታተል መጥተው ይሰግዱላታል ምስጋናም ያቀርቡላታል ሁለተኛም ደግሞ ፃድቃን በአንድነታቸው መጥተው በፊቷ ሰግደው ይመላለሳሉ

👉ሄሮድስ የገደላቸው ሕፃናትም መጥተው ይሰግዱላታል በፊቷም እየዘለሉ አንዱ በአንዱ ላይ እየዘለለ በመተቃቀፍም ይጫወታሉ የተሰበሰቡትም በአዩ ጊዜ ደስታ ይመላባቸዋል በሰማይም ያሉ ይመስላቸው ነበር
@eotcy
👉 እናትና አባቱም የሞቱበት ቢኖር ወይም ከዘመዶቹ ወይም ባልንጀራዉ ቅድስት ድንግል እመቤቴ ሆይ ዕገሌን አሳይኝ ብሎ በሚለምናት ጊዜ ቀድሞ በነበረበት መልኩ ያን ጊዜ ታመጣዋለች ደግሞ መሀረባቸውን ወደላይ ይወረውሩላታል የወደደችውንም በእጇ ተቀብላ መልሳ ትጥልላቸዋለች ለበረከትም በየጥቂቱ ይካፈሉታል
@eotcy
👉እንዲህም አምስት ቀን ሁሉ ክርስቲያንም እስላሞችም አረማውያንም ያይዋታል ወደ ቤታቸውም ለመሔድ ሲሹ በፊቷ ሰግደው ይሰናበቷታል እርሷም ትባርካቸውና ይመለሳሉ

👉ለአባቶቻችን የተለመነች እናታችን እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ለኛም ትለመነን ከልጇ ከወዳጇ ታማልደን "አሜን"


👉 ኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶች
#ለቻናሉ_ቤተሰቦቼ 😘

አንድ የቆሎ ተማሪ ይለምን ዘንድ ወደ ከተማዋ ወጣ በእንተ ስሟ ለማርያም እያለ ለመነ የሰጠው የለም ስለ እግዚአብሔር አለ የተመለከተው የለም ሁለም እግዚአብሔር ይስጥህ ከማለት በቀር አንድስ እንኳን የሚላስ የሚቀመስ አጣ በዚህ ተበሳጭቶ ወደ ቤተ ሲሄድ መንገድ ላይ የሚያስተምሩትን አባት አገኛቸው ምነው ልጄ ማዘንህ ቢሉት

ተወኝ የኔታ ከጠዋት ጀምሬ ስንከራተት ዋልኩ ግን እግዚአብሔር ይስጥህ ከማለት ውጪ ምንም አላገኘሁም ኧረ ሰው ከፍቷል አባ አለ ተማሪው

ልጄ ተሞኘህ እግዜር ይስጥህ ከማለት የበለጠ ቸርነት አለን
እግዚአብሔር የሚሰጠውስ ከሰው ጋር እኩል ይሆናልን አሉት ይሄን እያሰበ ወደቤቱ ሄደ ከሁሉ እርሱ እንዳተረፈ ገባው እናም እንዲህ አለ

እግዜር ይስጥህ በሉኝ ✟
የሀገር ሀብታችሁን እየነገራችው ከምታስደስቱኝ
የጣፈጠ ምግብ እያቀረባችሁ ከምትመግቡኝ
በለመለመ መስክ እያስቀመጣችሁ ከምታሳርፉኝ
ስለ ወላዲቷ እግዜር ይስጥህ በሉኝ
ቢበርደኝ የተዋበውን ልብስ አትስጡኝ
ቢጠማኝ ይጠማኝ ዘንድ ውሀ አትስጡኝ
ለእግሬ ጫማ አልፈልግም
ለፊቴ ዘይት አልመኝም
እተኛበት ንፁሕ ፍራሽ እበላ ዘንድ ትንሽ ቁራሽ
አልጠይቅም
ለመኖሬ ማህተም ከሞት ማምለጫ አይሆኑኝም
ይልቁን ከሻታችሁ የልቤን ደስታ
ከገባችሁ የኔ እውነት ምኑም ነገር አይመችም እግዚአብሔር የሌለበት

ቤተሰቦቼ ስለዚህ እኔም ልበላችሁ የምትወዱኝ እህት ወንድሞቸ እግዚአብሔር ይስጥህ በሉኝ በሱ ፈንታ እኔን በማርያም በእናቴ።

በቸር ቆዩልኝ 

ባይሆን ቻናሉን ለወዳጆ በመጋበዝ ካሱኝ🙏

https://www.tgoop.com/eotcy
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
📌 አስራት በኩራት ምንድነው
📌 ጥቅሙስ

መስጠት ማለት በኩራት፣ አስራት፣ መባና ልዩ ስጦታን ለእግዚአብሔር ቤት አገልግሎት እንዲሆን ማቅረብ  ይኸውም ያለንን ነገር ሁሉ ነው። እግዚአብሔር እንደተቀበልን ማሳያና ለእግዚአብሔር ያለንን አክብሮት ፍቅርና አምልኮ የመግለጫ መንገድ ነው።

የስጦታ ዓይነቶችና ትርጉማቸው፦

👉 አስራት
ዘፍ 14፡20፣ ዕብ 7፡4-5
- አስራት በብሉይ ኪዳን ከአስር አንድ እጅ ማለት ነው - ዘፍ 28፡22።
አስራት በአዲስ ኪዳን ግን ከአስር አንድ እጅ ባለፈ በዘራኸው ልክ ነው - 2ቆሮ 9፡6-7
- አስራት የእግዚአብሔር ንብረት ነው - ሚል 3፡8-10
- አስራት የሚሰጡ (የሚያስገቡ) ሰዎች በታማኝነት የእግዚአብሔርን ንብረት መልሰው ለእርሱ የሚሰጡ ናቸው - ዘዳ 14፡22-23
- አስራትን በማስገባት (በመስጠት) ውሰጥ በረከት አለ - ሚል 3፡8-10

👉 በኩራት
በኩር (የመጀመሪያ) ከሚለው ቃል የወጣ ነው። በኩራት የእግዚአብሔር ነው - ዘፀ 23፡19፣ ዘሌ 23፡10-11
- በኩራት መስጠት ማለት እግዚአብሔርን በነገሮቻችን ሁሉ ማስቀደም ማለት ነው - ዘኁ 3፡13፣ ዘዳ 15፡19
- የበኩራት ስጦታ ትዕዛዝ ነው - ዘፀ 13፡2፣ ዘዳ 26፡2
- የመጀመሪያውን ስንሰጥ ያለን ነገር ይባረክልናል - 1ሳሙ 2፡20-21

👉 መባ -
እግዚአብሔር ለእኛ ከሰጠን ገቢ አስራት አውጥተን ከሚቀረው ድረሻችን ላይ ለወንጌል ስራ፣ ለድሆች መርጃ፣ ለቤተ ክርስቲያን አጠቃላይ እንቅስቃሴ የምሰጠው ስጦታ ነው። ይህ አይነቱ ስጦታ በልብ ደስታ በራሳችን ውሳኔ በአቅማችን መጠንና ከዚያም በላይ የምንሰጠው ይሆናል - ዘፀ 25፡1-5፣ 2ቆሮ 8፡1-2፣ ዘፀ 34፡20

👉 የፍቅር ስጦታ
ለእግዚአብሔር ቤት ስራና ለእግዚአብሔር አገልጋዮች ፍቅርን ለመግለጽ የሚሰጥ ሲሆን በተለያዩ ጊዚያቶች ሊደረግ ይችላል - ሐዋ 11፡27-30፣ ፊሊ 4፡16-18

#የምንሰጥበት_ምክንያት እና #አላማ

#እግዚአብሔር_እንድንሰጥ_አዟል - ዘፀ 25፡1-5፣ ዘሌ 25፡31፣ ዘኁ 18፡21ቤት

ስጦታችን የእግዚአብሔርን መንግስት የማስፋፋት ስራና የእግዚአብሔር  አገልግሎት ላይ የሚውል ነው - 1ቆሮ 9፡4-14፣ 2ቆሮ 8፡4፣ ፊሊ 4፡15-18

በመስጠት እግዚአብሔርን እናከብራለን፣ እናመልካለን - ምሳ 3፡9-10

በመስጠት የእግዚአብሔርን በረከት እንለማመዳለን - ሚል 3፡10-12፣ ሉቃ 6፡10ታማኝ

በመስጠት ለእግዚአብሔር  እንሆናለን (አንሰርቀውም) - ሚል 3፡8-10

👉 እንዴት መስጠት እንዳለብን

❗️የምንሰጠው አስቀድመን ራሳችንን ለእግዚአብሔር በመስጠት ነው -

❗️የምንሰጠው በሃዘን (በግድ) ሳይሆን በደስታ ነው -

❗️የምንሰጠው እንደገቢያችን ብቻ ሳይሆን ከጉድለታችንም ጭምር መሆን አለበት -

❗️የምንሰጠው ለሰዎች ለመታየት መሆን የለበትም -

❗️የምንሰጠው በስጦታችን ለመመካት መሆን የለበትም -

ስለ ስጦታ ያስተማረንና አስቀድሞ ያሳየን ራሱ እግዚአብሔር ነው። ከስጦታዎች በላይ የሆነውን ስጦታ ለሰው ልጆች ሰጥቷል (ዮሐ 3፡16-30፣ ሮሜ 8፡32)። ይህ በምድራዊ ቃላት ሊገለጽ የማይችል ስጦታ ላመኑት ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲያገኙ አድርጓል። ቤተ ክርስቲያን ይህንን የምስራች ለአለም ሁሉ ለማድረስ እንድንችልና የእግዚአብሔርን ቤት ስራ እንድትሰራ አማኞች የታዘዙትን የፈቀዱትን ስጦታ ለወንጌል መስጠት አለባቸው።

https://www.tgoop.com/eotcy
+ረፈደ አትበል+

ሰይጣን እኛን ከሚያዘናጋበት መንገድ አንዱ ወደ ጽድቅ የምትሄድበት ጊዜ አሁን ረፍዷል "አሁን እኮ ትዳር መስርተሃል"ብዙ ሀላፊነት አለብህ "ደግሞም ብዙ ጓደኞች አፍርተሃል"እነሱን ትተህ ወዴት ትሄዳለህ?መፅሐፋም እሚለው በጉብዝናህ ወራት ፈጣሪህን አስብ ነው ሆኖም ግን አንተ ወጣትነትህን በአጋጉል ቦታ አሳልፈኸዋል "አሁን በቃ መንፈሳዊነት ካንተ protocol ጋር አይሄድም ፣በዚያ ላይ ያልሰራኸው ሀጢያት የለም ፣እንዴት ፈጣሪስ ይቅር ይልሀል ? እያለ ከተተበተብንበት የሀጢአት እስራት እንዳንወጣ የተቻለውን ያደርግል። እኛም ደግሞ ከዚህ ለመውጣት የተቻለንን አናደርግም! 😓


ወንድሜ ስማኝማ ልንገርህ አብርሃም የሀጢአት ምሳሌ ከሆነችው ከካራን በ 75 አመቱ ነው ነበር የወጣው፣ ከአገርህ ከዘመዶችህ ከአባትህ ቤት ተለይተህ እኔ ወደማሳይህ ምድር ውጣ ሲለው ምክንያት አልደረደረም ፣እሺ ብሎ ነው የወጣው ። ወንድሜ በሃጢአት ያረጀህ ከመሰለህ ፣እንደ አብርሃም 75 ዓመት አልሞላህምና ተቻኩለህ ቶሎ ውጣ ፤ እንደ ሀገር መኖርያ ካደረከው በደል ቶሎ ውጣ !አባትና እናትህን ማክበር አስትተው አባት እና እናት ከሆኑብህ ኃጢያቶች ቶሎ ውጣ!!

ብቻ አንተ ውጣ እንጂ ፣ አንተን ታላቅ ሕዝብ ማድረግ ፣ ከነዓን ማስገባት ለእግዚአብሔር አይሳነውም ። የእርሱ ወዳጅ ስትሆን አብዝቶ ይባርክሃል በል ቶሎ በል ወንድሜ ዛሬውኑ ከካራን ውጣ እግዚአብሔርንም ይዘህ ጉዞ ወደ ከነዓን ጀምር !!!
         
   ውጣ ውጣ እባክህ ወንድሜ ረፈደ አትበል !ውጣ!!!
          ውጪ ውጪ እህቴ ረፈደ ሳትይ ውጪ !!!
እባካችሁን ወንድም እህቶቼ እንውጣ 🙏
መልዕክቱን ለጓደኞቻችሁም አስተላልፉ ዳግም።
    (ስላነበባችሁት አመሰግናለሁ )
       ፣ተግባር ላይ ለማዋል እንጠንክር ችላ አንበል። 🥰
"...........እነሆ፥ የተወደደው ሰዓት አሁን ነው፤ የመዳን ቀን አሁን ነው"
--2ኛ ቆሮ 6፥2

https://www.tgoop.com/eotcy
እውነት እስኪ ይችን እውነታ አንብቡልኝ

ኤልሳቤጥም የማርያምን ሰላምታ በሰማች ጊዜ መንፈስ ቅዱስ ሞላባት አሰምታም እንዲህ አለች ከሴቶች መካከል ተለይተሽ የተባረክሽ ነሽ የማህጸንሽም ፍሬ የተባረከ ነው የጌታየ እናት ወደኔ ትመጣ ዘንድ እንደት ይሆናል
የሰላምታሽ ድምፅ ወደኔ በመጣ ጊዜ ጽንሱ በማህጸኔ ዘሏልና" ሉቃ.፩÷፳-፵፫🙏
#ልብ_በሉ ሰላምታዋ መንፈስ ቅዱስን የሚሞላ ሴት እንደት የተመረጠች ናት
በመንፈስ ቅዱስ የተሞላች አረጋዊት ሴት አንች ከሴቶች መካከል ተለይተሽ የተባረክሽ ነሽ የምትባል ሴት እንዴት አይነት መመረጥ ነው በኤልሳቤጥ ብቻ አይደለም መልአኩ ቅዱስ ገብርኤልም ይህንኑ ቃል አንቺ ከሴቶች መካከል ተለይተሽ የተባረክሽ ነሽ ብሏታል ምን አይነት መመረጥ ነው
ሰላምታዋን በሰማ ጊዜ በማሕጸን ያለ ጽንስ እንኳ በደስታ የዘለለ ምን አይነት ቅድስና ነው
@eotcy
ታዲያ በመንፈስ ቅዱስ ተሞልታ ኤልሳቤጥ ካመሰገነች ድንግል ማርያምን ፕሮቴስታንት አላመሰግንም የሚል ምን ተሞልቶ ነው
በመልአኩ አንደበት ጸጋን የተሞላሽ ሆይ ደስ ይበልሽ እግዚአብሔር ካንቺ ጋር ነውና፤ አንች ከሴቶች መካከል ተለይተሽ የተባረክሽ ነሽ የተባለችን እናት እኛም እንደመልአኩ እናመሰግናታለን።
እኛስ መንፈስ ቅዱስን ተመልታ እመቤታችንን
እንዳመሰገነቻች ኤልሳቤት እንደ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል እናመሰግናታለን መንፈስ ቅዱስ እመቤታችንን እንድትመሰገን
ሲያደርግ አይተናል። የጌታዬ እናት እንላታለን በመንፈስ ቅዱስ ሆና የጌታዬ እናት አንች ወደኔ ትመጭ ዘንድ እንደት ይሆንልኛል፤ አንች ከሴቶች መካከል ተለይተሽ የተባረክሽ ነሽ፣ የማህጸንሸ ፍሬ የተባረከ ነው.....እያልን እናመሰግናታለን
ይህን ያደረገ መንፈስ ቅዱስ እንደሆነ በግልፅ አይተናልና።
@eotcy
ሰማያዊ መልአክና ምድራዊት ሴት ተባብረው በአንድ ቃል በአንድ መንፈስ ቅዱስ ያመሰገኗትን አላመሰግንም የሚሉ በምን መንፈስ ሆነው ነውመንፈስ ቅዱስ እመቤታችንን አስመሰገነ እንጅ ሲከለክል አላየንም። አላመሰግንም የሚሉ ከምን እንዳገኙት እንኳ አይነግሩንም።
ሰይጣንና ክፉ የገንዘብ ፍቅር ክብሯን ሸፍኖባቸዋልና።
እኛ ግን ከመጽሐፍ ቅዱስ እንደተረዳነው እንደ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤልና ቅድስት ኤልሳጼጥ እናመሰግናታለን።
ሁላችችንም እንደ ቅዱስ ዮሐንስ በእምነት ወደቤታችን ወስደናታል

"...........እነሆ፥ የተወደደው ሰዓት አሁን ነው፤ የመዳን ቀን አሁን ነው"
--2ኛ ቆሮ 6፥2

@eotcy    @eotcy
@eotcy    @eotcy
@eotcy    @eotcy
@eotcy    @eotcy
"ባልሽን የገደልሽው መርዟ አንች ነሽ"

ከለታት አንድ ቀን አንዲት ውብ የሆነች ልጃገረድ ባገባች በ ሁለተኛው ዓመት ትዳሯ ምርር ስላላት ባሏን ለመግደል ፈለገች።

ይህች ቆንጆ ልጅት አንድ ቀን ጠዋት ወደ እናቷ ቤት ብርር ብላ በመሄድ፦ "እማዬ የባሌ ነገር አድክሞኛል የሚያደርጋቸው የማይረባ ነገሮች ሰልችተውኛል ለኔ አያስብልኝም ዞር ብሎ አያየኝም እኔንጃ ከሌላ ሴት ጋር የጀመረው ነገር አለ እርሱን ገድዬ መገላገል ፈልጋለው በሌላ በኩል ህግ ያስረኛል ብዬ እፈራለው እባክሽ እርጂን " አለቻት።

እናቷም "እሺ ውድ ልጄ እረዳሻለው ነገር ግን አንዳንድ የምታደርጊያቸው ነገሮች አሉ"። አለቻት።

ልጅቷም " አንቺ ያልሽኝን ሁሉ አደርጋለው አለች"

እናትየውም "ባልሽ ሞቶ ሬሳው ከቤትሽ እስከሚወጣ ድረስ ከዛሬ ጀምሮ የምታደርገውን 6 ነገሮች በጥንቃቄ ፈጽሚው አለች፦

1. የገደለችው እሷናት ብለው ጎረቤት እንዳይጠረጥሩሽ ከአሁን ሰዓት ጀምረሽ ከባልሽ ጋር ሰላም ፍጠሪ

2. ሁልግዜ ውበትሽን ጠብቀሽ ወጣትና ቆንጆ ሆነሽ ታይ

3. በደንብ አድርገሽ ተንከባከቢው ጥሩ ሁኚለት አበረታችው

4. ትዕግስት አድርጊ ብዙም አትቅኚ ብዙ ግዜ አዳማጭ ሁኝ በማክበር ታዘዥው

5.በእጅሽ ያለውን ገንዘብ ለእሱ ጥቅም ብቻ አድርጊው እንዲች ብለሽ ለራስሽ እንዳትጠቀሚ ገንዘብ ከከለከለሽ አትናገሪ ዝም በይ

6. ማንም ገድላዋለች ብሎ እንዳይጠረጥርሽ የጭቅጭቅና የጩኸት ድምፅ አታሰሚ ሰላምና ፍቅር ብቻ ከአፍሽ ይውጣ ... እስከ ምትገላገይው ድረስ ብቻ ነው።

እናትዮዋ፦ በድጋሚ "ሳታዛንፊ ያልኩሽ ታደርጊያለሽ?" አለቻት።

ልጅቷም " እሱ ብቻ ሞቶ ሬሳው ይውጣልኝ እንጂ አደርገዋለሁ" አለች።

እናትየዋም የሆነ ብልቃጥ እየሰጠቻት፦ " ይህንን መርዝ ያዥው ቀስ እያለ ውስጡን አመንምኖ እንዲገድለው በየቀኑ ምግቡ ውስጥ ጠብ እያደረግሽ ስጭው" አለች።

ልጅቷም ድስ እያላት ወደ ቤቷ ተመለሰች።

ከአንድ ወር ብሓላ ልጅቷ ወደ እናቷ ቤት ተመልሳ መጣች። እንዲህ አለቻት" ወይ ጉድ ሰውዬው ወሬ ሰምቶ ይሁን ወይ ቀልቡ ነግሮት? ድሮ ዞር ብሎ የማያየኝ ሰውዬ ፣ ፍቅሬ፣ማሬ ፣ወለላዬ፣ ህይወቴ፣ ንግስቴ፣ በዓለም ላይ የምታክልሽ ሴት የለችም ይለኝ ጀምሯል ብቻ እኔንጃ ጸባዩ ልውጥ አለብኝ"

እናትየውም፦ መርዙን እየሰጠሽው ነው? አለቻት

ልጅቷም አይኗ ላይ እንባ እየቀረረ ፦ አዎ ግን አሁን ጸባየ ሸጋ ጣፋጭ አፍቃሪ ባል ሆኗል እንዲሞትብኝ አልፈልግም ማርከሻ ሌላ መድሃኒት ካለ ፈልጊልኝ እባክሽ ጸጸቱ ሊገለኝ ነው።

እናትየዋ፦  ልጄ በብልቃጥ የሰጠሁሽ መርዝ አይደለም የእርድ ዱቄት ነው። ነገር ግን ቀስ በቀስ ጸባየ መጥፎውን ባልሽን የገደልሽው "መርዟ አንቺ ነሽ" ማለቴ እሱን ማፍቀር ፣ መታዘዝ፣ መንከባከብ፣ መታገስ፣ ማክበር እና ውብ ሆነሽ ስትገኚ ባልሽን መለወጥ ችለሻል። አንቺ ለሌላው ሰው ምንም ነገር ሳትሰጭ እንዴት ከሌላ ሰው ያልሰጠሽውን ትጠቢቂያለሽ? ፍቅር ማለት ሰጥቶ መቀበል ነው። ቅድሚያ ግን መስጠት ያስፈልጋል ፍቅር ከሰጠሽው ፍቅር ታገኝያለሽ ጸብና ጭቅጭቅ ይዘሽ የምጠብቂው ከሆነ ያንኑ ታገኛለሽ።
ምላሽ ሳትጠብቂ ከራስሽ አስበልጠሽ በሁሉም ነገር ባልሽን አስቀድሚ ፍቅር ስጭው!

እንዲህ በጥበብ ትዳርን የሚያክል ተቋም የሚታደጉ እናቶችን፣ አባቶችን እግዚአብሔር ያብዛልን።አሜን!

ብታጋሩት መልካም ታደርጋላችሁ።

"...........እነሆ፥ የተወደደው ሰዓት አሁን ነው፤ የመዳን ቀን አሁን ነው"
--2ኛ ቆሮ 6፥2

@eotcy
@eotcy
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
#አምናለሁ_እና_አላምንም +

ልጁ የታመመበት አባት ነው። ጌታን " #ቢቻልህስ_ልጄን_ፈውስልኝ " አለው:: ኢየሱስም፦ ቢቻልህ ትላለህ፤ ለሚያምን ሁሉ ይቻላል፡ አለው።

ይህን ጊዜ ሰውዬው  " #ወዲያውም_የብላቴናው_አባት_ጮኾ#አምናለሁ_አለማመኔን_እርዳው፡ አለ" ማር. 9:24

የዚህ ሰውዬ ንግግር ፍቺ የሚፈልግ ቅኔ ይሆንብኛል " #አምናለሁ_አለማመኔን_እርዳው "

ይኼ ሰውዬ ያምናል ወይንስ አያምንም

ያምናል እንዳንል " #አለማመኔን " ይላል ፤ አያምንም እንዳንል " #አምናለሁ " ይላል። የቸገረ ነገር ነው ሁሉን አዋቂው መድኃኔዓለም  ምን ለማለት እንደፈለገ ገብቶት ልጁን ፈወሰለት:: እኔ አላዋቂው ግን " #አምናለሁ_አለማመኔን_እርዳው " የሚለውን ቃል እየደጋገምኩት ቀረሁ::

እያመኑ አለማመን እንዴት ያለ ነው ብዬ መላልሼ ሳጤነው ግን ሰውዬው #የእኔኑ ድክመት እየተናገረ እንደሆነ ገባኝ::

አምናለሁ እላለሁ:: በእርግጥም በፈጣሪ መኖር አምናለሁ:: ሁሉን እንደሚችልም አምናለሁ::
ግን ደግሞ በእርሱ ታምኜ አላውቅምና በሥራዬ እክደዋለሁ:: ኑሮዬ  "በሥራቸው ይክዱታል" ከተባሉት የሚመደብ ነው:: (ቲቶ 1:16) አቅዋሜ የማመን ኑሮዬ ያለማመን ነውና አምናለሁ አለማመኔን እርዳው ብል ለእኔ የሚገባ ጸሎት ነው::

ወረደ ተወለደ ተጠመቀ ተሰቀለ ሞተ ተነሣ ዐረገ ብዬ አምናለሁ:: በትሕትና መውረድን ፣ በንስሓ መወለድን ፣ በታናሽ እጅ ዝቅ ብሎ ጽድቅን መፈጸምን ፣ መከራን በትዕግሥት መቀበልን ፣ ከመከራ ሞት ወዲያ ተነሥቶ በክብር ከፍ ማለትን ግን እኔ ሕይወት ላይ #አላውቀውም:: #የምተርከው_ክርስቶስ_እንጂ_የሚተረክ_ክርስትና_የለኝም:: ስለዚህ አምናለሁ አለማመኔን እርዳው በልኬ የተሰፋ ጸሎት ነው::

#መች_በዚህ_ያበቃል::

እጾማለሁ አለመጾሜን እርዳው::
ከምግብ እጾማለሁ ከኃጢኃት ግን አልጾምም:: ሥጋ መብላት ትቼ የሰው ሥጋ በሐሜት የምበላ ነኝና እጾማለሁ አለመጾሜን እርዳሁ እላለሁ::🙏

እጸልያለሁ አለመጸለዬን እርዳው::🙏
ቆሜ የማደርሰው ጸሎትስ አለኝ:: ግን ልቤ ሠላሳ ቦታ ደርሶ ይመለሳል:: የምጸልየው ማናገር የማልፈልገውን ሰው በግድ የማናግር ያህል የግብር ይውጣ እንጂ ነፍሴ እርሱን ሽታ አይደለምና እጸልያለሁ አለመጸለዬን እርዳው🙏 እላለሁ::

እሰግዳለሁ አለመስገዴን እርዳውስ?
ላቤ እስኪወርድ ሰግጄ አውቃለሁ:: ልቤ ግን አንዴ አልሰገደም:: 😭

ጌታ ሆይ እመጸውታለሁ አለመመጽወቴን እርዳው::🙏
እዘምራለሁ አለመዘመሬን እርዳው::🙏
አስቀድሳለሁ አለማስቀደሴን እርዳው::🙏
እማራለሁ አለመማሬን እርዳው::🙏
ሆኜ ያልሆንሁትን አድርጌ ያላደርግሁትን ሁሉ አንተ ታውቀዋለህና እርዳኝ::

"...........እነሆ፥ የተወደደው ሰዓት አሁን ነው፤ የመዳን ቀን አሁን ነው"
--2ኛ ቆሮ 6፥2

@eotcy
@eotcy
@eotcy
ክርስቲያን ከሆንክ እነዚህን 7 ነገሮች መቼም አታድርግ

1. ለንስሐ ተዘጋጅ ወደ ቤተክርስቲያን ና ወገብህን ሱሪህን ታጠቅ

2. ነገርን ሁሉ በ3ቱ መሥፈርት ሳትመዝን አትቀበል
☞︎︎︎ መጽሐፍ ቅዱስ
☞︎︎︎ አዋልድ መጻሕፍት
☞︎︎︎ ቅዱስ ትውፊት

3. ለማብዛትም ሆነ ምን አለበት ብለህ መቼም ቢሆን
☞︎︎︎ ከአህዛብና
☞︎︎︎ ከመናፍቃን
ጋር አትተባበር። እነርሱ ካሉ እግዚአብሔር ይለይሃልና❗️
ብርሃን ከጨለማ ጋር ህብረት የለውምና❗️

4.ምንም ነገርን ከመቀበልህ ከመንቀፍህና ከመደገፍህ በፊት:-
☞︎︎︎ እንደ ክርስቲያን ለፈጣሪህ ንገር
☞︎︎︎ እንደ ሰው አገላብጠህ መርምር

5.ከእግዚአብሔር እና የርሱ የሆኑት በቀር ፈጽመህ ምስጢርህን አትግለጽ❗️
ኋላ ተወግተህ የምትሞተው ባወጣኸው ምስጢር:- አመንኩት ባልከው ሰው ነውና❗️

6.የቤተክርስቲያንን ሥርዓት ትጠብቅ ታስጠብቅም ዘንድ ቸል አትበል❗️
አጥሩ ከፈረሰ ቤቱም መፍረሱ ፣ መዘረፉም አይቀርምና❗️

7.በሰማይ ካለው እግዚአብሔር እና ወዳዶቹ በቀር በሥጋ ለባሽ አትታመን❗️ አትከተለው፣ አታድንቀው፣ አታምልከው

በዚች በተቀጥተኛዋ ሀይማኖታችን ፀንተን የመንግስቱ ወራሾች ያድርገን

ወሰብሐት ለእግዚአብሔር

"...........እነሆ፥ የተወደደው ሰዓት አሁን ነው፤ የመዳን ቀን አሁን ነው"
--2ኛ ቆሮ 6፥2
➲ ልብ የሚነካ አሳዛኝ ታሪክ 😢


🚺 በጣም ከወደድኩት ታሪክ ላጋራችሁ

እናቱን የሚወድ ሁሉ ሊያነበው የሚገባ ፅሁፍ መልካም ንባብ

ከባለቤቴ ጋር ትዳር ከመሰረትን 21 ዓመት ሞላን ባለቤቴ አንድ እራሴን እንድፈትሽበት ያደረገኝን ጥያቄ አቀረበችልኝ ሃያ አንድ ዓመት ካንተ ጋር ስኖር አንድም ቀን ከእናትህ ጋር ለመዝናናት ስትወጣ አይቼክ አላውቅም ዛሬ ማታ እናትህን እራት ምሽት ጋብዛትና አዝናናት አለችኝ።

ውዷ ባለቤቴ ባቀረበችልኝ ሃሳብ ከመገረም በላይ መሰጠኝ ተስማማሁኝ እናም ወደ እናቴ ጋር ደወልኩላት እማ ዛሬ ካንቺ ጋር ሽርሽር መውጣት ፈልጋለሁ አልኳት ደነገጠች "ምነው ሰላም አይደል ልጆችሕ ምን ሆኑ ባለቤትህስ ሰላም አይደለች እንዴ ?" በማለት የድንጋጤ ጥያቄዎቿን አርከፈከፈችብኝ።

አብሽሪ እማ ሁሉም ሰላም ነው ካንቺ ጋር ለመዝናናት ፈልጌ ነው"አልኳት በጣም ደስ አላት ተስማማች ወደማታ ተዘጋጅተሽ ጠብቂኝ አልኳት በቀጠሮዬ ሰዓት ወደ እናቴ ጋር ሄድኩኝ እናቴ በረንዳው ላይ ቆማ እየጠበቀችኝ ነበር እናቴ ሁለመናዋ ተቀያይሯል እርጅና ተጫችጭኗታል ሰላምታ ከተለዋወጥን በኋላ ወደ መኪናዬ አስገብቺያት ጉዞ ጀመርን።

እናቴ በጣም ደስታ ይነበብባታል "ልጄ ዛሬ ካንተ ጋር ሽርሽር እንደምወጣ ለሰፈር ሰዎች ሁሉ እንዲሁም ለዘመድ አዝማዶቼ በሙሉ ተናግርያለሁኝ" በጣም ከመደሰቷ የተነሳ አንድም የምታውቀው አልቀራትም ወሬውን ለሁሉም አዳርሳዋለች ወደ ሆቴል ይዥያት ሄድኩኝ አስተናጋጁ የምግብ ዝርዝር ወረቀት የያዘ ኩፖን ሰጠን "እማ ምረጪ" አልኳት ፈገግ አለች ከእርጅና የተነሳ ማየት እንደማትችል ተረዳሁ ላንብብልሽ አልኳት "ልጅ እያለህ ሆቴል ቤት ገብተን ልንመገብ ስንል የምግብ ዝርዝር አነብልህ ነበር አሁን እዳህን ክፈል" ብላ ፈገግ አለች እኔም ፈገግ ብዬ አነበብኩላት።

የለበሰችውን ልብስ ስመለከት ከአስራ ዘጠኝ ዓመት በፊት የሞተው አባቴ የገዛላት የመጨረሻ ልብሷ እንደነበር አስታወስኩ ምግቡ ቀርቦ እናቴ ከደስታ የተነሳ ምንም እየበላች አልነበርም ደስታ በደስታ ሆናለች
በሕይወቴ እኔም በጣም የተደሰትኩበት አጋጣሚ ነበር ከእናቴ ጋር ተዝናንተን ስናበቃ ይህ ምሽት እንዲደገም ፈልጌ "እማ መቼ ተመልሼ ልምጣና ልውሰድሽ..?" አልኳት በእንደዚ ቀን ና ነገር ግን እኔ ነኝ የምጋብዝህ ከተስማማህ ና " አለቺኝ ፈገግ አልኩኝ ትጋብዥኛለሽ አልኳትና ተለያየን።

በመሃል እናቴ ታመመች ከህመሟ ድናልኝ አብርያት የማሳልፍበትን
ምሽት ናፈቀኝ ነገር ግን ከእናቴ ጋር ዳግም አልወጣንም እናቴ ወደ
ማይቀረው የሞት ጉዞ ተጓዘች በጣም አዘንኩ አለቀስኩ ከእናቴ ጋር ቀጠሮ ይዘን ወደነበረው ምሽት ከአንድ ታዋቂ ሆቴል ቤት ተደወለልኝ ዛሬ እራት ከባለቤትህ ጋር በነፃ ተጋብዛቹሃል።
@eotcy
ግራ ተጋባው ማነው እንዴት ለማንኛውም እሺ እንመጣለን ብዬ ስልኩን ዘግቼ ምሽት ላይ ከባለቤቴ ጋር ሄድኩኝ ግብዣው ከደብዳቤው ጋር ቀረበልን ደብዳቤውን ከፈትኩት እንዲህ ይላል :-"ልጄ ሰላም ላንተ ይሁን የእራቱን ግብዣ ስንቀጣጠር መገኘት እንደማልችል አውቅ ነበር
የሞት ቀጠሮዬ እየተቃረበ እንደነበር ነፍሴ ይነግረኝ ነበር ልጄ ይኸው እኔ በቃሌ መሰረት ጋብዥሃለው በኔ ፋንታ ውዷባለቤትህ አብራህ እንድትሆን ፈቅጃለሁ!" ይላል ሳይታወቀኝ እንባዬ ወረደ አለቀስኩ 21 ዓመት ሙሉ የዘነጋሁትን ውድ ዕቃ አሁን ነው ማጣቴን ያወኩት...!
@eotcy
ስንቶቻችን ይሆን ካገባን በኋላ እናቶቻችንን ወላጆቻችንን የምናስታውሰው ? ...ስንቶቻችን ነን ለራሳችን ስንሯሯጥ ወላጆቻችንን የረሳነው..? ስንቶቻችንስ ነን የእናት ፍቅር ያልገባን
ወላጆቻችን በህይወት ያሉ መቼም አይደለም ጊዜው አሁን ነው

እባካቹህ ሀሳባቹህን አካፍሉን🙏 👇👇 @eotcy_comment


"...........እነሆ፥ የተወደደው ሰዓት አሁን ነው፤ የመዳን ቀን አሁን ነው"
--2ኛ ቆሮ 6፥2
ጉድለትህን ተጠቀምበት

ዘኪዎስ በማጠሩ ምክንያት በኢያሪኮ እያለፈ ያለውን ክርስቶሰን ለማግኘት ተቸገረ። ሕዝቡ ብዙ ነው የቆሙት ሁሉ ጌታን ከማየት ከለሉት። የሾላ ዛፍ ላይ ወጥቶ ጌታን ለማየት ሲሞክር ጌታ አሻቅቦ አየው።

እሱ ዛፍ ላይ ሊያይ እንጂ ሊታይ አልወጣም። ጌታ ሊታዩ ከሚሞክሩ ይልቅ ሊያዩት የሚሹትን ይወዳልና ዘኪዎስን ጠራው።

ከምድር ቆመን ዓይናችንን አንጋጥጠን ማረን የምንለው ጌታ ዘኪዎስን ከምድር ሆኖ ወደ ላይ እያየ ና ልማርህ አለው።
"ዛሬ በቤትህ እውል ዘንድ ይገባኛል" አለው። ጌታ ወደ ቤቱ ገባ ለዘኪዎስ ቤት መዳን ሆነለት።

ዘኪዎስ አጭር ባይሆን ኖሮ ከሰዎች ጋር እየተጋፋ ጌታን ያይ ይሆናል እንጂ በጌታው ዓይን ለመታየት የሚያበቃ ትጋት አያሳይም ነበር። ምናልባትም ሰዎችን ገለል በሉ እያለ በኩራት ሲጋፋ ከአንዱ ጋር ሊጣላ ሊቆይ ይችል ነበር።

ዘኪዎስ አጭር ባይሆን ኖሮ ከዛፍ ላይ አይወጣም ነበር።
ዘኪዎስ አጭር ባይሆን የሠራዊት አምላክ ወደ ቤቱ አይገባም ነበር። በኪሩቤል ላይ የሚቀመጠው ንጉስ በቤቱ ወንበሮች ላይ የተቀመጠው ዘኪዎስ በማጠሩ ምክንያት ነው። የዘኪዎስ ነፍስ የዳነው በቁመቱ ማጠር ነበር።
እግዚአብሔር የማዳኑን ቀን የቆጠረለት ቁመቱን ሲያሳንሰው ነበር። በምድር በመጽሐፍ ቅዱስ በሰማይ በሕይወት መዝገብ ስሙ የተጻፈው ዘኪዎስ አጭር በመሆኑ ነው።

ስለ ቁመቱ የማወራ እንዳይመስልህ።
ለነፍሳችን መዳን የሚያሳጥርብን ብዙ ነገር አለ። እንደ ዘኪዎስ ቁመትህ አጭር ባይሆን የሚያጥርህ ነገር ግን አይጠፋም።

ይሄ ጎደለኝ የምትለው ከሰዎች አነስኩበት የምትለው ነገር አንዳች ነገር የለም እሱን ማለቴ ነው። ይሄ ይጎለኛል ከሰው አንሳለሁ እያልክ አትማረር እጥረትህ መክበሪያህ ነው። ጉድለትህም መዳኛህ ነው።
ችግሮችህ የእግዚአብሔርን ቸርነት ምታባቸው መስታዎቶችህ ናቸው

እግዚአብሔር ያጎደለብህ የመሰለህ ነገር ወደ ዛፍ እንድትወጣ ምክንያትህ ይሁን። በጉድለትህ እንደ ዘኪዎስ ከፍ በልበት። ያኔ ሰዎች አንተን አንጋጠው ከማየት ውጪ አማራጭ አይኖራቸውም።
ፈጣሪ በፍቅሩ ይይህ እንጂ ሰዎች ወዳንተ ያዘነብላሉ።
በቤትህ መዳን ይሆንልሀል፡፡ ከዚያም ስላጠረህ ስለተጎዳህ ነገር ፈጣሪህን ስታመሰግነው ትኖራለህ።

እመነኝ አንዳንድ ጉድለቶች እድሎች ናቸው። ዘኪዎስ አጭር ባይሆን ይሄኔ በሾላው ዛፍ ጥርሱን እየፋቀ ይቀር ነበር።

"...........እነሆ፥ የተወደደው ሰዓት አሁን ነው፤ የመዳን ቀን አሁን ነው"
--2ኛ ቆሮ 6፥2


@eotcy
@eotcy
@eotcy
ሁለት የሚዋደዱ ጓደኛሞች በረሃ ውስጥ እየተጓዙ እያሉ ድንገት አለመግባባት ተፈጠረና አንደኛው አንደኛውን በጥፊ ይመታዋል። የተመታው ጥፊው ቢያመውም ምንም ሳይናገር ዝም አለና
አሸዋው ላይ ዛሬ የምወደው ጓደኛየ በጥፊ መታኝ ብሎ ፃፈ ከዛም እየተጓዙ እያሉ ትልቅ ባህር ያለበት ወንዝ ያገኙና መታጠብ ፈልገው ይገባሉ እየዋኙ እያሉ ያ በጥፊ የተመታው ልጅ ይሰምጣል በዚህ ስዓት ጓደኛው እንደምንም ብሎ ሂወቱን ያተርፈዋል ከሞት የተረፈው ልጅ ቋጥኝ ድንጋይ ፈልጎ ድንጋዩ ላይ እየፈለፈለ ዛሬ የምወደው ጓደኛዬ ሕይወቴን አተረፈኝ ብሎ ፃፈ ጓደኛውም ገርሞት ቅድም በጥፊ ስመታህ አሸዋ ላይ ፃፍክ አሁን ከሞት ሳተርፍህ ደግሞ ድንጋይ ላይ ለምን እንደዚህ አደረክ አለው። ጓደኛውም እንዲህ አለው የምንወዳቸው ሰዎች ሲበድሉን በደላችንን የይቅርታ እና የምህረት ንፋስ እንዲያጠፋው አሸዋ ላይ መፃፍ አለብን ጡሩ ነገር ሲያደርጉልን ግን ውለታቸውን እንዳንረሳ ሁሌም እንድናስታውሰው ድንጋይ ላይ መፃፍ አለብን አለው።

ባለህም በሌለህም ነገር ሁሉ አመስግን አንተ አለህና።
ሰላሙን ያምጣልን ሀገራችንን ሰላም ያርግልን
https://www.tgoop.com/eotcy
2025/02/22 08:32:39
Back to Top
HTML Embed Code: