ETHIOPIANARCHITECTUREANDURBANISM Telegram 15095
የወላይታ ሶዶ ከተማ የቶፖግራፊ ካርታ ዝግጅት

የወላይታ አውራጃ ካርታ እንዲነሣ እና የሰባቱ ወረዳዎች ይዞታ በካርታው ላይ እንዲሰፍር ካደረግሁ በኋላ፣ ለሶዶ ከተማ ዘመናዊ ማስተር ኘላን ወደ ማዘጋጀት ዕቅዴ ገባሁ፡፡ ለሶዶ ከተማ ዘመናዊ ማስተር ፕላን እንዲዘጋጅ ማድረግ የከተማዋ ዕድገት በዕቅድ እንዲመራ ያግዛል፡፡ ለዚህ ሥራ ደግሞ አስቀድሞ የቶፖግራፊ ካርታ መዘጋጀት አለበት፡፡ የቶፖግራፊ ካርታውን ለማዘጋጀት ሰርቬየሮች ከአገር ግዛት ሚኒስቴር የማዘጋጃ ቤቶች ክፍል እንዲሰጡኝ ብጠይቅ ግን ፈቃደኛ ሳይሆኑ ቀሩ፡፡ለአስተዳደሩም ሆነ ለሕዝቡ አመች እንዲሆን አውራጃውን በአዲስ መልክ ለማዋቀር ከአገር ግዛት ሚኒስቴር ፈቃደኝነት ሳጣ፣ ቀደም ብሎ የአውራጃውን ካርታ በማንሳት ወደ ተባበሩኝ መሥሪያ ቤቶችና ድርጅቶች ፊቴን አዞርኩኝና እንዳለፈው ጊዜ ሁሉ የሥራ ሰዓት ሳይጠብቁና ቅዳሜ፣ እሁድ፣ የበዓል ቀን ሳይሉ፣ ለሶዶ ከተማ ማስተር አጠናቀቁልን፡፡ ባለሙያዎቹ የሕዝብና ቤት ቆጠራውን ስለአካሄዱልን እንዲሁም ፕላን ሥራ አስፈላጊ የሆነውን የቶፖግራፊ ካርታ ሥራ በአጭር ጊዜ ውስጥ ሌሎች ብዙ የልማት ሥራዎችን በዕቅድ ለማከናወን የሚያስፈልገውንና ለልማት ሥራ መሠረት የሆነውን የአውራጃውንም ሆነ የሶዶ ከተማን ካርታ ስላነሱልንና ለወላይታ አውራጃ ልማት ከፍ ያለ አስተዋፅኦ ስላደረጉ ባለውለታዎች ናቸው፡፡ በጊዜው ምስጋና ያቀረብኩላቸው ቢሆንም እዚህ ላይ ስማቸው ሲጠራ እንዲኖር ደግሜ አመሰግናቸዋለሁ፡፡ ሥራውን አጠናቀው ሲያስረክቡንም አብረው የመሐንዲስ የሥራ መሣሪያዎችን ጭምር ለግሰውናል፡፡

#የመሐንዲስ የሥራ መሣሪያዎቹን ልገሳ ያደረጉልን፣ የውኃ ልማት መሥሪያ ቤት ሄጄ የካርታ ሥራ ባለሙያዎቹን ርዳታ በጠየኩበት ወቅት ከዕቃ ግምጃ ቤታቸው የመግባት እድል አጋጥሞኝ ነበር፡፡ መሥሪያ ቤቱ በርዳታ ያገኛቸው ብዙ የቅየሳ መሣሪያዎች(ቴዎዶላይቶች፣ ጃሎዎች፣ ስታድያዎችና ባለመቶ ሃምሳና ሰላሳ ሜትር፣ አደጋ የሚችሉ እና ለገጠር ሥራ አገልግሎት የተሠሩ ጥቅል ሜትሮች) የዕቃ ግምጃ ቤቱን ያጨናነቁት መሆኑንም አይቼ ነበር፡፡ ስለዚህ የውሀ ልማት ባለሙያዎች ወደ አውራጃው ይዘዋቸው የሄዱትን የቅየሳ መሣሪዎች እዛው ለአውራጃው ግዛት ለልማት ሥራ አገልግሎት እንዲውሉ፣ ያንበሳ ልመና ጋማ ይዞ እንደሚባለው ሆኜ ሥራው ሲያልቅ መሣሪያዎቹን ሁሉ ትተውልን እንዲሄዱ አድርጌያለሁ፡፡

#የባለሙያዎቹ ኃላፊ የነበረው ስሙን የዘነጋሁት መሐንዲስ እስከቅርብ ጊዜ ድረስ ባየኝ ቁጥር «ባገለገልን ፈንታ መሣሪያዎቻችንን ነጥቀህ አባረርከን›› እያለ በውስጠ ወይራ ቀልድ እየወቀሰኝ እንሳሳቅ ነበር፡፡ የቅየሳ መሣሪያዎቻቸውም በወላይታ አውራጃ ለወረዳ ከተማዎች መንገዶች ቅየሳ እንዲሁም በአበላና በሌ ለሰፈሩት ጭሰኞች ለአንድ ሰው አምስት ሄክታር (250 በ200 ሜትር) መሬት እየሸነሸኑ ለመስጠት አገልግለውናል፡፡ በተጨማሪም የሲዳሞ ጠቅላይ ግዛት ምክትል አስተዳዳሪ በነበርኩበት ጊዜ ከዲላ እስከ ሞያሌ : ባለው ኢንተርናሽናል መንገድ ላይ ላሉ ከተሞች ቶፖግራፊ  ካርታ ለማዘጋጀት ለቅየሳ ሥራ ተጠቅመንባቸዋል፡፡ የውኃ ልማት መሥሪያ ቤት በባለሙያዎች ብቻ ሳይሆን በቅየሳ መሣሪዎችም ርዳታ ስላበረከተልን ከፍ ያለ ምስጋና ይገባዋል፡፡

▼ሕይወቴ ፤ ደጃዝማች ወልደሰማዕት ገብረወልድ ፣ 262-3

Via Ethiopian History and Tourism/የኢትዮጵያ ታሪክና ቱሪዝም
@ethiopianarchitectureandurbanism



tgoop.com/ethiopianarchitectureandurbanism/15095
Create:
Last Update:

የወላይታ ሶዶ ከተማ የቶፖግራፊ ካርታ ዝግጅት

የወላይታ አውራጃ ካርታ እንዲነሣ እና የሰባቱ ወረዳዎች ይዞታ በካርታው ላይ እንዲሰፍር ካደረግሁ በኋላ፣ ለሶዶ ከተማ ዘመናዊ ማስተር ኘላን ወደ ማዘጋጀት ዕቅዴ ገባሁ፡፡ ለሶዶ ከተማ ዘመናዊ ማስተር ፕላን እንዲዘጋጅ ማድረግ የከተማዋ ዕድገት በዕቅድ እንዲመራ ያግዛል፡፡ ለዚህ ሥራ ደግሞ አስቀድሞ የቶፖግራፊ ካርታ መዘጋጀት አለበት፡፡ የቶፖግራፊ ካርታውን ለማዘጋጀት ሰርቬየሮች ከአገር ግዛት ሚኒስቴር የማዘጋጃ ቤቶች ክፍል እንዲሰጡኝ ብጠይቅ ግን ፈቃደኛ ሳይሆኑ ቀሩ፡፡ለአስተዳደሩም ሆነ ለሕዝቡ አመች እንዲሆን አውራጃውን በአዲስ መልክ ለማዋቀር ከአገር ግዛት ሚኒስቴር ፈቃደኝነት ሳጣ፣ ቀደም ብሎ የአውራጃውን ካርታ በማንሳት ወደ ተባበሩኝ መሥሪያ ቤቶችና ድርጅቶች ፊቴን አዞርኩኝና እንዳለፈው ጊዜ ሁሉ የሥራ ሰዓት ሳይጠብቁና ቅዳሜ፣ እሁድ፣ የበዓል ቀን ሳይሉ፣ ለሶዶ ከተማ ማስተር አጠናቀቁልን፡፡ ባለሙያዎቹ የሕዝብና ቤት ቆጠራውን ስለአካሄዱልን እንዲሁም ፕላን ሥራ አስፈላጊ የሆነውን የቶፖግራፊ ካርታ ሥራ በአጭር ጊዜ ውስጥ ሌሎች ብዙ የልማት ሥራዎችን በዕቅድ ለማከናወን የሚያስፈልገውንና ለልማት ሥራ መሠረት የሆነውን የአውራጃውንም ሆነ የሶዶ ከተማን ካርታ ስላነሱልንና ለወላይታ አውራጃ ልማት ከፍ ያለ አስተዋፅኦ ስላደረጉ ባለውለታዎች ናቸው፡፡ በጊዜው ምስጋና ያቀረብኩላቸው ቢሆንም እዚህ ላይ ስማቸው ሲጠራ እንዲኖር ደግሜ አመሰግናቸዋለሁ፡፡ ሥራውን አጠናቀው ሲያስረክቡንም አብረው የመሐንዲስ የሥራ መሣሪያዎችን ጭምር ለግሰውናል፡፡

#የመሐንዲስ የሥራ መሣሪያዎቹን ልገሳ ያደረጉልን፣ የውኃ ልማት መሥሪያ ቤት ሄጄ የካርታ ሥራ ባለሙያዎቹን ርዳታ በጠየኩበት ወቅት ከዕቃ ግምጃ ቤታቸው የመግባት እድል አጋጥሞኝ ነበር፡፡ መሥሪያ ቤቱ በርዳታ ያገኛቸው ብዙ የቅየሳ መሣሪያዎች(ቴዎዶላይቶች፣ ጃሎዎች፣ ስታድያዎችና ባለመቶ ሃምሳና ሰላሳ ሜትር፣ አደጋ የሚችሉ እና ለገጠር ሥራ አገልግሎት የተሠሩ ጥቅል ሜትሮች) የዕቃ ግምጃ ቤቱን ያጨናነቁት መሆኑንም አይቼ ነበር፡፡ ስለዚህ የውሀ ልማት ባለሙያዎች ወደ አውራጃው ይዘዋቸው የሄዱትን የቅየሳ መሣሪዎች እዛው ለአውራጃው ግዛት ለልማት ሥራ አገልግሎት እንዲውሉ፣ ያንበሳ ልመና ጋማ ይዞ እንደሚባለው ሆኜ ሥራው ሲያልቅ መሣሪያዎቹን ሁሉ ትተውልን እንዲሄዱ አድርጌያለሁ፡፡

#የባለሙያዎቹ ኃላፊ የነበረው ስሙን የዘነጋሁት መሐንዲስ እስከቅርብ ጊዜ ድረስ ባየኝ ቁጥር «ባገለገልን ፈንታ መሣሪያዎቻችንን ነጥቀህ አባረርከን›› እያለ በውስጠ ወይራ ቀልድ እየወቀሰኝ እንሳሳቅ ነበር፡፡ የቅየሳ መሣሪያዎቻቸውም በወላይታ አውራጃ ለወረዳ ከተማዎች መንገዶች ቅየሳ እንዲሁም በአበላና በሌ ለሰፈሩት ጭሰኞች ለአንድ ሰው አምስት ሄክታር (250 በ200 ሜትር) መሬት እየሸነሸኑ ለመስጠት አገልግለውናል፡፡ በተጨማሪም የሲዳሞ ጠቅላይ ግዛት ምክትል አስተዳዳሪ በነበርኩበት ጊዜ ከዲላ እስከ ሞያሌ : ባለው ኢንተርናሽናል መንገድ ላይ ላሉ ከተሞች ቶፖግራፊ  ካርታ ለማዘጋጀት ለቅየሳ ሥራ ተጠቅመንባቸዋል፡፡ የውኃ ልማት መሥሪያ ቤት በባለሙያዎች ብቻ ሳይሆን በቅየሳ መሣሪዎችም ርዳታ ስላበረከተልን ከፍ ያለ ምስጋና ይገባዋል፡፡

▼ሕይወቴ ፤ ደጃዝማች ወልደሰማዕት ገብረወልድ ፣ 262-3

Via Ethiopian History and Tourism/የኢትዮጵያ ታሪክና ቱሪዝም
@ethiopianarchitectureandurbanism

BY Ethiopian Architecture Construction and Urbanism


Share with your friend now:
tgoop.com/ethiopianarchitectureandurbanism/15095

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

Hui said the time period and nature of some offences “overlapped” and thus their prison terms could be served concurrently. The judge ordered Ng to be jailed for a total of six years and six months. Among the requests, the Brazilian electoral Court wanted to know if they could obtain data on the origins of malicious content posted on the platform. According to the TSE, this would enable the authorities to track false content and identify the user responsible for publishing it in the first place. With the “Bear Market Screaming Therapy Group,” we’ve now transcended language. Just at this time, Bitcoin and the broader crypto market have dropped to new 2022 lows. The Bitcoin price has tanked 10 percent dropping to $20,000. On the other hand, the altcoin space is witnessing even more brutal correction. Bitcoin has dropped nearly 60 percent year-to-date and more than 70 percent since its all-time high in November 2021. As the broader market downturn continues, yelling online has become the crypto trader’s latest coping mechanism after the rise of Goblintown Ethereum NFTs at the end of May and beginning of June, where holders made incoherent groaning sounds and role-played as urine-loving goblin creatures in late-night Twitter Spaces.
from us


Telegram Ethiopian Architecture Construction and Urbanism
FROM American