Telegram Web
#ኢዜማ ወጣቶች መምሪያ የሚዘጋጀው #የኔ_ፖለቲካ መርኃግብር በዛሬው ዕለት በኢዜማ ዋና ጽ/ቤት ተካሔደ።

በውይይቱ ዓለም አቀፍ እና ሀገራዊ ሁኔታን መሠረት በማድረግ የኢትዮጵያ የባሕር በር ፍላጎት ላይ ያሉ እድሎች እና ተግዳሮቶች በዘርፉ ምሁር የሺጥላ ወንድሜነህ (ዶ/ር) የመነሻ ሐሣብ አቅራቢነት እና በተወያዮች ተጨማሪ ሐሣብ እና ጥያቄዎች ሠፊ ውይይት ተደርጓል።

ሙሉ ውይይቱን በፓርቲው የዩቲዩብ ገጽ (https://bit.ly/Ezema_YT) በቅርቡ ይፋ የምናደርግ ይሆናል።

ሌሎች የኢዜማ የማኅበራዊ ትስስር ገፆችንም ይወዳጁ።

👉 ፌስቡክ: https://bit.ly/Ezema_FB

👉 ትዊተር (X): https://bit.ly/3XgzDbH

👉 ቲክቶክ: https://bit.ly/EzemaT_T

👉 ቴሌግራም: https://bit.ly/Ezema_TG

👉 ዋትስአፕ: https://whatsapp.com/channel/0029Vb4gZHl9sBI4OBw49p2z
ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ 1446ኛው የኢድ አል-ፈጥር በዓል አደረሳችሁ!

#ኢዜማ
#ኢትዮጵያ
ከኢትዮጵያ ዜጎች ለማኀበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) የተሰጠ መግለጫ

የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ)
መጋቢት 22/2017 ዓ.ም
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ
ከኢትዮጵያ ዜጎች ለማኀበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) የተሰጠ መግለጫ
መጋቢት 19/2017 ዓ.ም ከምሽቱ አምስት ሰዓት አካባቢ በዛይሴ ወዘቃ፣ ፃናኦ ቀበሌ በግለሰብ ቤት ላይ በተፈፀመ የቤት ማቃጠል ጥቃት ቤት ንብረት መውደሙ እና የሁለት ህፃናት ህይወት ማለፉን ለማወቅ ችለናል፡፡
በዚህ አሰቃቂ ሕገወጥ ድርጊት ድርጅታችን ኢዜማ የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን እየገለጸ የክልሉ መንግስት ድርጊቱን የፈፀሙትን አካላት ሕጋዊውን መንገድ ተከትሎ እንዲያጣራ እና በድርጊቱ የተሳተፉ አካላትን ለፍርድ እንዲያቀርብ እንጠይቃለን፡፡ከዚህ አሳፋሪ እና አስነዋሪ ተግባር ጀርባ ያለ የትኛውም አካል ቢሆን በጋራ ሊወገዝ የሚገባው መሆኑንም ኢዜማ በፅኑ ያምናል።
ይህን በጭካኔ የተሞላ አስነዋሪ ድርጊት ተከትሎ በአካባቢው የሚንቀሳቀሱ አንዳንድ የማህበራዊ ሚዲያዎች እና የመንግስት አካላት የድርጅታችንን ስም አላግባብ እያነሱ መሆኑን ለመረዳት ችለናል፡፡ ይህን መሰል ስም ማጥፋት በቸልታ የማናየው መሆኑ እንዳለ ሆኖ ኢዜማ በእንደዚህ አይነት ሕገወጥ ተግባር ውስጥ የማይገኝ ብሎም ከቆመለት የሰላማዊ ትግል መርሆ ውጪ መሆኑን ለማሳወቅ እንወዳለን፡፡
ሳናነሳ የማናልፈው ጉዳይ ቢኖር ወንጀል የፈፀሙ አካላትን ለፍርድ በማቅረብ ሂደት ውስጥ ከዚህ በፊት የተስተዋሉ አይነት የፖለቲካ ልዩነትን መሰረት ያደረጉ ንፁሐንን ከአጥፊዎች ያለየ የጅምላ እስርና ህገወጥ አፈና እንዳይኖር የህግ አስከባሪ አካላትም ሕግና ሕግን ብቻ መሰረት አድርገው እንዲሰሩ በአፅንኦት ለማሳሰብ እንወዳለን ፡፡
ስለሆነም ይህን አሰቃቂ ወንጀል የፈፀሙ አካላት በአስቸኳይ ሕግ ፊት እንዲቀርቡ የፀጥታ አካላትም የደረሱበትን ግኝት ደረጃ በደረጃ ለሕብረተሰቡ እንዲያሳውቁ እየጠየቅን ኢዜማም ጉዳዩን በልዩ ሁኔታ እንደሚከታተል ለማሳወቅ እንወዳለን።
በተፈፀመው ሕገወጥ እና በጭካኔ ለተሞላ አስነዋሪ ተግባር ቤት ንብረታቸውን እና ህፃናት ልጆቻቸውን ላጡ ቤተሰብ፣ ወዳጅ እና ዘመድ መፅናናትን እንመኛለን፡፡

የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ)
መጋቢት 22/2017 ዓ.ም
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
የፌደራል መንግሥት በክልል ጣልቃ የሚገባበትን ሥርዓት ለመደንገግ የወጣውን አዋጅ ቁ: 359/1995 ለማሻሻል በቀረበው ረቂቅ አዋጅ ላይ የኢፌዴሪ ሕዝብ ተወካዮችች ም/ቤት አባል (የ #ኢዜማ ተመራጭ) የሆኑት አወቀ አምዛዬ (ዶ/ር) ያቀረቡት ሐሣብ

#ኢዜማ
#ኢትዮጵያ
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
የፌደራል መንግሥት በክልል ጣልቃ የሚገባበትን ሥርዓት ለመደንገግ የወጣውን አዋጅ ቁ: 359/1995 ለማሻሻል በቀረበው ረቂቅ አዋጅ ላይ የኢፌዴሪ ሕዝብ ተወካዮችች ም/ቤት አባል (የኢዜማ ተመራጭ) የሆኑት አብርሃም በርታ (ዶ/ር) ያቀረቡት ሐሣብ

#ኢዜማ
#ኢትዮጵያ
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
ኢትዮጵያ ውስጥ የማንነት ፖለቲካ ያመጣብንን ችግር ከሌላ ቦታ አጣቅሰን የምንረዳው ሣይሆን፤ በራሣችን ያየነው ነው!

#ኢዜማ
#ኢትዮጵያ
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
እንዴት አድርገን በጋራ ለልጆቻችን እንሰራለን ብለን የምናስብበት ጊዜ ነው!

#ኢዜማ
#ኢትዮጵያ
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
ፖለቲካ ማለት ማኅበረሠብን ወደተሻለ ቦታ ለመውሰድ የሚደረግ ሙከራ እንጂ ማኅበረሠብን ሊያጠፋ የሚችል ነገር ዕያየን አብሮ ሲጠፋ ማየት አይደለም!

#ኢዜማ
#ኢትዮጵያ
በኢዜማ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ የምትዘጋጀው የዜጎች ልሳን መጽሔት ቅጽ 02_ቁ: 12 ባለፉት ሁለት ዓመታት በመጽሔቷ የተዳሰሱ ጉዳዮችን ታወሳናለች፤ ማስፈንጠሪያውን በመጫን ሙሉውን ይዘት ያንብቡ።

https://drive.google.com/file/d/1MC-aVkGR2D2T614KNLS8OUQ7IX7k5gkn/view?usp=drivesdk


#ኢዜማ
#የዜጎች_ልሳን
የቀድሞ ፖለቲካ አሁን ባለው ላይ ያሣረፈው አዎንታዊ እና አሉታዊ ተጽዕኖ ምንድነው በሚል ርዕስ በሴቶች መምሪያ የተዘጋጀው የውይይት መርኃግብር ተካሔደ።

የውይይቱን መነሻ ሐሣብ የፓርቲው ም/ሊ ማዕረጉ ግርማ ያቀረቡ ሲሆን ተወያዮች ሐሣቦችን በማከል እና ጥያቄዎችን በማንሣት ሰፊ ውይይት እንዲካሔድ አስችለዋል።

#ኢዜማ
#ኢትዮጵያ
2025/04/16 13:20:54
Back to Top
HTML Embed Code: