የ #ኢዜማ ም/መሪ ዮሐንስ መኮንን ከኮምፓስ ሚዲያ ጋር በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳይ ላይ ያደረጉትን ቆይታ ይመልከቱ
https://www.youtube.com/live/6fMxt6PYM8w?si=TNdfZPxAzNxTGcfG
https://www.youtube.com/live/6fMxt6PYM8w?si=TNdfZPxAzNxTGcfG
YouTube
ኢትዮጵያ ከየት ወዴት?፣ የአዲስ አበባ ጉዳይ፣ ቆይታ ከአርክቴክት ዮሐንስ መኮንን ጋር!
ኢትዮጵያ ከየት ወዴት?፣
የአዲስ አበባ ጉዳይ፣
ቆይታ ከአርክቴክት ዮሐንስ መኮንን ጋር!
የአዲስ አበባ ጉዳይ፣
ቆይታ ከአርክቴክት ዮሐንስ መኮንን ጋር!
የኢዜማ ብሔራዊ ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ (ብሥአኮ) ከየካቲት 22-24/ 2017 ዓ.ም. ባደረገው ስብሰባ የፓርቲው መሪ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ የፖለቲካ ትንታኔ በምን ላይ መመሥረት እንዳለበት ያቀረቡትን ሐሳብ ይመልከቱ
https://youtu.be/dc1prc6kAxs?si=XLzxatW3_JAWxYhL
https://youtu.be/dc1prc6kAxs?si=XLzxatW3_JAWxYhL
YouTube
Lualawi ሉዓላዊ- "አሁን የሥዕሉ ሰሌዳ ባዶ ነው፣ ምን እንጻፍበት?"ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ - (በፓርቲያቸው ኢዜማ ሥራ አስፈጻሚ ስብሰባ ላይ ከተናገሩት )
ሊንኮች
Telegram
https://www.tgoop.com/+tfZYjOsLvR00YzRh
TikTok
https://www.tiktok.com/@lualawi2016
YouTube
www.youtube.com/@Lualawi-2016
Instagram
https://www.instagram.com/lualawi2016/
Telegram/Whatsapp/viber
571-531-5892
…
Telegram
https://www.tgoop.com/+tfZYjOsLvR00YzRh
TikTok
https://www.tiktok.com/@lualawi2016
YouTube
www.youtube.com/@Lualawi-2016
https://www.instagram.com/lualawi2016/
Telegram/Whatsapp/viber
571-531-5892
…
ለፖለቲካ ፍጆታ በሚል የሚደረጉ የሴቶች ተሳትፎን ኢዜማ እንደማይቀበል ያሣውቃል!!
የሰው ልጆች ሰው በመሆናቸው ብቻ ከሚጎናጸፉት ሰብዓዊ መብት ባሻገር የአንድ ሀገር ዜጋ ከመሆን የሚመነጩ ዴሞክራሲያዊ መብቶችም አሉ።
እንደ አጠቃላይ የሰው ልጆች እንደ ሁኔታው በተለያዩ ጊዜያት እነዚህን መብቶች በቅጡ ባለመከበራቸው እነዚህን መብቶች ለማስከበር ከፍተኛ ትግል እና መስዋዕትነት ተከፍሏል።
እነኚህ ከፍተኛ ትግሎች ቢደረጉም የሴቶች መብት መከበር ከተወሰኑ መሻሻሎች ባሻገር አሁንም ገና ብዙ የሚቀረው ሆኖ እናገኘዋለን።
ሴቶች የዓለምን ግማሽ በመቶ የሚሆን ቁጥር ቢይዙም ይህንን የሚመጥን በቂ እና ውጤት የሚያመጣ ውክልና ግን ኖሯቸው አያውቅም፤ ይልቁንም በዓለም ላይ ባሉ ሰው ሰራሽም ሆነ ተፈጥሯዊ አደጋ ከፍ ያለውን ዋጋ ከሕፃናት ጋር ሲወስዱ እንመለከታለን። ከዚህ በተጨማሪም እንደ መደፈር፣ ጠለፋ እና የመሣሠሉ የተለያዩ አይነት ጥቃት ሰለባዎችም ናቸው።
ለዚህ በዋነኛነት የማኅበረሰብ አረዳድ እና የመንግሥት አስፈላጊው የሕግ ሽፋን አለመሥጠት በመሠረታዊነት የሚነሱ ሲሆኑ ከእነዚህ ሁለቱ የመነጩ ታሪካዊ ኢፍትሐዊነቶች ሴቶች መብቶቻቸውን በተሟላ ሁኔታ ለመጠየቅ የሚያስችላቸው አቅምን እንዳያጎለብቱ ከፍ ሲል ለእነርሱም ምቹ የሆነ ሥርዓት መገንባት አለመቻል ምክንያት ሆኗል።
የዘንድሮ ዓለምአቀፍ የሴቶች ቀን ጭብጥ (Theme) "ሁሉም መብቶች፤ ለሁሉም ሴቶች" በሚል ይከበራል።
ይህም ጭብጡ ካለፉት ጊዜያት ውስን ጉዳይ ላይ ካተኮረ ጭብጥነት ይልቅ ሰፋ ያሉ ጉዳዮችን የሚመለከት ሆኖ ተቀርጿል።
ይህ መሠረታዊ የሆኑ የመብት እና እኩልነት ጥያቄዎችን አንግቦ የተነሣው ጭብጥ በይደር የሚቆይ ሳይሆን ባለው አቅም ሁሉ ዛሬ ላይ እየተተገበረ መሔድ ያለበት ሆኖ እናገኘዋለን።
ይህንን ተግባር በእውነት ተፈፃሚ ለማድረግ ግን በመጀመርያ ስለችግሩ አንገብጋቢነት ጆሮ ሰጥቶ ከመስማት አንስቶ እስከ በበቂ ሁኔታ ችግሩን ለማስወገድ ፍላጎት ማሣደር እና አቅምን መገንባት ይሻል፤ ለዚህም በዚህ ውስጥ የሚመለከታቸው የሲቪክ ማኅበራት እንደ አጠቃላይ በሴቶች መብት ላይ በቂ ግንዛቤ መፍጠር፣ አስፈላጊ የሕግ ማዕቀፎችን በማነሳሳት እንዲወጡ ግፊት ማድረግ እና የመሣሠሉት ይጠበቃል፤ መንግሥት ችግሩን የሚመጥን የፖሊሲ እና ሕግ ማዕቀፍ አበጅቶ ሴቶች ለሀገራቸው እንደማንኛውም ዜጋ ሊያበረክቱ የሚገባቸው ላይ እንዲያተኩሩ ማድረግ እና ማኅበረሰቡ ሴቶች በዕለት ተዕለት ሕይወት ውስጥ የሚገጥሟቸውን ፈተናዎች አብሮ በመቆም ፍትሐዊ እና የተረጋጋ ማኅበረሰብ መፍጠር ላይ ሁሉም የድርሻቸውን እንዲወጡ ይጠበቃል።
ኢዜማ በማኅበራዊ ፕሮግራሙ በግልጽ እንዳስቀመጠው ሴቶችን ያገለለ ማንኛውም ዓይነት ፖሊሲ ውጤታማ እንደማይሆን ይገነዘባል፡፡ በተለይ የሴቶች በፖለቲካው መስክ መሳተፍ የራሳቸውን ጉዳይ በጥልቅ ያገናዘበ ፖሊሲ ለመቅረፅ ፋይዳው የጎላ እንደሚሆን ያምናል፡፡ ትምህርት ለእኩል ተሣትፎ ወሣኝ መሣሪያ በመሆኑ ሴት ልጆች ከትምህርት ገበታ የሚያስቀሩ ማነቆዎችን በማስወገድ ዘላቂ የሆነ የሴቶች ተሳትፎን ለማረጋገጥ ይሠራል፡፡ ሴቶች አሁን ያለው የፖለቲካ ምህዳር የፈጠረው አፈና ሲነሣ ሙሉ ኃይላቸውን ሊጠቀሙ የሚችሉበት እድል እንደሚፈጠር ኢዜማ ያምናል፡፡ ለይስሙላ ለፖለቲካ ፍጆታ በሚል የሚደረጉ የሴቶች ተሳትፎን #ኢዜማ እንደማይቀበልም ያሣውቃል።
እንኳን ለዓለም አቀፉ የሴቶች ቀን አደረሣችሁ!!
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
የ #ኢዜማ ሴቶች መምሪያ ኃላፊ ሠናይት ዘውዴ የእንኳን አደረሣችሁ መልዕክት
“የተቋማት ግንባታው ይበልጥ ወደፊት መራመድ ሲገባው ወደ ኋላ የተመለሰበትን አግባብ እያስተዋልን ነው”
ቃልኪዳን ከበደ የኢዜማ በጀትና ፋይናንስ/ትሬዥረር መመሪያ ኃላፊ
በኢዜማ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ የምትዘጋጀው የዜጎች ልሳን መጽሔት ቅጽ 02_ቁ: 11 ትኩረቷን በተቋማት ግንባታ ላይ አድርጋ የተሠናዳች ሲሆን የወሩን እንግዳ ጨምሮ የተለያዩ ወቅታዊ ጉዳዮችን ታሥነብበናለች፤ ማስፈንጠሪያውን በመጫን ሙሉውን ይዘት ያንብቡ።
https://drive.google.com/file/d/1mo5NeeWewZ79jZc_twPEX0OuajVGqTVq/view?usp=drivesdk
#ኢዜማ
#የዜጎች_ልሳን