tgoop.com/eyorkis/1265
Last Update:
ፍቅረኛ ለመያዝ ቀና ልብ ይፈልጋል። ከዛ ደግሞ አስተዋይ መሆን አለብን። ምክንያቱም ዘው ብለን የምንገባው የሰው ህይወት ውስጥ ነው።
ስንወጣ ደግሞ የሰውን ልብ እና ቅስሙን ሰባብረን... ህይወቱን አመሰቃቅለን ... ስሜቱን ጎድተን ተስፋ አስቆርጠን ነው የምንወጣው።
ይህን ሁሉ በደል ከማድረሳችን በፊት እስክንበስል ፍቅረኛ አንያዝ።
- ይኸውልሽ <አርግዣለሁ > ብለሽ ፍቅረኛሽን የመፈተን እድሜ ላይ ካለሽ ፍቅረኛ ይቅርብሽ።
ምን አድርጌ ላስደስተው ብሎ ከመጨነቅ ይልቅ ምን ብዬ ላስጨንቀው የምትይበት እድሜ ላይ ከሆንሽ ይቅርብሽ።
የእንትና ባል ለሷ እንዲ ያደርጋል አንተ ግን... ምናምን የሚል አስተሳሰብ ላይ ከሆንሽ ገና አልበሰልሽም።
ፍቅር ማለት ካፌ ለካፌ ሬስቶራንት ለሬስቶራንት መንከራተት መስሎ የሚሰማሽ ከሆነ በቃ ይቅርብሽ።
ፍቅሩን የገለፀልሽን ቴክስቶች ለሴት ጓደኞችሽ በማሳየት <እኔ እኮ እስከዚህም ነኝ .. > ብለሽ የማውራት ሞራል ላይ ከሆንሽ ይቅርብሽ።
- ይኸውልህ። ስለፍቅረኛህ ለጓደኞችህ መናገር የምታፍርበት ጊዜ ላይ ከሆንክ ተወው ፍቅረኛ አትያዝ።
<እኔ እኮ ለሷ እስከዚህም ነኝ ስለምታሳዝነኝ ነው ወይ ደግሞ እሷ ናት በደንብ የምታፈቅረኝ > ብለህ የምታወራበት እድሜ ላይ ካለህ አታፍቅር።
አውቀህ ስልክ አለማንሳት ... ሚስኮሎቿን ለጓደኞችህ ለማሳየት የምትጣጣር እድሜ ላይ ካለህ ይቅርብህ። ጊዜ ያለመስጠት ...
የማስቀናት... ሌላ ሴት የመደረብ ሞራል ላይ ከሆንክ ገና ስለሆንክ ፍቅረኛ አትያዝ።
ስንት ልቦች የተሰበሩት... ስንት ተስፋዎች የተቆረጡት ...ስንት ቤቶች የተዘጉት ... ስንት ህይወቶች የጠፉት በግዴለሽ ፍቅር ነው።
ፍቅርን ሁሉም ሰው ይፈልገዋል። የሰው ልጅ ሁሉ ይፈልገዋል። ግን በግዴለሽ አፍቃሪ ነን ባዮች አጥተውታል።
✨ሰው ሁን ከሰውም ሰው ሁን
ምንጭ ከሀሽማል ወመዘክር የtg Chanel
@eyorkis
BY ኢዮርቅስ
Share with your friend now:
tgoop.com/eyorkis/1265