tgoop.com/fnoteAemro/201
Last Update:
ሕይወት አዙሪት ናት
📖📖📖
ሕይወት አዙሪት ናት፡፡ ረጅም ርቀት የተጓዝክ ቢመስልህም የምትጨርሠው ከጀመርክበት ነው፡፡
፨ ራቁትክን ትወለዳለህ፤ እርቃንህን ወደመቃብር ትወርዳለህ ፡፡
፨ በጥርስ አልባው ድድህ እየጋጥክ ትጀምራለህ፤ ጥርሱን ባረገፈው ድድህ እያልጎጠጎጥክ ትጨርሳለህ ።
፨ የሕይወትን ትግል እየዳህ ትጀምራለህ፤ አጎንብሠህ ትጨርሳለህ፡፡
📜📜📜
ዘመንም ተምኔታዊ ነው፡፡
መስከረም ጥቅምት ብሎ ያስጀምርህና መስከረም ብሎ ይመጣብሃል፡፡ ሠኞ ማክሠኞ ብለህ ተጉዘህ፤ እንደገና ሠኞ ትላለህ ፡፡ ሕይወት አዙሪት ናት! መጀመሪያህ መጨረሻህ ነው፡፡ የጀመርክበትን አትርሳ፤ መጨረሻህ ነውና፡፡ የጀመርክበትን አትናቀው፤ ትጨርስበታለህና፡፡ ተራ ሠው ሆነህ ትጀምራለህ፤ ተምረህ ዕውቀት ብትጨምርም፤ ነግደህ ሃብት ብታገኝ፤ ተሹመህ በሕዝብ ላይ ብትሠለጥን፤ ክቡረ ክቡራን ሆነህ የወርቅ ካባ ብትለብስ፤ የምትጨርሠው እንደተራ ሠው አፈር ለብሠህ ነው፡፡
ልብ በል! ባለማወቅ ትጀምራለህ፤ በመዘንጋት ትጨርሳህ፡፡ ዕውቀት አላመጣህምና ዕውቀትም ይዘህ አትሄድም፡፡ በለቅሶ ትጀምራለህ፤ በጭንቅ ትጨርሳለህ፡፡ በሠው እቅፍ ትጀምራለህ፤ በሠው ሸክም ትጨርሳለህ፡፡
ልደትህ ከሞትህ በምን ይለያል? ሞትህስ ከልደትህ በምን ይከፋል? ሕይወት መጀመሪያዋና መጨረሻዋ አንድ ነው፡፡ በዚህ የተነሣ ጠቢቡ እንዳለው ሁሉም የከንቱ ከንቱ ነው፡፡ ከፀሐይ በታች አዲስ ነገር የለም፡፡ ልብ በል! የዓለም ከንቱነት ግን ውበትዋ ነው፡፡ ዓለም አዲስ ነገር ቢኖራት እኛን እንዴት በፀፀተን፤ ሞት የእውነት መጨረሻ ቢሆን እንዴት በቆጨን!!
‹‹ርቀህ የሄድክ ቢመስልህም፤ ትልቅ ክብ ሠርተህ ተመልሠህ እዚህ ትመጣለህ፡፡ ዋናውን ተግባርክን ግን እስካሁን አልጀመርከውም፡፡››
፧
ምንጭ ፦ ዶክተር ዓለማየሁ ዋሴ
(መርበብት - ከገጽ 314 - 315)
ያንብቡት ይወዱታል
፧
በተጨማሪም መነበብና መጋበዝ አለባቸው የምትሏቸውን ከመጽሐፍት ገጽ የተገኙ ፅሁፎች በዚህች አድራሻ አድርሱን
፧
ያነበቡትን ለወዳጅዎም ያካፍሉ(ይጋብዙ)
https://www.tgoop.com/joinchat-AAAAAETna_q_yoo2wsRYgg
BY ኰኲሐ ሃይማኖት
Share with your friend now:
tgoop.com/fnoteAemro/201