tgoop.com/hamreel/4239
Last Update:
#የትሩፋት_ሥራ_ጀምር
ጨክነህ ቆርጠህ የትሩፋትን ሥራ ጀምር፡፡ በትሩፋት አጠገብ እየተጠራጠርህ አትኑር፡፡ ክብር ይግባውና እግዚአብሔር ከማመን ተስፋ ወጥተህ በልብህ እንኳ አትጠራጠር፡፡ ትሩፋትህ ረብህ ጥቅም የሌለው እንዳይሆን የትሩፋት ሥራ ክቡድ አይምሰልህ፡፡ መሐሪ እግዚአብሔር ለለመኑት ሰዎች ጸጋውን ፈጽሞ እንዲሰጣቸው እመን እንጂ ስጦታው እንደየሥራችን አይደለም፡፡ በትጋታችን፣ በማመናችንና በመሻታችን መጠን ነው እንጂ እንደ ሃይማኖትህ ይደረግልህ ብሏልና፡፡
የትሩፋት ሥራም ይህች ናት፣ አንዱ መተምተሚያ አዘጋጅቶ መሐል ራሱን ይተመትመዋል፡፡ በየጊዜው በሚጸልየው ጸሎት እንዳያፍር ትቀርበኛለች ብሎ ያዝናል፡፡ አንዱ አብዝቶ ይሰግዳል፣ ልጸልይ ያለውን ይጸልያል፣ ስለ ጸሎቱ ፈንታ ብዙ ያለቅሳል፣ በልቅሶው ረብህ ጥቅም ያገኝበታል፡፡ አንዱ የልቡና ሥራ የምትሆን ትሩፋትን በመዘከር ይጋደላል፣ ወደ ተወሰነለት ጸጋ ይደርሳል፣ አንዱ ምግብ ነስቶ ሰውነቱን በረኃብ ያስጨንቃታል ጸሎቱን መፈጸም የማይቻለው እስኪሆን ድረስ፣ አንዱ ተናዶ እየመላለሰ ዳዊት ይጸልያል። በመድገም ዘወትር ጸሎትን ገንዘብ ያደርጋታል፣ አንዱ መጽሐፍ ለመመልከት፣ ለመድገም ጽሙድ ሆኖ ይኖራል፣ አንዱ ከአምላክ በተገኙ መጻሕፍት ያለውን ትርጓሜ ምሥጢር ያስበዋል፣ ያስተውለዋል፣ ይመረምረዋል። ወደ ሥራው ይሳባል፤ አንዱ የዐቢይ ምዕራፉን መለያ አይቶ ምሥጢሩን ያደንቃል፣ ዝምታ ይሰለጥንበታል፡፡ በልማድ መጽሐፍ ከመመልከት በልማድ ከመድገም ይከለከላል፡፡
አንዱ ደግሞ ሁሉንም አንድ አድርጎ ይሠራቸዋል፡፡ በዚህም ይሰለቻል፡፡ ዓለማዊ ሥራ ይሠራል፣ ለሐኬት ጽሙድ ሆኖ ይኖራል። አንዱ መጽሐፍ ከመመልከት ጥቂት ምሥጢር ያገኛል፡፡ በዚህም ትዕቢት ያድርበታል፡፡ በሰው መዘበት ያድርበታል፤ ይበድላል፡፡ አንዱ የልማድ ምክንያት ይሰለጥንበታል፣ አንዱም ይህን ሁሉ ድል ይነሣል፤ ከዚህ ሁሉ ይጠበቃል፡፡ ዕንቁ ክርስቶስን ገንዘብ እስኪያደርገው ወደኋላ አይመለስም፡፡ ደስ ብሎህ እግዚአብሔር ያዘዘውን የትሩፋት ሥራ ጀምር፡፡
BY የኖህ መርከብ ዘኦርቶዶክስ ተዋህዶ
Share with your friend now:
tgoop.com/hamreel/4239