tgoop.com/hamreel/4251
Last Update:
" የመንፈሳዊነት ግቡ፤ የአገልጋይነት ልኩ፤ የክርስትናችንም ጥጉ ወደ እግዚአብሔር መድረስ፣ እግዚአብሔርን ማግኘትና ከእግዚአብሔር ጋር መሆን ነው! "
.
“እናንተ በመጽሐፍት የዘለዓለም ሕይወት እንዳላችኹ ይመስላችኋልና፥ እነርሱን ትመረምራላችኹ፤ እነርሱም ስለ እኔ የሚመሰክሩ ናቸው፤ ነገር ግን፥ ሕይወት እንዲኾንላችኹ ወደ እኔ ልትመጡ አትወዱም።” ዮሐ 5፤39-40
.
የመንፈሳዊነት ግቡ፤ የአገልጋይነት ልኩ፤ የክርስትናችንም ጥጉ ወደ እግዚአብሔር መድረስ፣ እግዚአብሔርን ማግኘትና ከእግዚአብሔር ጋር መሆን ነው!!!
.
ክርስቲያኖች የሆንነው እግዚአብሔርን ለማግኘትና ከእግዚአብሔር ጋር ለመሆን ነው!
.
መጽሐፍ ቅዱስ የምናነበውና ቅዱሳት መጽሐፍትን የምንመረምረው እግዚአብሔርን ለማግኘትና ከእግዚአብሔር ጋር ለመሆን ነው!
.
ቤተ ክርስቲያን የምንሔደው፤ ቅዳሴ የምንቀድሰውና የምናስቀድሰው፣ ማኅሌት የምንቆመው፣ በሥርዐተ አምልኮው ውስጥ የምንሳተፈው . . . እግዚአብሔርን ለማግኘትና ከእግዚአብሔር ጋር ለመሆን ነው!
.
የምንማረውም ሆነ የምናስተምረው፤ ጉባዔ የምንዘረጋውና በጉባዔም የምንታደመው፤ የምንዘምረውና የምናገለግለው . . . ታቦት የኖረን፣ በታቦቱ መስዋዕት የምንሰዋው፣ ታቦት አክብረን በዓለ ንግሥ የምናነግሠው . . . እግዚአብሔርን ለማግኘትና ከእግዚአብሔር ጋር ለመሆን ነው!
.
መብዐ የምናገባው፣ ጳጳሳትና ከህናት ያስፈለጉን፣ ሕንፃ ቤተ ክርስቲያን የኖረን፣ ገዳማትን የመሠረትነው፣ ቤተ ክህነት የሚባል መዋቅር የፈጠርነው፣ ሰበካ ጉባኤ የሚባል ሥርዓት የዘረጋነው፣ ሰንበት ትምህርት ቤቶችን ያቋቋምነው፣ ማኅበረ ቅዱሳን የሚባል ማኅበር እንዲኖረን የተደረገው፣ ሌሎች ማኅበራትን የፈጠርነው . . . እግዚአብሔርን ለማግኘትና ከእግዚአብሔር ጋር ለመሆን ነው!
.
ባሉን ነገሮችና በምንሳተፍባቸው አገልግሎቶች ሁሉ እግዚአብሔርን ማግኘት ካልቻልንና ከእግዚአብሔር ጋር ካልሆንበት ጥቅሙ ምንድን ነው? በትምህርታችንም ሆነ በሥርዐተ አምልኳችን እግአብሔርን ካልሆነ በቀር ምን ልናተርፍበት እንችላለን?
.
የትምህርታችንም ሆነ የሥርዐተ አምልኳችን ማዕከሉ ወደ እግዚአብሔር መድረስ ነው! የክርስትናችን መሠረታዊ አላማና የአገልግሎታችን ዋነኛ ተልዕኮ እግዚአብሔርን ማግኘትና ከእግዚአብሔር ጋር መሆን ነው! . . . እግዚአብሔርን ካላገኘንበትና ወደ እግዚአብሔር ካልቀረብንበት፤ እግዚአብሔርንም ካላገኘንበት ክርስትናችን፣ አገልግሎታችን፣ የቤተ ክርስቲያን ልጅነታችን፣ ልዩ ልዩ ተሳትፏችን . . . ፋይዳው ምንድን ነው!
.
“እናንተ በመጽሐፍት የዘለዓለም ሕይወት እንዳላችኹ ይመስላችኋልና፥ እነርሱን ትመረምራላችኹ፤ እነርሱም ስለ እኔ የሚመሰክሩ ናቸው፤ ነገር ግን፥ ሕይወት እንዲኾንላችኹ ወደ እኔ ልትመጡ አትወዱም።” ዮሐ 5፤39-40 ተብሎ እንደተጻፈ ክርስትና ወደ እግዚአብሔር መምጣት፤ ወደ ክርስቶስም መድረስ ነው!!! ሕይወት እንዲሆንልን፤ እንዲበዛልንም ወደ እግዚአብሔር እንምጣ፤ ወደ ክርስቶስም እንድረስ፤ ከእግዚአብሔር ጋር እንሁን፤ እንደቃሉ እናድርግ፤ እንደተማርነው እንኑር፤ ከፈቃዱም ጋር ውለን እንደር!!!
BY የኖህ መርከብ ዘኦርቶዶክስ ተዋህዶ
Share with your friend now:
tgoop.com/hamreel/4251