MAHETEBEN123 Telegram 20329
"ጾምን የምንጾመው ዲያብሎስንና ግብረ ኃጢአትን ለማሸነፍ ነው::" ቅዱስነታቸው

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት የ2017 ዓ.ም የዐቢይ ጾምን አስመልክተው የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላለፉ !

የካቲት 15 ቀን 2017 ዓ.ም (ተ.ሚ.ማ /አዲስ አበባ)

ቅዱስነታቸው በመልእክታቸው መነሻ <<ጌታችን አምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በፈለገ ዮርዳኖስ ከተጠመቀ በኋላ ሳይውል ሳያድር ወዲያውኑ ወደ በረኻ በመሄድ አርባ ቀንና አርባ ሌሊት ጾመ፡፡>> በማለት የጌታችንና አምላካችን የመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የመጾሙን ጥንተ ነገር አውስተዋል።

ቅዱስነታቸው በአርባ ቀናት ውስጥ የጌታችንና አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን በዲያቢሎስ መፈተንና ድል መንሳትም አብራርተው ሲያወሱ <<በዚህ ጊዜ የጌታችን መልስ “ሰው ከእግዚአብሔር አፍ በሚወጣ ቃል ሁሉ እንጂ በእንጀራ ብቻ ኣይኖርም” የሚል ነበረ፤
ጌታችን በዚህ አባባሉ የዲያብሎስን ክፉ ሐሳብ የሚንድ እንጂ የእሱ ታዛዥ አለመሆኑን ኣሳየ፤ ዲያብሎስ በዚህ ሳያበቃ በትዕቢት በፍቅረ ንዋይና በባዕድ አምልኮ ሊጥለው ደጋግሞ ሙከራ አደረገ፤ ግን አልተሳካለትም፤>> ብለዋል።

ቅዱስነታቸው የመጾማችንን ምክንያት ሲያጠይቁ <<...የዲያብሎስን ፈተናዎች እንዴት በድል ማለፍ እንደምንችል ጌታችን በተግባር ኣሳይቶናል፤ ጌታችን ዲያብሎስን ያሸነበፈበት ስልት በመንፈስ ልዕልና እንጂ በዱላም፣ በካባድ መሳሪያም ኣይደለም፤ አለመሆኑንም የድርጊቱ ሂደት በግልጽ ያመለክታል፤ እንግዲያውስ እኛም ዲያብሎስን የምናሸንፈው በዚህ የመንፈስ ልዕልና ነው ማለት ነው::... ስለሆነም ጾምን የምንጾመው በዚህ ስልት ዲያብሎስንና ግብረ ኃጢአትን ለማሸነፍ ነው::
ከዚህ አኳያ ዲያብሎስን ለማሸነፍ መጾም ግድ ስለሆነ ጌታችን በከፈተልንና ባሳየን መንገድ እንጾማለን>> ብለዋል።

ስንጾምም <<የምንጾመው መልካም ኅሊና ኖሮን ለእግዚአብሔር ለመታዘዝና ለመገዛት፣ ከዚያም ከቃሉ በተነገረን መሠረት የተራቡትን ልንመግብ፣ የተራቈቱትን ልናለብስ፣ የተጣሉትን ልናስታርቅ፣ ፍትሕ ያጡትን ፍትሕ እንዲያገኙ ልናደርግ፣ ለንኡሳን የሕብረተ ሰብ ክፍሎች የተለየ ትኵረት ልንሰጥ፤ እኩልና ፍትሓዊ የሀብት ክፍፍል በሰው ልጆች መካከል ልናረጋግጥ፣ ሰብኣዊ ክብር እንዳይነካ ጦርነት፣ ጥላቻ፣ አደገኛ የቃላት ውርወራና መነቃቀፍ እንዲቀር ልናደርግ ነው፤>> በማለት አጽንዖት ሰጥተው አባታዊ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።



tgoop.com/maheteben123/20329
Create:
Last Update:

"ጾምን የምንጾመው ዲያብሎስንና ግብረ ኃጢአትን ለማሸነፍ ነው::" ቅዱስነታቸው

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት የ2017 ዓ.ም የዐቢይ ጾምን አስመልክተው የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላለፉ !

የካቲት 15 ቀን 2017 ዓ.ም (ተ.ሚ.ማ /አዲስ አበባ)

ቅዱስነታቸው በመልእክታቸው መነሻ <<ጌታችን አምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በፈለገ ዮርዳኖስ ከተጠመቀ በኋላ ሳይውል ሳያድር ወዲያውኑ ወደ በረኻ በመሄድ አርባ ቀንና አርባ ሌሊት ጾመ፡፡>> በማለት የጌታችንና አምላካችን የመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የመጾሙን ጥንተ ነገር አውስተዋል።

ቅዱስነታቸው በአርባ ቀናት ውስጥ የጌታችንና አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን በዲያቢሎስ መፈተንና ድል መንሳትም አብራርተው ሲያወሱ <<በዚህ ጊዜ የጌታችን መልስ “ሰው ከእግዚአብሔር አፍ በሚወጣ ቃል ሁሉ እንጂ በእንጀራ ብቻ ኣይኖርም” የሚል ነበረ፤
ጌታችን በዚህ አባባሉ የዲያብሎስን ክፉ ሐሳብ የሚንድ እንጂ የእሱ ታዛዥ አለመሆኑን ኣሳየ፤ ዲያብሎስ በዚህ ሳያበቃ በትዕቢት በፍቅረ ንዋይና በባዕድ አምልኮ ሊጥለው ደጋግሞ ሙከራ አደረገ፤ ግን አልተሳካለትም፤>> ብለዋል።

ቅዱስነታቸው የመጾማችንን ምክንያት ሲያጠይቁ <<...የዲያብሎስን ፈተናዎች እንዴት በድል ማለፍ እንደምንችል ጌታችን በተግባር ኣሳይቶናል፤ ጌታችን ዲያብሎስን ያሸነበፈበት ስልት በመንፈስ ልዕልና እንጂ በዱላም፣ በካባድ መሳሪያም ኣይደለም፤ አለመሆኑንም የድርጊቱ ሂደት በግልጽ ያመለክታል፤ እንግዲያውስ እኛም ዲያብሎስን የምናሸንፈው በዚህ የመንፈስ ልዕልና ነው ማለት ነው::... ስለሆነም ጾምን የምንጾመው በዚህ ስልት ዲያብሎስንና ግብረ ኃጢአትን ለማሸነፍ ነው::
ከዚህ አኳያ ዲያብሎስን ለማሸነፍ መጾም ግድ ስለሆነ ጌታችን በከፈተልንና ባሳየን መንገድ እንጾማለን>> ብለዋል።

ስንጾምም <<የምንጾመው መልካም ኅሊና ኖሮን ለእግዚአብሔር ለመታዘዝና ለመገዛት፣ ከዚያም ከቃሉ በተነገረን መሠረት የተራቡትን ልንመግብ፣ የተራቈቱትን ልናለብስ፣ የተጣሉትን ልናስታርቅ፣ ፍትሕ ያጡትን ፍትሕ እንዲያገኙ ልናደርግ፣ ለንኡሳን የሕብረተ ሰብ ክፍሎች የተለየ ትኵረት ልንሰጥ፤ እኩልና ፍትሓዊ የሀብት ክፍፍል በሰው ልጆች መካከል ልናረጋግጥ፣ ሰብኣዊ ክብር እንዳይነካ ጦርነት፣ ጥላቻ፣ አደገኛ የቃላት ውርወራና መነቃቀፍ እንዲቀር ልናደርግ ነው፤>> በማለት አጽንዖት ሰጥተው አባታዊ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

BY ማህተቤን አልበጥስም የተዋህዶ ድምፅ ✝💒


Share with your friend now:
tgoop.com/maheteben123/20329

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

How to Create a Private or Public Channel on Telegram? Users are more open to new information on workdays rather than weekends. To edit your name or bio, click the Menu icon and select “Manage Channel.” 2How to set up a Telegram channel? (A step-by-step tutorial) Add the logo from your device. Adjust the visible area of your image. Congratulations! Now your Telegram channel has a face Click “Save”.!
from us


Telegram ማህተቤን አልበጥስም የተዋህዶ ድምፅ ✝💒
FROM American