በአውሮፓ ማእከል የሥራ አስፈጻሚ ጉባኤ አባላት የገጽ ለገጽ ስብስባ ማካሄዱ ተገለጸ።
የካቲት ፬/፳፻፲፯ ዓ.ም
ማኅበረ ቅዱሳን በአውሮፓ ማእከል የሥራ አስፈጻሚ ጉባኤ አባላት የዘንድሮውን ዓመት የገጽ ለገጽ ስብሰባ በዴንማርክ ኮፐንሀገን ከተማ ደብረ ምሕረት ቅዱስ አማኑኤል ቤተ ክርስቲያን ከጥር 30 እስከ የካቲት 2 ቀን 2017 ዓ.ም አካሂደዋል።
በስብሰባው የደብሩ አስተዳዳሪ መልአከ ምሕረት ቆሞስ አባ ዘሚካኤል ዴሬሳ፣ አገልጋይ ካህን ቀሲስ ኃይለ ጊዮርጊስና የዴንማርክ ግንኙነት ጣቢያ አባላት ተገኝተዋል።
በዚህም የማእከሉ የ6 ወራት የአገልግሎት አፈጻጸም፣ የንዑሳን ማእከላትና የግንኙነት ጣቢያዎች አሁናዊ ሁኔታ ምን እንደሚመስል በመምከር ለቀጣይ የማእከሉ የአገልግሎት አቅጣጫዎች ዙሪያ ሰፊ ውይይት ተደርጓል።
"መልካም ሥራን ለመሥራት አንታክት" በሚል ርእስም በአባ ዘሚካኤል በማኀበራዊ ሕይወት ዙሪያ ትምህርት የተሰጠ ሲሆን ከመደበኛ የአገልግሎት ክንውን በተጨማሪም መንፈሳዊ ሕይወትን በሚመለከት የምክክር መርሐ ግብር ተከናውኗል፡፡
የገጽ ለገጽ ስብሰባ፥ የማእከሉ የሥራ አስፈጻሚ ጉባኤ አባላት በአካል በመገናኘት ይበልጥ የሚተዋወቁበትና የሚወያዩት በዓመት አንድ ጊዜ የሚካሄድ ልዩ መርሐግብር ነው፡፡
የካቲት ፬/፳፻፲፯ ዓ.ም
ማኅበረ ቅዱሳን በአውሮፓ ማእከል የሥራ አስፈጻሚ ጉባኤ አባላት የዘንድሮውን ዓመት የገጽ ለገጽ ስብሰባ በዴንማርክ ኮፐንሀገን ከተማ ደብረ ምሕረት ቅዱስ አማኑኤል ቤተ ክርስቲያን ከጥር 30 እስከ የካቲት 2 ቀን 2017 ዓ.ም አካሂደዋል።
በስብሰባው የደብሩ አስተዳዳሪ መልአከ ምሕረት ቆሞስ አባ ዘሚካኤል ዴሬሳ፣ አገልጋይ ካህን ቀሲስ ኃይለ ጊዮርጊስና የዴንማርክ ግንኙነት ጣቢያ አባላት ተገኝተዋል።
በዚህም የማእከሉ የ6 ወራት የአገልግሎት አፈጻጸም፣ የንዑሳን ማእከላትና የግንኙነት ጣቢያዎች አሁናዊ ሁኔታ ምን እንደሚመስል በመምከር ለቀጣይ የማእከሉ የአገልግሎት አቅጣጫዎች ዙሪያ ሰፊ ውይይት ተደርጓል።
"መልካም ሥራን ለመሥራት አንታክት" በሚል ርእስም በአባ ዘሚካኤል በማኀበራዊ ሕይወት ዙሪያ ትምህርት የተሰጠ ሲሆን ከመደበኛ የአገልግሎት ክንውን በተጨማሪም መንፈሳዊ ሕይወትን በሚመለከት የምክክር መርሐ ግብር ተከናውኗል፡፡
የገጽ ለገጽ ስብሰባ፥ የማእከሉ የሥራ አስፈጻሚ ጉባኤ አባላት በአካል በመገናኘት ይበልጥ የሚተዋወቁበትና የሚወያዩት በዓመት አንድ ጊዜ የሚካሄድ ልዩ መርሐግብር ነው፡፡
tgoop.com/mahibere_kidusan/8485
Create:
Last Update:
Last Update:
በአውሮፓ ማእከል የሥራ አስፈጻሚ ጉባኤ አባላት የገጽ ለገጽ ስብስባ ማካሄዱ ተገለጸ።
የካቲት ፬/፳፻፲፯ ዓ.ም
ማኅበረ ቅዱሳን በአውሮፓ ማእከል የሥራ አስፈጻሚ ጉባኤ አባላት የዘንድሮውን ዓመት የገጽ ለገጽ ስብሰባ በዴንማርክ ኮፐንሀገን ከተማ ደብረ ምሕረት ቅዱስ አማኑኤል ቤተ ክርስቲያን ከጥር 30 እስከ የካቲት 2 ቀን 2017 ዓ.ም አካሂደዋል።
በስብሰባው የደብሩ አስተዳዳሪ መልአከ ምሕረት ቆሞስ አባ ዘሚካኤል ዴሬሳ፣ አገልጋይ ካህን ቀሲስ ኃይለ ጊዮርጊስና የዴንማርክ ግንኙነት ጣቢያ አባላት ተገኝተዋል።
በዚህም የማእከሉ የ6 ወራት የአገልግሎት አፈጻጸም፣ የንዑሳን ማእከላትና የግንኙነት ጣቢያዎች አሁናዊ ሁኔታ ምን እንደሚመስል በመምከር ለቀጣይ የማእከሉ የአገልግሎት አቅጣጫዎች ዙሪያ ሰፊ ውይይት ተደርጓል።
"መልካም ሥራን ለመሥራት አንታክት" በሚል ርእስም በአባ ዘሚካኤል በማኀበራዊ ሕይወት ዙሪያ ትምህርት የተሰጠ ሲሆን ከመደበኛ የአገልግሎት ክንውን በተጨማሪም መንፈሳዊ ሕይወትን በሚመለከት የምክክር መርሐ ግብር ተከናውኗል፡፡
የገጽ ለገጽ ስብሰባ፥ የማእከሉ የሥራ አስፈጻሚ ጉባኤ አባላት በአካል በመገናኘት ይበልጥ የሚተዋወቁበትና የሚወያዩት በዓመት አንድ ጊዜ የሚካሄድ ልዩ መርሐግብር ነው፡፡
የካቲት ፬/፳፻፲፯ ዓ.ም
ማኅበረ ቅዱሳን በአውሮፓ ማእከል የሥራ አስፈጻሚ ጉባኤ አባላት የዘንድሮውን ዓመት የገጽ ለገጽ ስብሰባ በዴንማርክ ኮፐንሀገን ከተማ ደብረ ምሕረት ቅዱስ አማኑኤል ቤተ ክርስቲያን ከጥር 30 እስከ የካቲት 2 ቀን 2017 ዓ.ም አካሂደዋል።
በስብሰባው የደብሩ አስተዳዳሪ መልአከ ምሕረት ቆሞስ አባ ዘሚካኤል ዴሬሳ፣ አገልጋይ ካህን ቀሲስ ኃይለ ጊዮርጊስና የዴንማርክ ግንኙነት ጣቢያ አባላት ተገኝተዋል።
በዚህም የማእከሉ የ6 ወራት የአገልግሎት አፈጻጸም፣ የንዑሳን ማእከላትና የግንኙነት ጣቢያዎች አሁናዊ ሁኔታ ምን እንደሚመስል በመምከር ለቀጣይ የማእከሉ የአገልግሎት አቅጣጫዎች ዙሪያ ሰፊ ውይይት ተደርጓል።
"መልካም ሥራን ለመሥራት አንታክት" በሚል ርእስም በአባ ዘሚካኤል በማኀበራዊ ሕይወት ዙሪያ ትምህርት የተሰጠ ሲሆን ከመደበኛ የአገልግሎት ክንውን በተጨማሪም መንፈሳዊ ሕይወትን በሚመለከት የምክክር መርሐ ግብር ተከናውኗል፡፡
የገጽ ለገጽ ስብሰባ፥ የማእከሉ የሥራ አስፈጻሚ ጉባኤ አባላት በአካል በመገናኘት ይበልጥ የሚተዋወቁበትና የሚወያዩት በዓመት አንድ ጊዜ የሚካሄድ ልዩ መርሐግብር ነው፡፡
BY ማኅበረ ቅዱሳን ( Mahibere Kidusan)




Share with your friend now:
tgoop.com/mahibere_kidusan/8485